Sunday, March 31, 2024

https://youtu.be/ZNUAyQ1xc44?si=-jPFYaqTvKHql092

''ካሳ ገብሬ በቴፕ ልቅረፅህ አለኝ'' | ቆይታ ከ ዘገየ አስፋው ጋር | ጊዜ ግስ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189575
https://youtu.be/ZNUAyQ1xc44?si=-jPFYaqTvKHql092

''ካሳ ገብሬ በቴፕ ልቅረፅህ አለኝ'' | ቆይታ ከ ዘገየ አስፋው ጋር | ጊዜ ግስ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189575

Saturday, March 30, 2024

የጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ ስንብት (በፍርድ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደጃዝማች ዘውዴ ገ/ሥላሴ አገላለጽ)
መጋቢት 21 ቀን 1953 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 63 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የታኅሣሥ ግርግር በመባል በታሪክ መዝገብ የሚታወቀውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በግንባር ቀደምነት ያካሄዱት የነበሩት የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ በተቀበሉት ፍርድ መሠረት በስቅላት የተቆጡበት ዕለት ነበር።

የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ

የእልፍኝ አስከልካዩ ኮሎኔል አሰፋ ደምሴ (በኋላ ጄኔራል) መጋቢት 20 ቀን 1953 ዓ.ም ከሌሊቱ 9፡00 ስልክ ደውሎ “የጄኔራል መንግሥቱን የሞት ቅጣት ፍርድ ጃንሆይ አጽድቀውታል፡፡ ቅጣቱን በጧቱ እንድታስፈጽም አዘዋል፡፡

አንደኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ግቢ በቶሎ እንገናኝ” አለኝ፡፡ እንዳለኝ ቶሎ ተዘጋጅቼ ከተባለው ቦታ ስደርስ፣ ሽብር የተነሣ ይመስል በአካባቢው የነበረው ግርግር ሌላ ነበር፡፡ ከዚያ ለጄኔራል መንግሥቱን ሰላምታ ከሰጠሁት በኋላ የሞት ቅጣቱ የሚፈጸመው በዕለቱ ጧት መሆኑን ነገርኩት፡፡ ምንም ዐይነት የመደንገጥ ወይም የመናደድ ነገር አላሳየም፤ ምንም አልመሰለውም፡፡ ዝም ብሎ ተቀበለው፡፡

ኮሎኔል አሰፋ ቀለም ከመነከሩ በቀር በጣም ተራ የሆነ ስስ መርዶፍ፣ እጅጌው አጭር ሸሚዝና ቁምጣ ሱሪ የወህኒ ልብስ አምጥቶ ኑሮ “ያን ይልበስ” አለ፡፡ “አይሆንም” ብዬ በመጨቃጨቅ ጊዜ ካሳለፍን በኋላ፣ እኔ “ለጃንሆይ ይነገር እንጂ ይህንን ልብስ አልብሼ ቅጣቱን አላስፈጽምም” ስላልኩ፣ ሌሊት ጃንሆይ እንዲሰሙት ተደርጎ “እሽ የራሱን ልብስ ይልበስ” ብለው ስለፈቀዱ፣ የራሱን ልብስ ከለበሰ በኋላ በስሪ ኳርተር መኪና ላይ “ተሳፈር” ስንለው፣ “እሱን እሺ፤ ነገር ግን አንድ ጥያቄ አለኝ፤ ብትቀበሉኝ” አለ፡፡ “እሺ ጠይቅ” አልነው፡፡

“እዚህ ያሉት ወታደሮች ባይኔ አጥርቶ አለማየት ምክንያት ወደ ሽንት ቤት ስሄድ እቸገር ስለነበር ደግፈው ወስደው በማድረስ፣ በመመለስና የሚያስፈልገኝን ሁሉ በማድረግ ውለታ ውለውልኛልና እንዳመሰግን ብትሰበስቡልኝ ፈቃዳችሁን እጠይቃለሁ” አለ፡፡ ፈቀድንለትና የተሰበሰቡትን አመሰገናቸው፡፡ ወታደሮቹ ወጣቶች ስለነበሩ በሁኔታው መቆጨትና ማዘናቸው በፊታቸው ላይ ይታይ ነበር፡፡

ከዚያ በስሪ ኳርተሩ ላይ ተሳፍሮ በብዙ ወታደሮች ታጅቦ ተክለሃይማኖት አደባባይ ከመስቀያው ቦታ እንደ ደረስን፣ ወደ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዞሮ እጅ እንዲነሣ አደረግን፡፡ ከዚያ ገመዱን ከዐንገቱ ላይ ሊያገቡ ሲሉ ኮሎኔል አሰፋ ደምሴ “አላይም” ብሎ መሄድ እንደ ጀመረ፣ “ጥሩት” ብሎ አስጠራውና “እባክህ እነዚህ ሰዎች አያውቁትምና የገመዱን ቋጠሮ በተገቢው ቦታ እንዲያደርጉት ንገርልኝ” አለው፡፡

ይህን ያለበት ምክንያት በላይ ዘለቀ ሲሰቀል ገመዱ በትክክለኛው ቦታ ባለመሆኑ የደረሰውን ሥቃይ ዐይቶ ስለነበር ነው፡፡ እሱም “እሺ” ብሎ ለሰዎቹ ነገራቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ገመዱን በተገቢው መንገድ አደረጉለትና መኪናው ወደፊት ሄደ፡፡ ብዙም አልቆየ፣ ነፍሱ ወዲያው ዐለፈ፡፡

#ታሪክን_ወደኋላ

ዩቲዩብ- youtube.com/@TariknWedehuala11

ቴሌግራም- t.me/TariknWedehuala

ቲክ ቶክ- tiktok.com/@tariknwedehuala
https://amharic.zehabesha.com/archives/189564
የጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ ስንብት (በፍርድ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደጃዝማች ዘውዴ ገ/ሥላሴ አገላለጽ)
መጋቢት 21 ቀን 1953 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 63 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የታኅሣሥ ግርግር በመባል በታሪክ መዝገብ የሚታወቀውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በግንባር ቀደምነት ያካሄዱት የነበሩት የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ በተቀበሉት ፍርድ መሠረት በስቅላት የተቆጡበት ዕለት ነበር።

የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ

የእልፍኝ አስከልካዩ ኮሎኔል አሰፋ ደምሴ (በኋላ ጄኔራል) መጋቢት 20 ቀን 1953 ዓ.ም ከሌሊቱ 9፡00 ስልክ ደውሎ “የጄኔራል መንግሥቱን የሞት ቅጣት ፍርድ ጃንሆይ አጽድቀውታል፡፡ ቅጣቱን በጧቱ እንድታስፈጽም አዘዋል፡፡

አንደኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ግቢ በቶሎ እንገናኝ” አለኝ፡፡ እንዳለኝ ቶሎ ተዘጋጅቼ ከተባለው ቦታ ስደርስ፣ ሽብር የተነሣ ይመስል በአካባቢው የነበረው ግርግር ሌላ ነበር፡፡ ከዚያ ለጄኔራል መንግሥቱን ሰላምታ ከሰጠሁት በኋላ የሞት ቅጣቱ የሚፈጸመው በዕለቱ ጧት መሆኑን ነገርኩት፡፡ ምንም ዐይነት የመደንገጥ ወይም የመናደድ ነገር አላሳየም፤ ምንም አልመሰለውም፡፡ ዝም ብሎ ተቀበለው፡፡

ኮሎኔል አሰፋ ቀለም ከመነከሩ በቀር በጣም ተራ የሆነ ስስ መርዶፍ፣ እጅጌው አጭር ሸሚዝና ቁምጣ ሱሪ የወህኒ ልብስ አምጥቶ ኑሮ “ያን ይልበስ” አለ፡፡ “አይሆንም” ብዬ በመጨቃጨቅ ጊዜ ካሳለፍን በኋላ፣ እኔ “ለጃንሆይ ይነገር እንጂ ይህንን ልብስ አልብሼ ቅጣቱን አላስፈጽምም” ስላልኩ፣ ሌሊት ጃንሆይ እንዲሰሙት ተደርጎ “እሽ የራሱን ልብስ ይልበስ” ብለው ስለፈቀዱ፣ የራሱን ልብስ ከለበሰ በኋላ በስሪ ኳርተር መኪና ላይ “ተሳፈር” ስንለው፣ “እሱን እሺ፤ ነገር ግን አንድ ጥያቄ አለኝ፤ ብትቀበሉኝ” አለ፡፡ “እሺ ጠይቅ” አልነው፡፡

“እዚህ ያሉት ወታደሮች ባይኔ አጥርቶ አለማየት ምክንያት ወደ ሽንት ቤት ስሄድ እቸገር ስለነበር ደግፈው ወስደው በማድረስ፣ በመመለስና የሚያስፈልገኝን ሁሉ በማድረግ ውለታ ውለውልኛልና እንዳመሰግን ብትሰበስቡልኝ ፈቃዳችሁን እጠይቃለሁ” አለ፡፡ ፈቀድንለትና የተሰበሰቡትን አመሰገናቸው፡፡ ወታደሮቹ ወጣቶች ስለነበሩ በሁኔታው መቆጨትና ማዘናቸው በፊታቸው ላይ ይታይ ነበር፡፡

ከዚያ በስሪ ኳርተሩ ላይ ተሳፍሮ በብዙ ወታደሮች ታጅቦ ተክለሃይማኖት አደባባይ ከመስቀያው ቦታ እንደ ደረስን፣ ወደ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዞሮ እጅ እንዲነሣ አደረግን፡፡ ከዚያ ገመዱን ከዐንገቱ ላይ ሊያገቡ ሲሉ ኮሎኔል አሰፋ ደምሴ “አላይም” ብሎ መሄድ እንደ ጀመረ፣ “ጥሩት” ብሎ አስጠራውና “እባክህ እነዚህ ሰዎች አያውቁትምና የገመዱን ቋጠሮ በተገቢው ቦታ እንዲያደርጉት ንገርልኝ” አለው፡፡

ይህን ያለበት ምክንያት በላይ ዘለቀ ሲሰቀል ገመዱ በትክክለኛው ቦታ ባለመሆኑ የደረሰውን ሥቃይ ዐይቶ ስለነበር ነው፡፡ እሱም “እሺ” ብሎ ለሰዎቹ ነገራቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ገመዱን በተገቢው መንገድ አደረጉለትና መኪናው ወደፊት ሄደ፡፡ ብዙም አልቆየ፣ ነፍሱ ወዲያው ዐለፈ፡፡

#ታሪክን_ወደኋላ

ዩቲዩብ- youtube.com/@TariknWedehuala11

ቴሌግራም- t.me/TariknWedehuala

ቲክ ቶክ- tiktok.com/@tariknwedehuala
https://amharic.zehabesha.com/archives/189564

Friday, March 29, 2024

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! የሜ/ጀኔራሎቹ የደም መሬት! Bombard the Orommuma Headquarter!››
ኢት-ኢኮኖሚ            /ET- ECONOMY

(ክፍል ሁለት)   ፂዮን ዘማርያም (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! Bombard the Orommuma Headquarter!!!››

‹‹አማራን አደህይቶ መግዛት መርሃ-ግብር!!!››ፊንፊኔ፣ቢሸፉቱ፣አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ኦሮሙማ በሰማይ ሲያይሽ ዋለ!

‹‹በሚፈርስ ከተማ ……….ነጋሪት ቢጎሰም………….አይሰማ!!!››

‹‹የማን ቤት ፈርሷ፣ የማን ሊበጅ

የአውሬ መፈንጫ፣ ይሆናል እንጅ››

የተባበሩት መንግሥታት የስብዓዊ ጉዳዬች ቢሮ  የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ማርች አንድ ቀን 2024 እኤአ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በዚህም መሠረት በ2024 እኤአ በኢትዮጵያ ለ15.5 (አስራአምስት ነጥብ አምስት) ሚሊዮን ህዝብ  ሁለገብ ስብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ያስፈልገዋል፡፡  ከኢትዮጵያ ህዝብ 4.4 (አራት ነጥብ አራት) ሚሊዮን ህዝብ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዬች ሲሆኑ በተለያዩ ግጭት፣ በጦርነትና፣  የዓየር ለውጥ ቀውስ የተነሳ ሁለገብ ድጋፍ ይሻሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትና የስብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች በጋራ  3.2 (ሦስት ነጥብ ሁለት)ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡US$3.2 billion required in 2024 to provide multisectoral humanitarian assistance to 15.5 million Ethiopians – Government of Ethiopia, humanitarian community joint appeal. 4.4 million internally displaced people severely impacted by conflict, hostilities and climate shocks require scaled up multi-sectoral assistance………………………(1)

በኢትዮጵያ  4.4 (አራት ነጥብ አራት) ሚሊዮን ህዝብ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዬች በድንኳን ውስጥ ለአመታት በመኖር ላይ ይገኛሉ ኮነሬል አብይ አህመድ ጨካኝ ሥርዓት እነሱን ከማስፈር ይልቅ የአዲስ አበባን ቤቶች በማፍረስ ስራ ላይ ተጠምዶል፡፡ የከተማ ሌላ ግማሽሚሊየን ተፈናቃይ በመፍጠር ላይ ይገኛሉ፡፡  አብይ አህመድ በዚህ የጭካኜ ሥራው ካልወደቀ መቼም አይወድቅ፣ የአማራ ፋኖም በድል አድራጊነት ሥራዓቱን ካልጣለ መቼም አያሸንፍ ከጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ የተውጣጣ መቶ ሽህ ፋኖ በአዲስ አበባ ቢገባ ወዲያው ስድስት ሚሊዮን ፋኖ ይሆናል ቃል ለምድረ ለሰማይ!!! የፋኖ መግቢያ መንገዶች  የደብረብርሃን በር፣ የባህርዳር በር፣የጅማ በር፣ አንቦ በር፣ አዳማ በር በኩል ፋኖ ዘው ብሎ ቢገባ ኮነሬል አብይ ዱባይ ወይ በሻሻ ይገባል፡፡ ልጆቹን ካሸሸ ቆይቶል፡፡ ሽመልስ አብዲሳ አንቦ ይሸሻል፣ አዳነች አቤቤ ቅቤ ተቀብታ አርሲ ተሰደድ ነበር፡፡  እስክንድር ብቻውን ቢገባ በስሙ ብቻ ጠቅላይ ጦር ሠፈሩን ይቆጣጠራል፣ያሸንፋል!!! እኛጋ ያለ ፍርሃት እኳ በእነሱ ይብሳል!!! የአዱ ገነት ከተማ አብዬት አብዬት ሸታለች፡፡ ህዝብ የሚበላው አጥቶል፣ ምድረ ዞንቢዎች ብዙ ቲዎሪ ቅመራ አይሠራም፤ አንድ ሽህ የኢህአፓ ወንዶች በሸፈቱባት መዲና፣ ሻለቃ መንግስቱን ሙሃሂቴን ያሰኙት ትንታጎች ዛሬ ቢኖሩ ኖሩ ደም መላሽ በሆኖት ነበር፡፡ የእምዬ ምኒልክ ከተማ፣ የእቴጌ ጣይቱ መዲና እናታችን አዲስ አበባ የሚታደጋት አጥታ አለቀሰች….አለቀሰች…..

‹‹አዲስ አበባ ላይ ትልቅ ድህነትና ችግር ያለው  ሴንተር ነው፡፡ መርካቶ፣ ፒያሳ፣ ሜክሴካ፣ የሚባለው ነው፡፡ ሲኤምሲ እንደዛ አይደለም፣ ለቡ እንደዛ አይደለም፣ ዋናው ችግር እዚህ ነው፡፡ዋናውን ችግር ደፍረን ብናፈርሰው ታያላችሁ በአምስት አመት ከተማው ምን እንደሚመስል፡፡››ኮነሬል አብይ አህመድ

‹‹ያፈረስነው ጭቃ ነው ቅርስ አይደለም!!!›› ኮነሬል አብይ አህመድ

‹አዲስ አበባ ላይ መዝሙር ተዘመረ ኦሮሙኛ እና ተረኝነት ነው የሚል ተረት ነበር፡፡ አዲስ አበባ ላይ ከፍተኛ ኦሮሞ ጠል ኃይሎች ኦሮሞን የሚጠሉ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር የሚያስቡ ሰዎች ኦሮሞኛ ተዘመረ አሉ!!!›› ኮነሬል  አብይ አህመድ

‹‹ፊንፊኔ ላይ የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ እጅግ በጣም ቀላልና አንድ ነገር ብቻ ናት፡፡ እርሶም ፊንፊኔ በኦሮሚያ አስተዳደር ስር መመለስ ብቻ ነው፡፡ በኦሮሚያ አስተዳደር ስር አልተዳደርም የሚል ዘረ ካለ ወደ መጣበት ክልሉ መሄድ ይችላል፡፡ አሻፈረኝ የሚል ጥጋበኛ ደግሞ ካለ በህግ ልክ ማስገባት ነው፡፡ ስለዚህ እባካችሁ ማጭበርበሩን ሌብነቱንና ማወናበዱን ተውትና ህጋዊ ስራ ስሩ፡፡ እነርሱ ሲወሩን የእኛን ፍቃድ ጠይቀውና አማክረውን ነው እንዴ?››……. “የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአዲስ አበባ ከንቲባ መሆን ያለበት ኦሮሞ ብቻ ነው” ብርሃነመስቀል አበበ ሰኝ፣

ፒያሳ ‹‹አስራአንድ ሽህ ሰዎች አፈናቅለናል!!!›› አዳነች አቤቤ

‹‹ይሄ የአዲስአበባ ህዝብ አጀንዳ አይደለም፡፡ ይሄ የነሸኔ የተለያዩ እነ ጽንፈኞ ፋኖ ከዚያ በኃላ ደሞ ምዕራባዊያን እጅ ያለበት አጀንዳ ነው፡፡›› አዳነች አቤቤ

‹‹ኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ትውጣ!!!››…“Ethiopia out of Oromia!” ….‹‹ዲቃላ›› ጁሃር መሃመድ፣

‹‹እንደሰባበሩን ሰባበርናቸው›› ‹‹አዲስ አበባን ኦሮሙማ እያደረግናት ነው!!!›› ሽመልስ አብዲሳ፣

 

‹‹አማራን አደህይቶ መግዛት መርሃ-ግብር!!!›› የአማራ ትግል በህይወት የመኖር የህልውና ትግል ነው፣ የመኖርና ያለመኖር አደጋ ነው ስንል

የኮነሬል አብይ አህመድ የእግረኛ መከላከያ ሠራዊት ቁጥር 350000 ከ(ሦስት መቶ ሃምሳ ሽህ) ወደ 59000 (ሃምሳ ዘጠኝ ሽህ)  መውረዱ ምክንያት የሌሎች ክልሎች መንግሥት ሠራዊት እንዲያዋጡ ትእዛዝ ወርዶላቸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከትግራይ መንግሥት ሃያ ሽህ ሠራዊት፣ ከደቡብ ክልል አሥር ሽህ ሠራዊት፣ ሱማሌ ክልል አምስት ሽህ ወታደር፣ ቤኒሻንጉል ክልል አምስት ሽህ፣ ጋምቤላ ክልል አምስት ሽህ ፣ አፋር ክልል አምሰት ሽህ ወታደር እንዲያዋጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል የወታደር መዋጮ አልተጣለበትም፣ ኮነሬል አብይ የኢትዮጵያ ሠራዊት በኦሮሞ ልጆች የተዋቀረ በማድረግ ተዋፅኦቸውን ከፍተኛ በመሆኑ የተነሳ በመሆኑ ነው፡፡

በኮነሬል አብይ አህመድ አገዛዝ፣ የብአዴን ብልፅግና ካድሬዎች ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጋር በማሴር አንድ የአማራ ፋኖ  እዝ እንዳይመሠረት የጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ እዞች ህብረት እንዳይመሠረቱ የሚያደርግ ስውር ቡድን 300 (ሦስት መቶ) ሚሊዮን ብር ተመድቦላቸው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡

የአማራ ክልላዊ መንግሥትን  የኢንተርኔት አገልግሎት መቆረጥ በኢኮኖሚው ላይ ተፅዕኖና ኪሳራ አስከትሎል፡፡

የአማራ ክልላዊ መንግሥትን የፍትህ ሚኒስቴር 107 260 (መቶ ሰባት ሽህ ሁለት መቶ ስልሳ) እስረኞች በኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛሉ፣ ከዚህ ውስጥ አብዛናዎቹ የፖለቲካ እስረኞች አማራዎች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ በአዲስ አበባ (ቅሊንጦ)፣ ሸዋ ሮቢት፣ ድሬዳዋ፣ ዝዋይ፣ እስርቤቶች ሌሎች ወህኒ ቤቶች እየተገነቡ እንደሆነ ተገልፆል፡፡

 

የኮነሬል አብይ መከላከያ ሠራዊት፣ ኮማንድ ፖስት ለተጎጂዎች የእህል እርዳታ እንዳይደርስ በማድረግ አካሂዶል፡፡ የአማራ ህዝብ የረድዔት ስብዓዊ ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶች ከክልሉ እንዲወጡ አድርጎል፡፡ የአማራን ደሃ ገበሬዎች አደህይቶ ለመግዛት፣ የቁም ከብቶቻቸውን አርዶ በመብላትና ቀሪዎቹን በመንዳት  ወንጀል ሥራ ተጠምደዋል፡፡ የአማራ ገበሬዎች ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እንዳይገዙ አግዶል፡፡ በአለፈው አመት በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እጦት የተነሳ፣ በደንብ ማረስ አልቻልንም፡፡ በዚህ አመትም በደንብ ማረስ ካልቻልን የመኖር ህልውናችን አስጊ ሁኔታ ላይ ይደርሳል፡፡ የአማራ ህዝብ ጥያቄ የህልውና ነው ስንል ለዚህ ነው፡፡ ጦርነቱን በቶሎ መጨረስ የሚገባን ለዘላቂ ህልውናችን ስንል ነው፡፡ ኮማንድ ፖስቱ በቀሰቀሱት ጦርነት የገበሬውን ተመርቶ የተከመረውን እህል አቃጠሉት፣ የነጋዴውን የእህል ጎተራ ዘረፉት ይህ ድርጊት ህዝቡን ለማስራብ የታቀደ ፋሽስታዊ ሴራ  ነው፡፡ በትግራይ ጦርነት ጊዜ ፈፅመውታል፣ ህዝቡን አስርበው ገድለውታል፣ የእርዳታ ድርጅቶች አህል እንዳያደርሱ መንገዶቹን ዘግተው በርሃብ እንዲያልቅ አድርገዋል፡፡ ኮማንድ ፖስት ሰዎችን ወህኒ በማውረድና ቶርቸር በማድረግ፣ በሲቪላውያን የጂምላ ግድያ ወንጀል ፈፅሟል፡፡ የአማራ ህዝብ ምሁራንና ታዋቂ ሰዎች ማፈንና አስገድዶ መሰወር ብሎም ለታጋቾች ገንዘብ በመጠየቅ ወንጀል ተግባር ተጠምደዋል፡፡ ኮማንድ ፖስት ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች ዘግተዋል፡፡

የኃይማኖት ተቆማትን ማዳከም በተለይ የኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያናትንና የሙስሊም መስጊዶችን የማፍረስ መርሃ-ግብር  በአዲስ አበባ ከተማ ከሃያ የበለጡ መስጊዶች ፈርሰዋል፡፡ ቤተክርስቲያን ተቃጥለዋል ፣ አገልጋዬች ታርደዋል፡፡ በምድሪቱ ላይ መንግሥት የለም!!! ህግ የለም! ህገ-መንግስት የለም!!!ነሬል አብይ ከሞተ እኳ ቆይቶል! ጎስቱ ነው የሚገዛን! አዲስ አበባን እንዲህ ሲያወድሞት እያየን ዝም እንል ነበር፣ ቢያንስ ቢያንስ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ የኡኡታ አናሰማም!! ኡኡታና ትሪ ማንኮኮት አደማ አይደረግም፣ ቀጥለንስ  የሦስት ቀናት የቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ አናደርግም፡፡ የአዲሰ አበባ ፋኖ ይህን አድማ ካልጠራ የኮነሬል አብይ ቅጥረኛ ላለመሆኑ በምን እናውቃለን፡፡ ‹‹ባትዋጋ እንኳ በል እንገፍ እንገፍ፣ የአባትህ ጋሻ ትኻኑ ይርገፍ!!!›› ‹‹Mass protests broke out in Addis Ababa following Friday prayers as a result of anger over mosque demolitions in the neighboring Shegger city. The demonstrations took place around mosques in the capital yesterday, May 23, 2023, including the Grand Anwar Mosque. Demonstrators called for an immediate stop to the demolitions as well as the rebuilding of the 19 mosques already razed during the last few weeks. Social media outcry has escalated due to the demolitions, with videos showing police officers in riot gear blocking angry protesters circulating widely››…………………..(2)

‹‹አዲስ አበባ ላይ ትልቅ ድህነትና ችግር ያለው ሴንተር ነው፡፡ መርካቶ፣ ፒያሳ፣ ሜክሴካ፣የሚባለው ነው፡፡ ሲኤምሲ እንደዛ አይደለም፣ ለቡ እንደዛ አይደለም፣ ዋናው ችግር እዚህ ነው፡፡ዋናውን ችግር ደፍረን ብናፈርሰው ታያላችሁ በአምስት አመት ከተማውምን እንደሚመስል፡፡››ኮነሬል አብይ አህመድ ለሜ/ጀኔራሎቹ የደሃ መሬት እየነጠቀ ይሸልማል፡፡ የአዲስ አበባን የደሃ ቤቶች እያፈረሰ ፓርክና ቤተ-መንግሥት ይገነባል፡፡ ደሃ ከቆረጠ አጥፍቶ ማጥፋት የእናንተንም ቤት ማፍረስ፣ የናንተንም ሥራ ማጥፋት የደቂቃ ሰከንድ ሥራ መሆኑን እወቁት፣ የእናንተ አይፈርስም ያላችሁ ማን ነው!!! እነእንትና!!! እነእንትና የጅብ ጥላ! ከዲያስፖራ  ዶላር ላታገኝ በመለመን  ስትጣላ እድሜህን አትግፋ!!!

የደም መሬት፡-ከደም መሬት የሚቆደሱ ጀነራል መኮንኖች አዲስ አበባን ከተማ ምርጥ አንደኛ ደረጃ ቦታዎች በገፀ-በረከትነት በኮነሬል አብይ አህመድ ተበርክቶላቸዋል፡፡ ጀነራሎቹ በታማኝነት ህዝብ በመግደል፣ ቤቶች በማፍረስና በማቃጠል፣ የህዝብን እንቢተኛነትና ህዝባዊ አመፅን በማፈን ሥርዓቱን በመጠበቃቸው የተከፈላቸው የደም ዋጋ ነው፡፡ የደም መሬቱን በሁለት መቶና ሦስት መቶ ሚሊዮን ሸጠው የደም ገንዘብ ያገኛሉ፡፡

{1} ሜ/ጀኔራል ጥሩዬ አሰፋ፣ ኮልፌ 1000ካሜ

{2} ሜ/ጀኔራል ከፍያለው ምዴ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{3} ሜ/ጀኔራል አብዱ ከድር ንፋስ ስልክ1000ካሜ

{4} ሜ/ጀኔራል ሰለሞን ቦጋለ መኮነንን ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{5}ሜ/ጀኔራል ሙላቱ ጀልዱ ዋቅጂራ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{6} ሜ/ጀኔራል አማረ ገብሩ ሀይሉ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{7} ሜ/ጀኔራል አድማሱ አለሙ ወ/ሰንበት ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{8} ሜ/ጀኔራል ሙሉአለም አድማሱ ካህሱንፋስ ስልክ1000ካሜ

{9} ሜ/ጀኔራል አዳምነህ መንግሥቴ ገብሬንፋስ ስልክ1000ካሜ

{10} ሜ/ጀኔራል ኢተፋ ራጋ ሜኮ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{11} ሜ/ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን በርሄ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{12} ሜ/ጀኔራል ታገሰ ላምባሞ ዱምቦሬ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{13} ሜ/ጀኔራል ግርማ ከበበው ቱፋ ንፋስ ስልክ1000ካሜ

{14} ሜ/ጀኔራል ፍቃዱ ጸጋዬ እምሩ ቦሌ 1000ካሜ

{15} ሜ/ጀኔራልታደሰ መኩሪያ ንፋስስልክ 1000ካሜ

{16} ሜ/ጀኔራልግዛው ኡማ አብዲ ኮልፌ 1000ካሜ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189555
‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! የሜ/ጀኔራሎቹ የደም መሬት! Bombard the Orommuma Headquarter!››
ኢት-ኢኮኖሚ            /ET- ECONOMY

(ክፍል ሁለት)   ፂዮን ዘማርያም (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! Bombard the Orommuma Headquarter!!!››

‹‹አማራን አደህይቶ መግዛት መርሃ-ግብር!!!››ፊንፊኔ፣ቢሸፉቱ፣አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ኦሮሙማ በሰማይ ሲያይሽ ዋለ!

‹‹በሚፈርስ ከተማ ……….ነጋሪት ቢጎሰም………….አይሰማ!!!››

‹‹የማን ቤት ፈርሷ፣ የማን ሊበጅ

የአውሬ መፈንጫ፣ ይሆናል እንጅ››

የተባበሩት መንግሥታት የስብዓዊ ጉዳዬች ቢሮ  የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ማርች አንድ ቀን 2024 እኤአ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በዚህም መሠረት በ2024 እኤአ በኢትዮጵያ ለ15.5 (አስራአምስት ነጥብ አምስት) ሚሊዮን ህዝብ  ሁለገብ ስብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ያስፈልገዋል፡፡  ከኢትዮጵያ ህዝብ 4.4 (አራት ነጥብ አራት) ሚሊዮን ህዝብ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዬች ሲሆኑ በተለያዩ ግጭት፣ በጦርነትና፣  የዓየር ለውጥ ቀውስ የተነሳ ሁለገብ ድጋፍ ይሻሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትና የስብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች በጋራ  3.2 (ሦስት ነጥብ ሁለት)ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡US$3.2 billion required in 2024 to provide multisectoral humanitarian assistance to 15.5 million Ethiopians – Government of Ethiopia, humanitarian community joint appeal. 4.4 million internally displaced people severely impacted by conflict, hostilities and climate shocks require scaled up multi-sectoral assistance………………………(1)

በኢትዮጵያ  4.4 (አራት ነጥብ አራት) ሚሊዮን ህዝብ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዬች በድንኳን ውስጥ ለአመታት በመኖር ላይ ይገኛሉ ኮነሬል አብይ አህመድ ጨካኝ ሥርዓት እነሱን ከማስፈር ይልቅ የአዲስ አበባን ቤቶች በማፍረስ ስራ ላይ ተጠምዶል፡፡ የከተማ ሌላ ግማሽሚሊየን ተፈናቃይ በመፍጠር ላይ ይገኛሉ፡፡  አብይ አህመድ በዚህ የጭካኜ ሥራው ካልወደቀ መቼም አይወድቅ፣ የአማራ ፋኖም በድል አድራጊነት ሥራዓቱን ካልጣለ መቼም አያሸንፍ ከጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ የተውጣጣ መቶ ሽህ ፋኖ በአዲስ አበባ ቢገባ ወዲያው ስድስት ሚሊዮን ፋኖ ይሆናል ቃል ለምድረ ለሰማይ!!! የፋኖ መግቢያ መንገዶች  የደብረብርሃን በር፣ የባህርዳር በር፣የጅማ በር፣ አንቦ በር፣ አዳማ በር በኩል ፋኖ ዘው ብሎ ቢገባ ኮነሬል አብይ ዱባይ ወይ በሻሻ ይገባል፡፡ ልጆቹን ካሸሸ ቆይቶል፡፡ ሽመልስ አብዲሳ አንቦ ይሸሻል፣ አዳነች አቤቤ ቅቤ ተቀብታ አርሲ ተሰደድ ነበር፡፡  እስክንድር ብቻውን ቢገባ በስሙ ብቻ ጠቅላይ ጦር ሠፈሩን ይቆጣጠራል፣ያሸንፋል!!! እኛጋ ያለ ፍርሃት እኳ በእነሱ ይብሳል!!! የአዱ ገነት ከተማ አብዬት አብዬት ሸታለች፡፡ ህዝብ የሚበላው አጥቶል፣ ምድረ ዞንቢዎች ብዙ ቲዎሪ ቅመራ አይሠራም፤ አንድ ሽህ የኢህአፓ ወንዶች በሸፈቱባት መዲና፣ ሻለቃ መንግስቱን ሙሃሂቴን ያሰኙት ትንታጎች ዛሬ ቢኖሩ ኖሩ ደም መላሽ በሆኖት ነበር፡፡ የእምዬ ምኒልክ ከተማ፣ የእቴጌ ጣይቱ መዲና እናታችን አዲስ አበባ የሚታደጋት አጥታ አለቀሰች….አለቀሰች…..

‹‹አዲስ አበባ ላይ ትልቅ ድህነትና ችግር ያለው  ሴንተር ነው፡፡ መርካቶ፣ ፒያሳ፣ ሜክሴካ፣ የሚባለው ነው፡፡ ሲኤምሲ እንደዛ አይደለም፣ ለቡ እንደዛ አይደለም፣ ዋናው ችግር እዚህ ነው፡፡ዋናውን ችግር ደፍረን ብናፈርሰው ታያላችሁ በአምስት አመት ከተማው ምን እንደሚመስል፡፡››ኮነሬል አብይ አህመድ

‹‹ያፈረስነው ጭቃ ነው ቅርስ አይደለም!!!›› ኮነሬል አብይ አህመድ

‹አዲስ አበባ ላይ መዝሙር ተዘመረ ኦሮሙኛ እና ተረኝነት ነው የሚል ተረት ነበር፡፡ አዲስ አበባ ላይ ከፍተኛ ኦሮሞ ጠል ኃይሎች ኦሮሞን የሚጠሉ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር የሚያስቡ ሰዎች ኦሮሞኛ ተዘመረ አሉ!!!›› ኮነሬል  አብይ አህመድ

‹‹ፊንፊኔ ላይ የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ እጅግ በጣም ቀላልና አንድ ነገር ብቻ ናት፡፡ እርሶም ፊንፊኔ በኦሮሚያ አስተዳደር ስር መመለስ ብቻ ነው፡፡ በኦሮሚያ አስተዳደር ስር አልተዳደርም የሚል ዘረ ካለ ወደ መጣበት ክልሉ መሄድ ይችላል፡፡ አሻፈረኝ የሚል ጥጋበኛ ደግሞ ካለ በህግ ልክ ማስገባት ነው፡፡ ስለዚህ እባካችሁ ማጭበርበሩን ሌብነቱንና ማወናበዱን ተውትና ህጋዊ ስራ ስሩ፡፡ እነርሱ ሲወሩን የእኛን ፍቃድ ጠይቀውና አማክረውን ነው እንዴ?››……. “የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአዲስ አበባ ከንቲባ መሆን ያለበት ኦሮሞ ብቻ ነው” ብርሃነመስቀል አበበ ሰኝ፣

ፒያሳ ‹‹አስራአንድ ሽህ ሰዎች አፈናቅለናል!!!›› አዳነች አቤቤ

‹‹ይሄ የአዲስአበባ ህዝብ አጀንዳ አይደለም፡፡ ይሄ የነሸኔ የተለያዩ እነ ጽንፈኞ ፋኖ ከዚያ በኃላ ደሞ ምዕራባዊያን እጅ ያለበት አጀንዳ ነው፡፡›› አዳነች አቤቤ

‹‹ኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ትውጣ!!!››…“Ethiopia out of Oromia!” ….‹‹ዲቃላ›› ጁሃር መሃመድ፣

‹‹እንደሰባበሩን ሰባበርናቸው›› ‹‹አዲስ አበባን ኦሮሙማ እያደረግናት ነው!!!›› ሽመልስ አብዲሳ፣

 

‹‹አማራን አደህይቶ መግዛት መርሃ-ግብር!!!›› የአማራ ትግል በህይወት የመኖር የህልውና ትግል ነው፣ የመኖርና ያለመኖር አደጋ ነው ስንል

የኮነሬል አብይ አህመድ የእግረኛ መከላከያ ሠራዊት ቁጥር 350000 ከ(ሦስት መቶ ሃምሳ ሽህ) ወደ 59000 (ሃምሳ ዘጠኝ ሽህ)  መውረዱ ምክንያት የሌሎች ክልሎች መንግሥት ሠራዊት እንዲያዋጡ ትእዛዝ ወርዶላቸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከትግራይ መንግሥት ሃያ ሽህ ሠራዊት፣ ከደቡብ ክልል አሥር ሽህ ሠራዊት፣ ሱማሌ ክልል አምስት ሽህ ወታደር፣ ቤኒሻንጉል ክልል አምስት ሽህ፣ ጋምቤላ ክልል አምስት ሽህ ፣ አፋር ክልል አምሰት ሽህ ወታደር እንዲያዋጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል የወታደር መዋጮ አልተጣለበትም፣ ኮነሬል አብይ የኢትዮጵያ ሠራዊት በኦሮሞ ልጆች የተዋቀረ በማድረግ ተዋፅኦቸውን ከፍተኛ በመሆኑ የተነሳ በመሆኑ ነው፡፡

በኮነሬል አብይ አህመድ አገዛዝ፣ የብአዴን ብልፅግና ካድሬዎች ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጋር በማሴር አንድ የአማራ ፋኖ  እዝ እንዳይመሠረት የጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ እዞች ህብረት እንዳይመሠረቱ የሚያደርግ ስውር ቡድን 300 (ሦስት መቶ) ሚሊዮን ብር ተመድቦላቸው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡

የአማራ ክልላዊ መንግሥትን  የኢንተርኔት አገልግሎት መቆረጥ በኢኮኖሚው ላይ ተፅዕኖና ኪሳራ አስከትሎል፡፡

የአማራ ክልላዊ መንግሥትን የፍትህ ሚኒስቴር 107 260 (መቶ ሰባት ሽህ ሁለት መቶ ስልሳ) እስረኞች በኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛሉ፣ ከዚህ ውስጥ አብዛናዎቹ የፖለቲካ እስረኞች አማራዎች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ በአዲስ አበባ (ቅሊንጦ)፣ ሸዋ ሮቢት፣ ድሬዳዋ፣ ዝዋይ፣ እስርቤቶች ሌሎች ወህኒ ቤቶች እየተገነቡ እንደሆነ ተገልፆል፡፡

 

የኮነሬል አብይ መከላከያ ሠራዊት፣ ኮማንድ ፖስት ለተጎጂዎች የእህል እርዳታ እንዳይደርስ በማድረግ አካሂዶል፡፡ የአማራ ህዝብ የረድዔት ስብዓዊ ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶች ከክልሉ እንዲወጡ አድርጎል፡፡ የአማራን ደሃ ገበሬዎች አደህይቶ ለመግዛት፣ የቁም ከብቶቻቸውን አርዶ በመብላትና ቀሪዎቹን በመንዳት  ወንጀል ሥራ ተጠምደዋል፡፡ የአማራ ገበሬዎች ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እንዳይገዙ አግዶል፡፡ በአለፈው አመት በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እጦት የተነሳ፣ በደንብ ማረስ አልቻልንም፡፡ በዚህ አመትም በደንብ ማረስ ካልቻልን የመኖር ህልውናችን አስጊ ሁኔታ ላይ ይደርሳል፡፡ የአማራ ህዝብ ጥያቄ የህልውና ነው ስንል ለዚህ ነው፡፡ ጦርነቱን በቶሎ መጨረስ የሚገባን ለዘላቂ ህልውናችን ስንል ነው፡፡ ኮማንድ ፖስቱ በቀሰቀሱት ጦርነት የገበሬውን ተመርቶ የተከመረውን እህል አቃጠሉት፣ የነጋዴውን የእህል ጎተራ ዘረፉት ይህ ድርጊት ህዝቡን ለማስራብ የታቀደ ፋሽስታዊ ሴራ  ነው፡፡ በትግራይ ጦርነት ጊዜ ፈፅመውታል፣ ህዝቡን አስርበው ገድለውታል፣ የእርዳታ ድርጅቶች አህል እንዳያደርሱ መንገዶቹን ዘግተው በርሃብ እንዲያልቅ አድርገዋል፡፡ ኮማንድ ፖስት ሰዎችን ወህኒ በማውረድና ቶርቸር በማድረግ፣ በሲቪላውያን የጂምላ ግድያ ወንጀል ፈፅሟል፡፡ የአማራ ህዝብ ምሁራንና ታዋቂ ሰዎች ማፈንና አስገድዶ መሰወር ብሎም ለታጋቾች ገንዘብ በመጠየቅ ወንጀል ተግባር ተጠምደዋል፡፡ ኮማንድ ፖስት ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች ዘግተዋል፡፡

የኃይማኖት ተቆማትን ማዳከም በተለይ የኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያናትንና የሙስሊም መስጊዶችን የማፍረስ መርሃ-ግብር  በአዲስ አበባ ከተማ ከሃያ የበለጡ መስጊዶች ፈርሰዋል፡፡ ቤተክርስቲያን ተቃጥለዋል ፣ አገልጋዬች ታርደዋል፡፡ በምድሪቱ ላይ መንግሥት የለም!!! ህግ የለም! ህገ-መንግስት የለም!!!ነሬል አብይ ከሞተ እኳ ቆይቶል! ጎስቱ ነው የሚገዛን! አዲስ አበባን እንዲህ ሲያወድሞት እያየን ዝም እንል ነበር፣ ቢያንስ ቢያንስ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ የኡኡታ አናሰማም!! ኡኡታና ትሪ ማንኮኮት አደማ አይደረግም፣ ቀጥለንስ  የሦስት ቀናት የቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ አናደርግም፡፡ የአዲሰ አበባ ፋኖ ይህን አድማ ካልጠራ የኮነሬል አብይ ቅጥረኛ ላለመሆኑ በምን እናውቃለን፡፡ ‹‹ባትዋጋ እንኳ በል እንገፍ እንገፍ፣ የአባትህ ጋሻ ትኻኑ ይርገፍ!!!›› ‹‹Mass protests broke out in Addis Ababa following Friday prayers as a result of anger over mosque demolitions in the neighboring Shegger city. The demonstrations took place around mosques in the capital yesterday, May 23, 2023, including the Grand Anwar Mosque. Demonstrators called for an immediate stop to the demolitions as well as the rebuilding of the 19 mosques already razed during the last few weeks. Social media outcry has escalated due to the demolitions, with videos showing police officers in riot gear blocking angry protesters circulating widely››…………………..(2)

‹‹አዲስ አበባ ላይ ትልቅ ድህነትና ችግር ያለው ሴንተር ነው፡፡ መርካቶ፣ ፒያሳ፣ ሜክሴካ፣የሚባለው ነው፡፡ ሲኤምሲ እንደዛ አይደለም፣ ለቡ እንደዛ አይደለም፣ ዋናው ችግር እዚህ ነው፡፡ዋናውን ችግር ደፍረን ብናፈርሰው ታያላችሁ በአምስት አመት ከተማውምን እንደሚመስል፡፡››ኮነሬል አብይ አህመድ ለሜ/ጀኔራሎቹ የደሃ መሬት እየነጠቀ ይሸልማል፡፡ የአዲስ አበባን የደሃ ቤቶች እያፈረሰ ፓርክና ቤተ-መንግሥት ይገነባል፡፡ ደሃ ከቆረጠ አጥፍቶ ማጥፋት የእናንተንም ቤት ማፍረስ፣ የናንተንም ሥራ ማጥፋት የደቂቃ ሰከንድ ሥራ መሆኑን እወቁት፣ የእናንተ አይፈርስም ያላችሁ ማን ነው!!! እነእንትና!!! እነእንትና የጅብ ጥላ! ከዲያስፖራ  ዶላር ላታገኝ በመለመን  ስትጣላ እድሜህን አትግፋ!!!

የደም መሬት፡-ከደም መሬት የሚቆደሱ ጀነራል መኮንኖች አዲስ አበባን ከተማ ምርጥ አንደኛ ደረጃ ቦታዎች በገፀ-በረከትነት በኮነሬል አብይ አህመድ ተበርክቶላቸዋል፡፡ ጀነራሎቹ በታማኝነት ህዝብ በመግደል፣ ቤቶች በማፍረስና በማቃጠል፣ የህዝብን እንቢተኛነትና ህዝባዊ አመፅን በማፈን ሥርዓቱን በመጠበቃቸው የተከፈላቸው የደም ዋጋ ነው፡፡ የደም መሬቱን በሁለት መቶና ሦስት መቶ ሚሊዮን ሸጠው የደም ገንዘብ ያገኛሉ፡፡

{1} ሜ/ጀኔራል ጥሩዬ አሰፋ፣ ኮልፌ 1000ካሜ

{2} ሜ/ጀኔራል ከፍያለው ምዴ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{3} ሜ/ጀኔራል አብዱ ከድር ንፋስ ስልክ1000ካሜ

{4} ሜ/ጀኔራል ሰለሞን ቦጋለ መኮነንን ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{5}ሜ/ጀኔራል ሙላቱ ጀልዱ ዋቅጂራ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{6} ሜ/ጀኔራል አማረ ገብሩ ሀይሉ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{7} ሜ/ጀኔራል አድማሱ አለሙ ወ/ሰንበት ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{8} ሜ/ጀኔራል ሙሉአለም አድማሱ ካህሱንፋስ ስልክ1000ካሜ

{9} ሜ/ጀኔራል አዳምነህ መንግሥቴ ገብሬንፋስ ስልክ1000ካሜ

{10} ሜ/ጀኔራል ኢተፋ ራጋ ሜኮ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{11} ሜ/ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን በርሄ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{12} ሜ/ጀኔራል ታገሰ ላምባሞ ዱምቦሬ ንፋስ ስልክ 1000ካሜ

{13} ሜ/ጀኔራል ግርማ ከበበው ቱፋ ንፋስ ስልክ1000ካሜ

{14} ሜ/ጀኔራል ፍቃዱ ጸጋዬ እምሩ ቦሌ 1000ካሜ

{15} ሜ/ጀኔራልታደሰ መኩሪያ ንፋስስልክ 1000ካሜ

{16} ሜ/ጀኔራልግዛው ኡማ አብዲ ኮልፌ 1000ካሜ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189555

Thursday, March 28, 2024

https://youtu.be/wpm6w1SLB_A?si=cUTq7fZVEuP3yEjJ

መጨረሻም ፋኖ ታላቅ የምስራች ይዞ እየመጣ ነው - ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ መግለጫ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189552
ወልቃይት የማን ነው? የማይረባ ጥያቄ | ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ነሐሴ 2008

አንድ

በነገረ አስተሳሰብ ወይም በአስተሳሰብ ሕግ (ሎጂክ) ትምህርት ላይ አንድ የማስታውሰው ምሳሌ አለ፤ ‹‹ሚስትህን መደብደብ ትተሃል ወይ?›› የሚል ጥያቄ ነው፤ ጥያቄው የሚነሣው ጠያቂው አውቃለሁ ብሎ ከያዘው እውቀት ወይም እምነት ነው፤ ስለዚህም ጠያቂው የሚፈልገው ጥያቄ ለማስተላለፍና መልስ ለማግኘት አይደለም፤ ጠያቂው የሚፈልገው በጥያቄ መልክ የራሱን ‹‹እውቀት›› ወይም እምነት ለተጠያቂው ለማስተላለፍና ተጠያቂውን የጠያቂው ደቀ መዝሙር ለማድረግ ነው፡፡

ሚስትህን መደብደብ ትተሃል ወይ? መልስ የሌለው ጥያቄ ነው፤ ‹‹አዎ›› የሚል መልስ ሰውዬው ሚስቱን ሲደበድብ እንደነበረ አመነ ማለት ነው፤ ‹‹አልተውሁም›› ከአለ በራሱ ላይ መሰከረ፤ ሁለቱም መልሶች ተጠያቂውን የሚያስወነጅሉ ስለሆኑ መልስ አይደሉም፤ ከዚያም በላይ ጥያቄው ትክክል አይደለም፤ የማይረባ መጥፎ ጥያቄ ነው፡፡

‹‹ወልቃይት የማን ነው?›› የሚለው ጥያቄ ትክክል አይደለም፤ የማይረባና መጥፎ ጥያቄ ነው፤ ጠያቂው የሚፈልገው መልስ የአማራ ነው፤ የጎንደር ነው፤ የትግሬ አይደለም፤ የሚል ነው፤ ነገር የሚገባው ተጠያቂ ጥያቄውን ጠያቂው በፈልገው መልክ አይመልስለትም፤ ሊመልስለትም አይገባም፤ ወልቃይት የኢትዮጵያ ነው የሚል መልስ አይፈለግም፤ የማይፈለግበትም ምክንያት ‹‹ወልቃይት የኢትዮጵያ ነው፤›› ማለት ወልቃይትን ከጎሠኛነት አጥር ስለሚያወጣ ነው፤ የትግራይ አይደለም፤ የአማራ አይደለም፤ የኢትዮጵያ ነው፤ አሁን ትግራይና አማራ የኢትዮጵያ ናቸው፤ ይህ ከተባለ በኋላ ወልቃይት የትግራይ ነው? ወይስ የአማራ? የሚለውን ጥያቄ ማንሣት የጎሠኛነት ጥያቄ ነው፤ የኢትዮጵያዊነት ጥያቄ አይደለም፤ ጥያቄው የማይረባ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው፤ ሁለተኛው ምክንያት የጎሠኛ ጥያቄ በመሆኑ የወያኔን የጎሠኛ መመሪያ የሚያከብር መሆኑ ነው፡፡

ትልቁና መሠረታዊው ጥያቄ በአማራ ክልል ስር የነበረው ወልቃይት በወያኔ አገዛዝ ወደትግራይ ክልል መግባቱ ነው፤ እዚህ ላይ ጥያቄው የወልቃይት ወረዳ ወይም አውራጃ ነው፤ በውስጡ የሚኖሩት ሰዎች የጎሣ ዓይነት ወይም የጎሣ ስብጥር አይደለም፤ የፈለገውን ዓይነት አንድ ጎሣ ወይም የብዙ የጎሣ ስብጥር ሊኖርበት ይችላል፤ ክርክሩ መሆን ያለበት የወልቃይት አውራጃ ከጎንደር ክልል ወጥቶ ወደትግራይ የገባበት መንገድ ትክክል አይደለም፤ የአስተዳደር ለውጡ የተፈጸመው የፌዴራል መዋቅሩን ሥርዓት በጣሰ መንገድ አንዱ ክልል (ትግራይ) በሌላው ክልል ላይ የጉልበተኛነት ወረራ አካሂዷል ነው፤ ይህ ወረራ ሕጋዊ አይደለም፤ ይህ ወረራ ሊቀለበስ ይገባል፤ ዋናው መቋጠሪያ ይኸው ነው፡፡

ግን ጉዳዩን የጀመርነው ከመሀሉ ነው፤ ሲጀመር ወያኔ ከኦሮሞ ቡድኖች ውስጥ ኦነግን መረጠና አማርኛ ተናጋሪውን አለ እያለ እንደሌለ ቆጠረው፤ በዚያን ጊዜ ኦሮሚኛ ተናጋሪዎቹም ኢፈትሐዊነቱን አልተናገሩም፤ ዋና የፖሊቲካ ጉዳይ አድርገው አላነሱትም፤ ለምን? እነሱ በሎሌነት በመመረጣቸው በደስታ ተውጠው ስለነበረ ጌቶቻቸውን ለማስቀየም ፍላጎት አልነበራቸውም፤ ግን ወያኔ በእጁ ያሉትን ምርኮኞች ከአደራጀ በኋላ ኦነግ ተባረረና በኦሕዴድ ተተካ፤ የኦነግ መሪዎች አገር ውስጥ ሆነው ለመታገል የሚያስከፍለውን ዋጋ ላለመክፈል በአሜሪካና በአውሮፓ ተቀምጠው በስልክ ‹‹ትግሉን›› መምራት መረጡ፤ ወያኔ አነግን በብዙ መንገድ ተጠቅሞበታል፤ አንደኛና ዋናው አማርኛ ተናጋሪውንና ኦሮምኛ ተናጋሪውን ለመለያየትና በቅራኔ ለማጋጠም፤ ሁለተኛ የኦሮሞ መሪዎች ነን የሚሉ ሁሉ ለወያኔ ትሑት አገልጋይ ከመሆን ሌላ አማራጭ እንደሌላቸው አረጋገጠላቸው፤ ኦነግንና እስላማዊ ኦነግን አፋጅቶ በኦሕዴድ አጋዥነት ሁለቱንም ከትግል መድረኩ አስወጣቸው፡፡

አለ ተብሎ እንደሌለ የተቆጠረው አማርኛ ተናጋሪው በነታምራት ላይኔ፣ በነበረከት ስምዖን፣ በነህላዌ ዮሴፍ፣ በነተፈራ ዋልዋ፣ (ሁሉም ያለጥርጥር አማርኛ ተናጋሪዎች ናቸው፤ ነገር ግን ከየት ከየት እንደበቀሉ አጠራጣሪ ነው፤) ተወከለ፤ ከጎንደርም ይሁን ከጎጃም፣ ከወሎም ይሁን ከሸዋ የእነዚህን ሰዎች ውክልና የተቃወመ የለም፤ እንዲያውም ለአሽከርነቱ ውድድር ነበር፤ በሁለቱ ድርጅቶች -- በብአዴንና በኦሕዴድ -- አማካይነት ወያኔ ወደሰባ በመቶ የሚጠጋውን የኢትዮጵያ ሕዝብ በቁጥጥሩ ስር አደረገ፤ ይሄ ሁሉ ሲሆን በአገር ውስጥ ያሉት የአማርኛ ተናጋሪውና የኦሮምኛ ተናጋሪው ወኪሎች ነን ባዮቹ ለፍርፋሪ ሲፎካከሩና ሲነታረኩ ወያኔ የራሱን ክልል በትምህርትና በልማት ለማሳደግ እየሞከረ ነበር፡፡

ለእኔ ፍሬ ነገሩ አማርኛ ተናጋሪውም ሆነ ኦሮምኛ ተናጋሪው ሃያ አምስት ዓመታት ሙሉ እየተፎካከሩ ወያኔን ከማገልገል ሌላ መብትና ሥልጣን ፈልገው አያውቁም፤ ስለዚህም ከማይናገር ከብቱን፣ ከማይራገጥ ወተቱን እንደተባለው ወያኔም በከብቱም በወተቱም ተጠቀመበት፡፡

ሁለት

በ1996 ዓ.ም. የክህደት ቁልቁለት በሚል ርእስ ትንሽ መጽሐፍ አሳትሜ ነበር፤ በዚያ መጽሐፍ ውስጥ በገጽ 96ና 97 መሀከል ካርታዎች አሉ፤ ከነዚህ ካርታዎች አንዱ የኢጣልያ ምሥራቅ አፍሪካ (AFRICA ORIENTALE ITALIANA) 1928-1933 ዓ.ም. የሚል ነው፤ በዚያ ካርታ ላይ ፋሺስት ኢጣልያ ትግራይን በሙሉና አፋርን በሙሉ በኤርትራ ክልል ውስጥ አድርጎት ነበር፤ በደቡብም የኢጣልያን ሶማልያ ወደሰሜን ገፍቶ ኦጋዴንን በሙሉና ግማሽ ባሌን ጨምሮበት ነበር፤ ምዕራቡን ክፍል -- ወለጋን፣ ኢሉባቦርን፣ ጋሞ ጎፋን፣ ሲዳሞን በአንድ ላይ አስሮ ጋላና ሲዳማ የሚል ስያሜ ሰጥቶት ነበር፤ ሀረር ሰሜን ባሌንና አርሲን ጠቅልሎ ነበር፤ ወያኔም ከፋሺስት ኢጣልያ የወረሰውን አስተሳሰብ ይዞ የጎሣ ክልሎችን ፈጠረ፤ በዚያን ጊዜ ግማሹ እልል እያለ ግማሹ እያጉረመረመ ተቀበለ፤ በዚህም ሥርዓት አንድ ትውልድ በቀለና በጫትና በጋያ አደገ፡፡

ወያኔ የበቀለበትን ትግራይን ሲያይ አነሰችው፤ በዚያ ላይ በሰሜን በቂልነት ደም ከተቃባቸው ከኤርትራውያን ጋር በደቡብ ደግሞ የሥልጣን ችጋሩ ጠላት በአደረጋቸው ኢጣልያ ‹‹አማራ›› ብሎ በከለላቸው ሰዎች በጎንደርና በወሎ በኩል ታፍኗል፤ በዚያ ላይ በትግራይ ውስጥ ካለው የእርሻ መሬት የተሻለ በጎንደርና በወሎ አለ፤ ጉልበተኛ ሆኖ መቸገር አይበጅምና በጊዜ፣ በጠዋቱ ከጎንደርም ቀንጨብ፣ ከወሎም ቀንጨብ አደረገና አበጠ፤ ሲያብጡ ቦታ ይጠብባል፤ ስለዚህ ወደቤኒ ሻንጉልና ወደጋምቤላ በመዝለቅ ሁለት ዓላማዎችን ማሳካት ይቻላል፤ አንደኛ ትግራይ ሰፊ ይሆንና በእርሻ ልማት የሚከብርበት ተጨማሪ መሬት ያገኛል፤ ሁለተኛ ጠላት ብሎ የፈረጀውን አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ የውጭ ንክኪ እንዳይኖረው ያፍነዋል፤ ከሱዳንም ጋር ጊዜያዊ ወዳጅነትን በመሬት ይገዛል፤ የወያኔ የእውቀትና የብስለት እጥረት ከብዙ ትንሽም ትልቅም ኃይሎች ጋር ያላትማቸዋል፤ ሱዳንን በመሬት በማታለል ሱዳንን ከደቡብ ሱዳን፣ ከኤርትራ፣ ከግብጽ፣ ከሳኡዲ አረብያ፣ ከየመን፣ ከሶማልያ … መለየት የሚችሉ ይመስላቸዋል (ልክ አማርኛ ተናጋሪውንና ኦሮምኛ ተናጋሪውን እንደለዩት)፤ የተዘረዘሩት አገሮች ሁሉ በሱዳን ላይ ከወያኔ የበለጠ ጫና ማድረግ የሚችሉ ናቸው፤ አሜሪካን ለብቻው ብቻ ሳይሆን ከነዚህ አገሮች ጋር አብረን ስንገምተው የወያኔን ደካማ ሁኔታ ለመገንዘብ ቀላል ነው፤ በአካባቢያችን ከአሉት አገሮች ሁሉ ወረተኛ የውጭ አመራር ያለው ሱዳን ነው፤ ሱዳን የኤርትራን መገንጠል የደገፈው በአሜሪካ ጫና መሆኑን አንርሳ፤ ለማንኛውም አሁን በወልቃይት የተጀመረው ውጊያ ከቀጠለ የወያኔና የሱዳን የጓዳ ጨዋታ ያበቃለታል፡፡

ጉዳዩ ሰፊ ጥናት የሚያስፈልገው ነው፡፡

ሦስት

ወደየጊዜው አንገብጋቢ ጥያቄ ስንመለስ፡-- ጥያቄው በቁሙ የወልቃይት-ጸገዴ ተወላጆች እንዳቀረቡት ሲታይ የወያኔ አገዛዝ ሃያ አምስት ዓመታት የደከመበት የጎሠኛ ሥርዓት ቢያንስ በአስተሳብ ደረጃ የተሳካ መሆኑን ያረጋግጣል፤ የኢትዮጵያ ሕዝብም ከጎሠኛ አስተሳሰብ ገና እንዳልወጣ የሚያረጋግጥ ነው፤ በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ በጎሣ ሥርዓት እየገዛ በጎሣ ሥርዓት የሚሸነፍ መሆኑ በግልጽ እየታየ ነው፤ ወያኔ ይህንን አዲስ ክስተት ገና አልተገነዘበውም፡፡

ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ከመለስ ዜናዊ ጋር ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ተገናኝተን ስንከራከር አማራ የሚባል ጎሣ አሁን የለም፤ ግን አንተ ትፈጥረዋለህ ብዬው ነበር፤ ገና በሕጻንነት ነው እንጂ አሁን ተፈጥሮአል!

በደቡብ አፍሪካ ኔልሰን ማንዴላ በእስር ላይ በሚንገላታበት ጊዜ ደ ክለርክ የሚባለው የደቡብ አፍሪካ መሪ ማንዴላን ከእስር አስወጥቶ እንደአኩያው በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግረው የሁለቱ ተቃራኒ መሪዎች መተማመን የደቡብ አፍሪካን ችግር ለጊዜው ፈታው፤ ማንዴላ በክብር ሞተ፤ ደ ክለርክ በክብር ይኖራል፤ የሚያሳዝነው በወያኔ አመራር ውስጥ እንደደቡብ አፍሪካዊው ደ ክለርክ ያለ ሰው እንኳን ሊኖር ሊታለምም አይቻልም፤ እንኳን በወያኔ ውስጥ በአገሩም እንዲህ ዓይነት ሰው እንዳይኖር አረጋግጠዋል፡፡

የተጀመረውን ግብግብ ኢትዮጵያ ካላሸነፈች ማንም አያሸንፍም!

ኢትዮጵያ የድንክዬዎች አገር ሆናለችና የገጠማትን ችግር እግዚአብሔር በጥበቡ ይፍታላት!
https://amharic.zehabesha.com/archives/64101
ወልቃይት የማን ነው? የማይረባ ጥያቄ | ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ነሐሴ 2008

አንድ

በነገረ አስተሳሰብ ወይም በአስተሳሰብ ሕግ (ሎጂክ) ትምህርት ላይ አንድ የማስታውሰው ምሳሌ አለ፤ ‹‹ሚስትህን መደብደብ ትተሃል ወይ?›› የሚል ጥያቄ ነው፤ ጥያቄው የሚነሣው ጠያቂው አውቃለሁ ብሎ ከያዘው እውቀት ወይም እምነት ነው፤ ስለዚህም ጠያቂው የሚፈልገው ጥያቄ ለማስተላለፍና መልስ ለማግኘት አይደለም፤ ጠያቂው የሚፈልገው በጥያቄ መልክ የራሱን ‹‹እውቀት›› ወይም እምነት ለተጠያቂው ለማስተላለፍና ተጠያቂውን የጠያቂው ደቀ መዝሙር ለማድረግ ነው፡፡

ሚስትህን መደብደብ ትተሃል ወይ? መልስ የሌለው ጥያቄ ነው፤ ‹‹አዎ›› የሚል መልስ ሰውዬው ሚስቱን ሲደበድብ እንደነበረ አመነ ማለት ነው፤ ‹‹አልተውሁም›› ከአለ በራሱ ላይ መሰከረ፤ ሁለቱም መልሶች ተጠያቂውን የሚያስወነጅሉ ስለሆኑ መልስ አይደሉም፤ ከዚያም በላይ ጥያቄው ትክክል አይደለም፤ የማይረባ መጥፎ ጥያቄ ነው፡፡

‹‹ወልቃይት የማን ነው?›› የሚለው ጥያቄ ትክክል አይደለም፤ የማይረባና መጥፎ ጥያቄ ነው፤ ጠያቂው የሚፈልገው መልስ የአማራ ነው፤ የጎንደር ነው፤ የትግሬ አይደለም፤ የሚል ነው፤ ነገር የሚገባው ተጠያቂ ጥያቄውን ጠያቂው በፈልገው መልክ አይመልስለትም፤ ሊመልስለትም አይገባም፤ ወልቃይት የኢትዮጵያ ነው የሚል መልስ አይፈለግም፤ የማይፈለግበትም ምክንያት ‹‹ወልቃይት የኢትዮጵያ ነው፤›› ማለት ወልቃይትን ከጎሠኛነት አጥር ስለሚያወጣ ነው፤ የትግራይ አይደለም፤ የአማራ አይደለም፤ የኢትዮጵያ ነው፤ አሁን ትግራይና አማራ የኢትዮጵያ ናቸው፤ ይህ ከተባለ በኋላ ወልቃይት የትግራይ ነው? ወይስ የአማራ? የሚለውን ጥያቄ ማንሣት የጎሠኛነት ጥያቄ ነው፤ የኢትዮጵያዊነት ጥያቄ አይደለም፤ ጥያቄው የማይረባ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው፤ ሁለተኛው ምክንያት የጎሠኛ ጥያቄ በመሆኑ የወያኔን የጎሠኛ መመሪያ የሚያከብር መሆኑ ነው፡፡

ትልቁና መሠረታዊው ጥያቄ በአማራ ክልል ስር የነበረው ወልቃይት በወያኔ አገዛዝ ወደትግራይ ክልል መግባቱ ነው፤ እዚህ ላይ ጥያቄው የወልቃይት ወረዳ ወይም አውራጃ ነው፤ በውስጡ የሚኖሩት ሰዎች የጎሣ ዓይነት ወይም የጎሣ ስብጥር አይደለም፤ የፈለገውን ዓይነት አንድ ጎሣ ወይም የብዙ የጎሣ ስብጥር ሊኖርበት ይችላል፤ ክርክሩ መሆን ያለበት የወልቃይት አውራጃ ከጎንደር ክልል ወጥቶ ወደትግራይ የገባበት መንገድ ትክክል አይደለም፤ የአስተዳደር ለውጡ የተፈጸመው የፌዴራል መዋቅሩን ሥርዓት በጣሰ መንገድ አንዱ ክልል (ትግራይ) በሌላው ክልል ላይ የጉልበተኛነት ወረራ አካሂዷል ነው፤ ይህ ወረራ ሕጋዊ አይደለም፤ ይህ ወረራ ሊቀለበስ ይገባል፤ ዋናው መቋጠሪያ ይኸው ነው፡፡

ግን ጉዳዩን የጀመርነው ከመሀሉ ነው፤ ሲጀመር ወያኔ ከኦሮሞ ቡድኖች ውስጥ ኦነግን መረጠና አማርኛ ተናጋሪውን አለ እያለ እንደሌለ ቆጠረው፤ በዚያን ጊዜ ኦሮሚኛ ተናጋሪዎቹም ኢፈትሐዊነቱን አልተናገሩም፤ ዋና የፖሊቲካ ጉዳይ አድርገው አላነሱትም፤ ለምን? እነሱ በሎሌነት በመመረጣቸው በደስታ ተውጠው ስለነበረ ጌቶቻቸውን ለማስቀየም ፍላጎት አልነበራቸውም፤ ግን ወያኔ በእጁ ያሉትን ምርኮኞች ከአደራጀ በኋላ ኦነግ ተባረረና በኦሕዴድ ተተካ፤ የኦነግ መሪዎች አገር ውስጥ ሆነው ለመታገል የሚያስከፍለውን ዋጋ ላለመክፈል በአሜሪካና በአውሮፓ ተቀምጠው በስልክ ‹‹ትግሉን›› መምራት መረጡ፤ ወያኔ አነግን በብዙ መንገድ ተጠቅሞበታል፤ አንደኛና ዋናው አማርኛ ተናጋሪውንና ኦሮምኛ ተናጋሪውን ለመለያየትና በቅራኔ ለማጋጠም፤ ሁለተኛ የኦሮሞ መሪዎች ነን የሚሉ ሁሉ ለወያኔ ትሑት አገልጋይ ከመሆን ሌላ አማራጭ እንደሌላቸው አረጋገጠላቸው፤ ኦነግንና እስላማዊ ኦነግን አፋጅቶ በኦሕዴድ አጋዥነት ሁለቱንም ከትግል መድረኩ አስወጣቸው፡፡

አለ ተብሎ እንደሌለ የተቆጠረው አማርኛ ተናጋሪው በነታምራት ላይኔ፣ በነበረከት ስምዖን፣ በነህላዌ ዮሴፍ፣ በነተፈራ ዋልዋ፣ (ሁሉም ያለጥርጥር አማርኛ ተናጋሪዎች ናቸው፤ ነገር ግን ከየት ከየት እንደበቀሉ አጠራጣሪ ነው፤) ተወከለ፤ ከጎንደርም ይሁን ከጎጃም፣ ከወሎም ይሁን ከሸዋ የእነዚህን ሰዎች ውክልና የተቃወመ የለም፤ እንዲያውም ለአሽከርነቱ ውድድር ነበር፤ በሁለቱ ድርጅቶች -- በብአዴንና በኦሕዴድ -- አማካይነት ወያኔ ወደሰባ በመቶ የሚጠጋውን የኢትዮጵያ ሕዝብ በቁጥጥሩ ስር አደረገ፤ ይሄ ሁሉ ሲሆን በአገር ውስጥ ያሉት የአማርኛ ተናጋሪውና የኦሮምኛ ተናጋሪው ወኪሎች ነን ባዮቹ ለፍርፋሪ ሲፎካከሩና ሲነታረኩ ወያኔ የራሱን ክልል በትምህርትና በልማት ለማሳደግ እየሞከረ ነበር፡፡

ለእኔ ፍሬ ነገሩ አማርኛ ተናጋሪውም ሆነ ኦሮምኛ ተናጋሪው ሃያ አምስት ዓመታት ሙሉ እየተፎካከሩ ወያኔን ከማገልገል ሌላ መብትና ሥልጣን ፈልገው አያውቁም፤ ስለዚህም ከማይናገር ከብቱን፣ ከማይራገጥ ወተቱን እንደተባለው ወያኔም በከብቱም በወተቱም ተጠቀመበት፡፡

ሁለት

በ1996 ዓ.ም. የክህደት ቁልቁለት በሚል ርእስ ትንሽ መጽሐፍ አሳትሜ ነበር፤ በዚያ መጽሐፍ ውስጥ በገጽ 96ና 97 መሀከል ካርታዎች አሉ፤ ከነዚህ ካርታዎች አንዱ የኢጣልያ ምሥራቅ አፍሪካ (AFRICA ORIENTALE ITALIANA) 1928-1933 ዓ.ም. የሚል ነው፤ በዚያ ካርታ ላይ ፋሺስት ኢጣልያ ትግራይን በሙሉና አፋርን በሙሉ በኤርትራ ክልል ውስጥ አድርጎት ነበር፤ በደቡብም የኢጣልያን ሶማልያ ወደሰሜን ገፍቶ ኦጋዴንን በሙሉና ግማሽ ባሌን ጨምሮበት ነበር፤ ምዕራቡን ክፍል -- ወለጋን፣ ኢሉባቦርን፣ ጋሞ ጎፋን፣ ሲዳሞን በአንድ ላይ አስሮ ጋላና ሲዳማ የሚል ስያሜ ሰጥቶት ነበር፤ ሀረር ሰሜን ባሌንና አርሲን ጠቅልሎ ነበር፤ ወያኔም ከፋሺስት ኢጣልያ የወረሰውን አስተሳሰብ ይዞ የጎሣ ክልሎችን ፈጠረ፤ በዚያን ጊዜ ግማሹ እልል እያለ ግማሹ እያጉረመረመ ተቀበለ፤ በዚህም ሥርዓት አንድ ትውልድ በቀለና በጫትና በጋያ አደገ፡፡

ወያኔ የበቀለበትን ትግራይን ሲያይ አነሰችው፤ በዚያ ላይ በሰሜን በቂልነት ደም ከተቃባቸው ከኤርትራውያን ጋር በደቡብ ደግሞ የሥልጣን ችጋሩ ጠላት በአደረጋቸው ኢጣልያ ‹‹አማራ›› ብሎ በከለላቸው ሰዎች በጎንደርና በወሎ በኩል ታፍኗል፤ በዚያ ላይ በትግራይ ውስጥ ካለው የእርሻ መሬት የተሻለ በጎንደርና በወሎ አለ፤ ጉልበተኛ ሆኖ መቸገር አይበጅምና በጊዜ፣ በጠዋቱ ከጎንደርም ቀንጨብ፣ ከወሎም ቀንጨብ አደረገና አበጠ፤ ሲያብጡ ቦታ ይጠብባል፤ ስለዚህ ወደቤኒ ሻንጉልና ወደጋምቤላ በመዝለቅ ሁለት ዓላማዎችን ማሳካት ይቻላል፤ አንደኛ ትግራይ ሰፊ ይሆንና በእርሻ ልማት የሚከብርበት ተጨማሪ መሬት ያገኛል፤ ሁለተኛ ጠላት ብሎ የፈረጀውን አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ የውጭ ንክኪ እንዳይኖረው ያፍነዋል፤ ከሱዳንም ጋር ጊዜያዊ ወዳጅነትን በመሬት ይገዛል፤ የወያኔ የእውቀትና የብስለት እጥረት ከብዙ ትንሽም ትልቅም ኃይሎች ጋር ያላትማቸዋል፤ ሱዳንን በመሬት በማታለል ሱዳንን ከደቡብ ሱዳን፣ ከኤርትራ፣ ከግብጽ፣ ከሳኡዲ አረብያ፣ ከየመን፣ ከሶማልያ … መለየት የሚችሉ ይመስላቸዋል (ልክ አማርኛ ተናጋሪውንና ኦሮምኛ ተናጋሪውን እንደለዩት)፤ የተዘረዘሩት አገሮች ሁሉ በሱዳን ላይ ከወያኔ የበለጠ ጫና ማድረግ የሚችሉ ናቸው፤ አሜሪካን ለብቻው ብቻ ሳይሆን ከነዚህ አገሮች ጋር አብረን ስንገምተው የወያኔን ደካማ ሁኔታ ለመገንዘብ ቀላል ነው፤ በአካባቢያችን ከአሉት አገሮች ሁሉ ወረተኛ የውጭ አመራር ያለው ሱዳን ነው፤ ሱዳን የኤርትራን መገንጠል የደገፈው በአሜሪካ ጫና መሆኑን አንርሳ፤ ለማንኛውም አሁን በወልቃይት የተጀመረው ውጊያ ከቀጠለ የወያኔና የሱዳን የጓዳ ጨዋታ ያበቃለታል፡፡

ጉዳዩ ሰፊ ጥናት የሚያስፈልገው ነው፡፡

ሦስት

ወደየጊዜው አንገብጋቢ ጥያቄ ስንመለስ፡-- ጥያቄው በቁሙ የወልቃይት-ጸገዴ ተወላጆች እንዳቀረቡት ሲታይ የወያኔ አገዛዝ ሃያ አምስት ዓመታት የደከመበት የጎሠኛ ሥርዓት ቢያንስ በአስተሳብ ደረጃ የተሳካ መሆኑን ያረጋግጣል፤ የኢትዮጵያ ሕዝብም ከጎሠኛ አስተሳሰብ ገና እንዳልወጣ የሚያረጋግጥ ነው፤ በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ በጎሣ ሥርዓት እየገዛ በጎሣ ሥርዓት የሚሸነፍ መሆኑ በግልጽ እየታየ ነው፤ ወያኔ ይህንን አዲስ ክስተት ገና አልተገነዘበውም፡፡

ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ከመለስ ዜናዊ ጋር ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ተገናኝተን ስንከራከር አማራ የሚባል ጎሣ አሁን የለም፤ ግን አንተ ትፈጥረዋለህ ብዬው ነበር፤ ገና በሕጻንነት ነው እንጂ አሁን ተፈጥሮአል!

በደቡብ አፍሪካ ኔልሰን ማንዴላ በእስር ላይ በሚንገላታበት ጊዜ ደ ክለርክ የሚባለው የደቡብ አፍሪካ መሪ ማንዴላን ከእስር አስወጥቶ እንደአኩያው በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግረው የሁለቱ ተቃራኒ መሪዎች መተማመን የደቡብ አፍሪካን ችግር ለጊዜው ፈታው፤ ማንዴላ በክብር ሞተ፤ ደ ክለርክ በክብር ይኖራል፤ የሚያሳዝነው በወያኔ አመራር ውስጥ እንደደቡብ አፍሪካዊው ደ ክለርክ ያለ ሰው እንኳን ሊኖር ሊታለምም አይቻልም፤ እንኳን በወያኔ ውስጥ በአገሩም እንዲህ ዓይነት ሰው እንዳይኖር አረጋግጠዋል፡፡

የተጀመረውን ግብግብ ኢትዮጵያ ካላሸነፈች ማንም አያሸንፍም!

ኢትዮጵያ የድንክዬዎች አገር ሆናለችና የገጠማትን ችግር እግዚአብሔር በጥበቡ ይፍታላት!
https://amharic.zehabesha.com/archives/64101

Wednesday, March 27, 2024

https://youtu.be/GfyGW0iy_Dc?si=yiLY3NVIz2hWjR60

የአማራ ፋኖ በጎጃም ቃል አቀባይ ፋኖ ማርሸት ለገበሬዎች ማዳበሪያ ሲያካፋፍል ያስተላለፈው ጥብቅ መልዕክት
https://amharic.zehabesha.com/archives/189543
https://youtu.be/B62aLl_ilWM?si=vGcJ-hNGHvelNqsB

ደብረብርሃን ውጊያ ፋኖ ዘልቆ ገባ | ክርስቲያን ታደለ ተመረዘ | ፋኖ ወደ አዲስ አበባ ገሰገሰ ጎጄ አናወጠው
https://amharic.zehabesha.com/archives/189520

Tuesday, March 26, 2024

https://youtu.be/B62aLl_ilWM?si=vGcJ-hNGHvelNqsB

ደብረብርሃን ውጊያ ፋኖ ዘልቆ ገባ | ክርስቲያን ታደለ ተመረዘ | ፋኖ ወደ አዲስ አበባ ገሰገሰ ጎጄ አናወጠው
https://amharic.zehabesha.com/archives/189520
ለአቶ ኤፍሬም ማዴቦ የዛሬዋ ኢትዮጵያ ዋናው ችግር ምንድነው? ብሎ ለጠየቀውና “መልስም ለመስጠት ለመኮረው” የተሰጠ ትችታዊና ሳይንሳዊ ሀተታ መልስ!! ቁጥር ፪
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ትልቁ ችግር ሳይንሳዊ ዕውቀት ጋር አለመተዋወቅ፣ የንቃተ-ህሊና አለመኖር ወይም አለመዳበር፣ ጥያቄ ለመጠየቅ ያለመቻል ችግር ነው! ለአቶ ኤፍሬም  ማዴቦ የዛሬዋ ኢትዮጵያ ዋናው ችግር ምንድነው? ብሎ ለጠየቀውና “መልስም ለመስጠት ለመኮረው” የተሰጠ ትችታዊና ሳይንሳዊ ሀተታ መልስ!! ቁጥር ፪     

      Sometime people don`t want to hear the truth because they don`t want their illusion       

      destroyed. (Friedrich Nietzsche)

ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)

         መጋቢት 17፣ 2016(March 26,  2024)

 

መግቢያ

ኤፍሬም ማዴቦ “የዛሬዋ ኢትዮጵያ ዋናው ችግር ምንድነው? ብሎ ላቀረበው ጥያቄና መልስም ለመስጠት ለሞከረው፣ የሱን ጽሁፍ ተመርኩዤ ደረጃ በደረጃ ሰፋ ያለ ሂሳዊ ሀተታ ሰጥቼበታለሁ። ኤፍሬም ማዴቦም ሆነ አንዳንድ ጽሁፌን ያነበቡ ግለሰቦች የጽሁፌን መሰረተ-ሃሳብና የተመረኮዝኩበትን ሳይንሳዊ መሰረት ሳይረዱ ከጽሁፌ ጋር የማይጣጣም ወይም ጽሁፉን የማይመለከት ትችት ለማቅረብ ሞክረዋል።

በመጀመሪያ ደረጃ እንዲታወቅልኝ የምፈልገው በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታና ከዓለም ፖለቲካ ጋር የተያያዙ ሳይንሳዊ ሀተታዎችን በእንግሊዘኛ፣ በጀርመንኛም ሆነ በአማርኛ ቋንቋዎች በመጻፍ ለንባብ አቅርቤአለሁ። እነዚህም ጽሁፎች ደረጃ በደረጃ በድረ-ገጼ ላይ ተቀምጠው ይገኛሉ። የተለያዩ ጽሁፎቼን ያነበበ ሰው ሊገነዘበው የሚችለው  ነገር አንዳችም ቦታ ላይ  ከተጨባጭ ሁኔታዎችና ከሰዎች ድርጊቶች፣ በተለይም የፖለቲካ ተዋናይ ነን ከሚሉትና፣ በተለይም ደግሞ በፖሊሲ ደረጃ ረቅቀው ተግባራዊ ከሁኑ ነገሮችና አሉታዊ ውጤታቸው ውጭ የጻፍኩበት ጊዜ የለም። ጽሁፎቼ ከኢትዮጵያ ውጭ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ውስጥም በመነበብ የድጋፍ መልዕክቶችና ያልገባቸው ነገሮች ካሉ በጥያቄ መልክም ደርሰውኛል። ኤፍሬም ማዴቦ ያቀረበውን ”የዛሬዋ ኢትዮጵያ ዋናው ችግር ምንድነው?” የሚለውን ጽሁፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው ያነበቡ ሰዎች ከጽሁፉ ብዙ ቁም ነገሮችን እንደተማሩ በኋትስ አፕ መልዕክት አስተላልፈውልኛል። እስካሁን እንድተከታተልኩት ከሆነ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ዘንድ አንዳንድ የማቀርባቸውን ክሪቲካል የሆኑ ጽሁፎቼን አስመልክቶ በሚገባ የማንበብና የመረዳት ችግር ያለባቸው ይመስለኛል። በአንዳንዶች ዘንድ  የሚታየው ይህ ዐይነቱ ችግር ደግሞ በተለያዩ መንገዶች ዕውቀት በተስፋፋበትና፣ የተለያዩ የሳይንስና የፍልስፍና መጽሀፎች እንደልብ በሚገኝባቸው በአሁኑ በ21ኛው ክፍለ-ዘመን ነው። መጽሀፍ ለመግዛት ቢከብድም እንኳ ካለምንም ወጭ ከመጻህፍት ቤቶች መጻፎችን በመዋስ በጣም ጠቃሚና ለጭንቅላት ገንቢ የሆኑ ዕውቀቶችን መቅሰም ይቻላል። በአሁኑ በኢንተርኔት ዓለምም አንዳንድ መጽሀፎችን ገንዘብ ሳይከፍሉ ማውረድና ማንበብ ይቻላል። ባጭሩ አንድ ሰው ከተለያዩ ዕውቀቶች ጋር የሚተዋወቅ ከሆነ በቀላሉ ግራ ሊጋባ አይችልም። እንዲያም ሲል ሳይንስ እያልክ ግራ አታጋባን ብሎ ሊጽፍ አይችልም። በሌላ ወገን ግን ማንኛውም ጽሁፍ ትችታዊ በሆነ መልክ መገምገምና ተገቢው ሂስ መቅረብ አለበት። ተተቸሁ ብሎ ቡራ ከረዩ የሚል ሰው ከሌሎችም ለመማር የማይፈልግ ሰው ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ነገር አውቃለሁ የሚል ነው። እንደሚታወቀው ማንኛውም ነገር በሂደት ላይ ያለ ነው። በየጊዜውም አዳዲስ ግኙቶችና ዕውቀቶች ይፈልቃሉ። በአንድ ዘመን ተቀባይነት ያላቸው ተሽረው በአዲስ ዕውቀቶች ይተካሉ። ይሁንና ግን ዘመን የማይሽራቸው ዘለዓለማዊ ዕውቀቶች አሉ። እነዚህም በሶክራተስ፣ በፕላቶንና፣ በአጠቃላይ ሲታይ በግሪክ ፈላስፎች የተፈጠሩ ፍልስፍናዎች፣ የተፈጥሮ ሳይንስና የማቲማቲክስ ዕውቀቶች ናቸው። እነዚህ ዕውቀቶች ደግሞ የኋላ ኋላ ላይ ከ15ኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ በአንዳንድ የአውሮፓ ፈላስፋዎች በመዳበርና ጥልቀትን በማግኘት ለተፈጥሮ ሳይንስ መሰረት ሊጥሉ ችለዋል። በአጭሩ ዘመን የማይሽራቸው ለሰው ልጅ የማቴሪያልም ሆነ የመንፈስ ዕድገት በጣም ጠቃሚ የሆኑ  ዕውቀቶች አሉ ማለት ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ የሚመለከተው ሰው ኤፍሬም ማዴቦ የጽሁፉን ይዘት በሚገባ ሳይረዳ  በቅድሚያ  ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ መታገል ያስፈልጋል ብዬ እንደጻፍኩ አድርጎ  በማስመሰል የጽሁፉን አቀራረብ፣ የቲዎሪ መሰረትና የሀተታ ዘዴውን ሳይረዳ  የተሳሳተ ግምገማና ትችት ለመስጠት ሞክሯል። አንድነት ሰመረ የሚባል ግለሰብም እንደዚሁ የጽሁፌንና የአሰራር ስልትና የአተናተን ዘዴዬንና ሳይንሳዊ መሰረቱን ሳይረዳ ልክ ኤፍሬም ማዴቦ የጻፈውን በማስተጋባት ለመተቸት ሞክሯል። አልፎም በመሄድ “የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ ስለማትረዳና የግራ አመለካከት ስላለህ ነው እንደዚህ ዐይነት ጽሁፍ የጻፍከው” በማለት ተራ ውንጀላ መሰል ነገር ለመሰንዘር ሞክሯል። ይሁንና ግን ራሱ የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታና ታሪካዊ ሂደቱን በምን መልክ እንደሚረዳ ለማስረዳት አልሞከረም። ይህ ብቻ ሳይሆን “የግራ አስተሳሰብ ስላለህ ነው እንደዚህ ብለህ የምትጽፈው ሲል” የግራ አስተሳሰብ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ግልጽ ለማድረግ አልሞከረም። ይሁንና አንድነት ሰመረ ጽሁፌን በደንብ አንብቦ ከሆነ በአብዮቱ ወቅት የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታና የህብረተሰብ አወቃቀር፣ እንዲሁም በጊዜው  ተፍ ተፍ በማለት አብዮቱን እናራምዳለን ወይም ለውጥ መምጣት አለበት ብለው ይታገሉ የነበሩ የተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎች ሁኔታውን በቲዎሪም ሆነ በኢምፔሪካል ደረጃ ስላላጠኑ ብዙ ስህተቶች ሊሰሩ እንደቻሉ ለማብራራት ሞክሬአለሁ። ይህ ብቻ ሳይሆን የራስን ኢጎ በማስቀደም የተወሰዱ አመጻዊ እርምጃዎች በማንኛውም የማርክሲስት መጽሀፎች ውስጥ እንዳልተጻፉና፣ ይህም አመጻዊ ድርጊት ሊፈጸም የቻለው ከጭንቅላት ብስለት ጉድለትና የፖለቲካን ትርጉም ለመረዳት ካለመቻል የተነሳ እንደሆነ ለማተት ሞክሬአለሁ። ወደ መሬት ለአራሹና የቤቶችን ወረሳ ጋ ስንመጣ በሚገባ ሳይጠኑ ተግባራዊ እንዲሆኑ በመደረጋቸው በተለይም ጥሮ ግሮ ሀብት ያፈራውን ዝም ብሎ ፊዩዳል እያሉ በመወንጀል ህብረተሰብአዊ መመሰቃቀል ሊፈጠር እንደቻለ ለማሳየት ሞክሬአለሁ። እንደነዚህ ዐይነት ስህተቶችም ሊሰሩ የቻሉት የተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎችና ደርግም ራሱ ከተለያዩ ዕውቀቶች ጋር ለመተዋወቅ ባለመቻላቸው ብቻ ሳይሆን በንፅፅር ጥናት(Comparative Studies) በቻይናም ሆነ በሶቭየት ህብረት በአብዮት ስም በጅምላ ተግባራዊ እንዲሆኑ የተደረጉ ዕርምጃዎች በሙሉ ምን ዐይነት ጉዳት  እንዳስከተሉ ጠጋ ብሎ ለማጥናት ባለመቻሉ እነዚህን የመሳሰሉ ስህተቶች ሊሰሩ እንደቻሉ ግልጽ ነው። ሌላው አብዮተኛ ነን በሚሉ ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች የሚሰራው ትልቁ ወንጀል የታሪክን ሂደትና ውጣ ውረድነትን፣ በተለይም ደግሞ የንቃተ-ህሊናን ጉዳይ ግንዛቤ ውስጥ ሳያስገቡ የሚወሰዱ እርምጃዎችና የሚስተጋቡ መፈክሮች ከትውልድ ወደ ትውልድ የተላለፉ ጥሩ እሴቶችንና ባህሎችን እንደሚያናጉና ህብረተሰብአዊ  መመሰቃቀልን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ አለመረዳት ነው። ከዚህ ሁሉ ውስጥ አደገኛውና ለምሁራዊ እንቅስቃሴም እንቅፋት የሚሆነው በአገራችን ምድር የተሰሩትን ስህተቶችና ወንጀሎች በሙሉ በሶሻሊዝም ወይም በግራ አስተሳሰብ ላይ ማላከኩ ነው። በህብረተሰብ ግንባታ ሂደት ውስጥ ወርቃማ መንገድ የለም። የሰው የማሰብ ኃይል እስኪዳብርና ረጋ እስኪል ድረስ ብዙ ዓመታትን ስለሚፈጅ እንደነዚህ ዐይነት ስህተቶች መሰራታቸው የታሪክ ግዴታ ነው።

ለምሳሌ የካፒታሊዝምን ዕድገት ስንመለትና በሶቭየት ህብረትም ሆነ በቻይና ውስጥ በአብዮቱ ዘመን ከተሰሩት ስህተቶች ወይም ወንጀሎች ጋር ስናወዳድረው በካፒታሊዝም የዕድገት የታሪክ ሂደት ውስጥ የተሰሩት ወንጀሎች በብዙ እጅ እንደሚበልጡ መታወቅ አለበት። በምዕራብ አውሮፓ አገሮች ውስጥ ብዙ ጦርነቶች ተካሂደዋል። ገበሬው በከፍተኛ ደረጃ ይበዘበዝና እንደ ግል ሀብትም ይቆጠር ነበር። ከባላባቱ ፈቃድ የሚያርስበትን መሬትና የሚኖርበትን ጓሮ ጥሎ የመሄድ መብት አልነበረውም። ገበሬው ለማግባት ከፈለገ ባላባቱን ፈቃድ መጠየቅ ነበረበት። ይህንን ዐይነቱን ጭቆናዊ ድርጊት በመቃውም በፊዩዳሉና በገበሬው መሀከል ብዙ ጦርነቶች ተካሂደዋል። በማዕከለኛው ክፍለ-ዘመን የሰፈነውን ጭቆናዊ አገዛዝና ጭፍን የሆነውን የካቶሊክ ርዕዮተ-ዓለም የተቃወሙና ትክክለኛውን ሳይንሳዊ መንገድ ለማሳየት የሞከሩና ያረጋገጡም ከነነፍሳቸው እንዳሉ ተቃጥለዋል። ብዙ ምሁራንም አገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ ለመደርግ በቅተዋል። ካፒታሊዝምም በአሸናፊነት ከወጣ በኋላ የባርያ ንግድና ቅኝ-ግዛት ተስፋፍተዋል። በእነዚህ መሰረቶች ላይ በመመርኮዝ ነው ካፒታሊዝም ከፍተኛ የሀብት ክምችት ማዳበር የቻለው። አሜሪካ የተቆረቆረቺው 17 ሚሊዮን የሚያህሉ ኢንዲያኖችን በማረድና ታሪካቸውንና ስልጣኔያቸውን በማውደም ነው። የኋላም ኋላም የአንደኛውና የሁለተኛው ዓለም ጦርነቶች ሰለጠንኩ በሚለው በካፒታሊስቱ ዓለም የተቀሰቀሱና ለብዙ ሚሊዮኖች ሰዎች ህይወት መቀሰፍ ምክንያት የሆኑ ናቸው። ባጭሩ ለማለት የምፈልገው የግራ አመለካከትን ወይም የሶሻሊስት አስተሳሰብን የሚቃወም ወይም ይህን አስተሳሰብ ያራምዳሉ የሚላቸውን የሚወነጅል ሰው ወይም ቡድን በካፒታሊዝም የኢኮኖሚ ግንባታ ታሪክ ውስጥ የተፈጸሙትን ወንጀሎች ሁሉ ማወቅም አለበት። ይህ ብቻ ሳይሆን መጻፍና ማብራራትም አለበት።  በሌላ ወገን ግን አንድነት ሰመረ ያልተረዳው ነገር እሱ እኔን “የግራ አመለካከት ያለህ ነው” ብሎ ሲወነጅለኝ ራሱ የቀኝ ወይም ፋሺሽታዊ አመለካከት ያለው ለመሆኑ ያለመረዳቱ ነው። በመሰረቱ በሳይንስ ዓለም ውስጥ የግራና የቀኝ አስተሳሰብ የሚል አቀራረብ የለም። ሳይንስ ሳይንስ ስለሆነ ማንኛውም የተፈጥሮንም ሆነ የህብረተሰብን አወቃቀር በሚመለከት አንድ ሰው ጽሁፎችን መጻፍ ያለበት ሳይንሳዊ መሰረትን ምርኩዝ በማድረግ ብቻ ነው። ይህም ማለት የህብረተሰብን አወቃቀር ሁለንተናዊ በሆነ መልክ ከቲዎሪም ሆነ ከኢምፔሪካል አንፃር በመመርመር ብቻ ነው።

ይሁንና በህብረተሰብ የግንባታ ታሪክ ውስጥ በአገሮች ውስጥ የፖለቲካ መዛባት፣ እንዲያም ሲል የጭቆናና የሀብት ክፍፍልና የድህነት ጥያቄዎች፣ ማለትም የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጥያቄዎች አፍጠው አግጠው የነበሩ ጉዳዮች ስለሆኑና፣ በተለይም ስልጣንን የጨበጡና ተጠቃሚ ኃይሎች ሀብትን በተስተካከለ መልክ ለማከፋል ስለማይፈልጉና የማህበራዊ ችግሮችም እየጎሉ ስለመጡ ይህ ዐይነቱ ሁኔታ ወደ ህብረተሰብአዊ ግጭት እንዳይሸጋገር የግዴታ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ፍትሃዊነት መስፈን እንዳለበት አንዳንድ የተገለጸላቸው ምሁራን በተለይም ተጨቆነ፣ ወይም ተበደለ ከሚባለው የህብረተሰብ ክፍል ጎን በመቆም ለፍትሃዊነት ታግለዋል። አንዳንዶችም ቀደም ብለው በመሄድና ሳይንሳዊ ሀተታ በመሰጠት ለመሰረታዊ ለውጥ ታግለዋል። እነዚህ ዐይነቱ የተገለጸላቸው ምሁራን ለመሰረታዊ ለውጥ ሲታገሉ በ19ኛው ክፍለ-ዘመንና በ20ኛው ክፍለ-ዘመን መጀመሪያ ላይ  የነበረውን የድህነት መስፋፋት፣ የከተማዎች መቆሸሽና፣ በተለይም በየፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞችን የስራ ሁኔታና በሰውነታቸው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ በሚገባ ከተመለከቱና፣ የፋብሪካም ስራ በዚህ መልክ መዋቀር የለብትም ብለው ሰፋ ያለ ሀተታ መስጠት ከጀመሩ በኋላ ነው። በተለይም የኢንዱስትሪ አብዮት ሲካሄድ ተፈጥሮንና የሰውን ልጅ በከፍተኝ ደረጃ የሚጎዱ ነገሮች ስለተከሰቱና ህብረተሰቡም በከፍተኛ ደረጃ መመሰቃቀል ስለጀመረ የግራ ወይም የማርክሲዝም አስተሳሰብ ከመስፋፋቱ በፊት የሰብአዊነት ባህርይ ያላቸውና ጠለቅ ብለው የሚያስቡ ምሁራን በአንድ አገር ውስጥ ለውጥ በዚህ መልክ መካሄድ የለበትም በማለት ይታገሉ ነበር። ይህም የሚያመለክተው እንደኛ አገር ሳይሆን በአውሮፓ የምሁራን እንቅስቃሴ ታሪክ ውስጥ የነገሮችን ሂደት ትችታዊ በሆነ መልክ የመመልከትና ሀተታ የመስጠት ልምድ ስላለ  እንደኛ አገር ዝም ብሎ የሚታለፍ ነገር የለም።  አብዛኛዎችም ሀተታዎች በአቦሰጡኝ ሳይሆን የሚጻፉት በስልትና ሳይንሳዊ መሰረተ-ሃሳብን በማስደገፍ ብቻ ነው። በጭፍን መጓዝ የተለመደ ነገር አይደለም ማለት ነው። በሌላ ወገን ያለው ሁኔታ መለወጥ ወይም መሻሻል የለበትም ብለው የሚታገሉና ሳይሰሩና ሳይንቀሳቀሱ ሌላው በሰራው ተንደላቀው ለመኖር የሚፈልጉ ሰዎች ነበሩ። እነዚህም ቀኝ የሚባል ስም ተስጥቶአቸዋል። አንዳንዶችም ከዚህ ገፍተው በመሄድ ወዝአደሩንና መሪዎችን፣ ወይም የእሱን ጥቅም ያራምዳሉ የሚባሉ ምሁራንን እንደዋና ጠላት በማየት ያሳድዱና ይገድሉ እንደነበረ ይታወቃል። እነዚህ ኃይሎች የኋላ ኋላ አደገኛ አዝማሚያ በመውሰድ ከሌሎች ሁኔታዎች ጋር በመዳበል ለፋሺዝም እንቅስቃሴ መነሳት እንደዋና ምክንያት ለመሆን በቅተዋል።

ከዚህ አጭር ሀተታ ስንነሳ የህዝብ ኑሮ መሻሻል አለበት፣ የኢኮኖሚው እንስቃሴና ዕድገት ሰፋና በጠነከረ መሰረት ላይ መገንባት አለበት ብሎ መታገል የግራ አመለካከት ተብሎ ሊወነጀል የሚገባው ጉዳይ አይደለም። ለውጥ ወይም መሻሻል አያስፈልገንም የሚል ሰው ካለ የግዴታ እዚህ አገር የቀኝ ወይም የፋሺሽት ኃይሎች ከብዙ አስርት ዓመታት ጀምሮ እንደሚታገሉት የራስን አቋም ግልጽ በማድረግ መታገል የሚያስፈልግ ይመስለኛል። ካለበለዚያ የሰውን አስተሳሰብ የግራ አስተሳሰብ እያሉ ማስፈራራት ኃይልን መበታተንና ብዙ ነገሮች ተድበስብሰው እንዲቀሩ ማድረግ ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን በምንም ዐይነት ለውጥ አያስፈልግም ማለት ነው። ስለሆነም የእኔ አቀራረብ የአገራችንን ሁኔታ በሚገባ ሳይንሳዊና ፍልስፍናዊ በሆነ መልክ መነበብና መጠናት ስላልተቻለና ልምድም ስለሌለን ነው እንደዚህ ዐይነቱ መወናበድና ዕልቂት ለመድረስ የቻለው ስል  ትግላችን በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ ብቻ ያትኩር ማለቴ ሳይሆን በጭንቅላት ዙሪያና መንፈስን በማጎልበስ መሰራት የነበረባቸው ነገሮች ስላልተሰሩ አብዮተኛ ነኝ ይል የነበረው ታጋይና መሪዎቻቸው ከመደማመጥ ይልቅ እንደ ጠላት በመተያየት ወደ መሳሪያ ትግል አመሩ ለማለት ፈልጌ ነው። የመሳሪያን ትግል የሚያስቀድምና ወደ አመጽም የሚያደላ ግለሰብም ሆነ ቡድን ጭንቅላቱ በሚገባ ያልተኮተኮተ ስለሆነ በመሰረቱ ሰፋ ያለና ለጭንቅላት መዳበር፣ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የሚያመቸውን በሁሉም መልክ የሚገለጸውን ምሁራዊ እንቅስቃሴ እንዲዳፈን ያደርጋል። በተግባርም ያየነው ይህንን ሀቅ ነው። በትግራይ ክልልና በኤርትራ ውስጥ ያሉት ሁኔታዎች ይህንን ነው የሚያረጋግጡት። በአገራችንም ምድር የሚታየው ሁኔታ ከምሁራዊ እንቅስቃሴ የራቀና በአመጽ ላይ የተመሰረተ አገዛዝ ነው። ፖለቲካን ወደ ማወናበድ፣ ወደ ተራ ተንኮልና ወደ ሽብርተኝነት የለወጠ አገዛዝ ካለፉት ስድስት ዓመታት ጀምሮ በአገራችን ምድር የፖለቲካውን መድረክ በመቆጣጠርና የመጨቆኛ መሳሪያውን ተገን በማድረግ አገራችንን በሁሉም መልክ በማዘበራረቅ ለዲሞክራሲና ለነፃነት የሚደረገውን ትግል ፈሩን እንዲስት አድርጎታል።

ኤፍሬም ማዴቦ የኢኮኖሚ ችግር አለ፣ ደርግም የተከተለው የማይገባውን የሶሻሊስት ኢኮኖሚ ፖሊሲ ነው ሲል፣ ይህ ትክክል አለመሆኑና ደርግ ስልጣን ላይ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን የአገራችንን የኢኮኖሚና የማህበራዊ ሁኔታ በማሳየት፣ ከአፄ ኃይለስላሴ አገዛዝ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በተሳሳተ መሰረት ላይ ለመመርኮዝ በመቻሉ ይህ ሁኔታ ለኢኮኖሚ ዝቅጠትና ለማህበራዊ ሁኔታ መዳከም እንደዳረገን ለማሳየት ነው የሞከርኩት። አንድነት አስመረ ጽሁፌን መስመር በመስመር በሚገባ ቢያነብ ኖሮና ቀድም ብዬ ካወጣኋቸው አያሌ የኢኮኖሚ ጽሁፎቼ ጋር ቢያወዳድር ኖሮ ተራና ኢ-ሳይንሳዊ የሆነ ውንጀላ ውስጥ ባልገባ ነበር። የኤፍሬም ማዴቦንም ጽሁፍ በሚገባ ካነበብኩ በኋላ ነው መሰረታዊ ትችት ለመስጥት የሞከርኩት እንጂ ሙሉ የምትባል ሌላዋ ተቺ እንደምትለው ግራ ለማጋባት የጻፍኩት ነገር አይደለም። ሁልግዜ ግራ የሚጋባ ሰው መሰረታዊ ዕውቀት የሌለውና መጽሀፎችንም የማንበብ ልምድ የሌለው  ሰው ብቻ ነው። ይህንን ካልኩኝ በኋላ ኤፍሬም ማዴቦ ባነሳው ጥያቄና በእኔ ግምት ግልጽ ያላደረጓቸው ነገሮች አሉ በምላቸው ነገሮች ላይ አንዳንድ ማብራሪያዎችን እንደገና ለመስጠት እሞክራለሁ። እንደገና ስል ቀደም ብዬ ባወጣኋቸው አንዳንድ ጽሁፎቼ ላይ ብዙ ነገሮችን ለማብራራት የሞከርኩ ስለነበር በዚኸኛው ጽሁፌ ላይ እንደገና ለመመለስ ስላልፈለጉ ዝምብዬ ስላለፍኩ አንባብያን ግራ ተጋብተው ይሆናል በሚል አስተባብ ብቻ  ነው።

 

እረ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ዕውቀት ሲባል ምን ማለት ነው?

“የዛሬዋ ኢትዮጵያ ዋናው ችግር ከሳንይሳዊ ዕውቀት ጋር አለመተዋወቅ ነው” ስል በመጀመሪያ ደረጃ ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ መታገል ማለቴ ሳይሆን፣ ተፈጥሮንም ሆነ የአንድን ህብረተሰብ አወቃቀር ጠጋ ብሎ በማየት(Observe) ከላይ ከሚታዩት ነገሮች በማለፍ ተፈጥሮንንም ሆነ ህብረተሰብን ምን ምን ነገሮች እንደሚያያዛቸውና፣ እንዴትስ አንደኛው ነገር በሌላኛው ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ለመረዳት መሞከር ማለት ነው። የተፈጥሮን ነገር ትተን ወደ ህብረተሰብ ጋ ስንመጣ፣ ከመንግስት አወቃቀር አንስቶ ሰለፖለቲካ አወቃቀርና፣ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሁኔታዎች ያሉትን ነገሮች ደረጃ በደረጃ ማጥናት ያስፈልጋል። የእነዚህ ነገሮች ደግሞ በስርዓትና በጥናት ወይም ደግሞ ያለስርዓትና ካለጥናት መዋቀር በጠቅላላው ህብረተሰብ ላይ ሊኖረው የሚችለውን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ እንድንገነዘበው ይረዳናል። ለዚህ ደግሞ ሳይቻኮሉ ጊዜ በመውሰድ ጥናትና ምርምር በማድረግ ብቻ ነው መገንዘብ የሚቻለው። በጥናትና በምርምር መልክ የሚታገዝ ግምገማ በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ለዕድገት፣ ለስልጣኔ፣ ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ ምጥቀት እንቅፋት የሆኑ ነገሮችን እንድናውቅና ቀስ በቀስም ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ እርምጃዎችን ደረጃ በደረጃ እንዲወሰዱ ግፊት ለማድረግ ያስችላል። ይህ ብቻ ሳይሆን በጥናትና በምርምር ላይ የሚደገፍ ህብረተሰብአዊ ሀተታ ለተከታታዩ ትውልድም እንደመነሻ በመውሰድ በዚያው እንዲቀጥል ይገፋበታል፤ የማሻሽልና የማስፋፋት ዕድልም ያገኛል።

የአንድ ህብረተሰብ ዕድገት ስልጣንን በተቆናጠጡ ወይም በመንግስት ብቻ የሚሳበብ አይደለም። አንድን ህብረተሰብ የሚያያዙ ልዩ ልዩ ባህሎችና እሴቶች፣ እንዲሁም የፈጠራ ስራዎች በሙሉ ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በግለሰቦች ወይም በቡድን የሚፈጠሩና የሚተገበሩ ናቸው። የሃይማኖትን ጉዳይ ወደ ጎን በመተው ለምሳሌ የእርሻ ስራንና በኢትዮጵያ ምድር የተገኙትን ሰብሎችና መራባት ስንመለከት ገበሬው በማየት፣ በሙከራና በልምድ ያስፋፏቸው ናቸው። ለምሳሌ ጤፍ በየትኛው ክፍለ-ዘመን እንደተገኘና ገበሬውም ለምን ጤፍን እንደ እህል በመቁጠር በመዝራትና ለምግብ እንዲውል ማድረጉ የሚታወቅ ነገር የለም። ይሁንና ይህ ዐይነቱ የአስተራረስ ባህልና እንደጤፍ የመሳሰሉትን ለምግብ እንዲሆኑ ማድረግ ራሱን የቻለ የፈጠራ ችሎታ ብቻ ሳይሆን፣ አንደኛው የዕድገት መገለጫና ህብርተሰብአችንንም ለማያያዝ የቻለ ነው ብሎ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። በዚህ ረገድ ገበሬው በረቀቀ መልክ በማሰብና ልዩ ልዩ ሰብሎችንና ለዘይት የሚሆኑ እንደተልባና ሰሊጥ፣ እንዲሁም ኑግ የመሳሰሉትን በመዝራትና በማስተዋወቅ በአገራችን ምድር የምግብ አብዮት እንዲካሄድ ለማድረግ በቅቷል። እናቶቻችንም ይህንን ዕድል በመጠቀም እንጀራና ዳቦ በመጋገር ለአገራችን የባህል ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ለማበርከት ችለዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን እንደ ጠላ፣ ጠጅና ካቲካላ የመሳሰሉትን እዚያው አገር ውስጥ በመፍጠርና በመጥመቅ የባህል መጠጦች እንዲሆኑ ለማድረግ በቅተዋል። የእነዚህን መጠጦች አጠማመቅ ስንመለከት ደግሞ ሳይንሳዊ ናቸው። ለምሳሌ የካቲካላን አጠማመቅ ስንመለከት ለካቲካላ የሚሆን የእህል ዐይነት ዳጉሳ ብቻ ነው። ይህ እህል በመጀመሪያ ደረጃ በውሃ እንዲበቅል ከተደረገ በኋላ ከጌሾ ጋር በመዋሃድ በመቆምጠጥ በስሎ ድፍድፉ በጋን ውስጥ ተቀምጦ በትንሽ እሳት እንዲበስል ይደረጋል። የተወሰነ የቴምፕሬቸር መጠን ላይ ከደረሰ በኋላ እንፋሎቱ በቀርቀሃ ጠብ ጠብ  በማለት ካቲካላ ይወጣዋል። የካቲካላ አጠማመቅም ሂደት ኬሚካላዊና ፊዚክስ ነው። መኮምጠጡ የኬሚካል ሂደት ሲሆን፣ ሲቀቀልና ወደ እንፋሎት ተለውጦ ካቲካላ ሲሆን ደግሞ ፊዚክስ ነው። ባጭሩ እናቶቻችን በኢንቲዩሽን  ደረጃ ሳይንቲስቶች ናቸው ማለት ይቻላል። ይህ ዐይነቱ የካቲካላና የጠላ አጠማመቅ በማዕከለኛው ዘመን በምዕራብ አውሮፓ የተለመደና ቀስ በቀስም ወደ ኢንዱስትሪ ምርትነት የተለወጠ ነው። ጌሾም በአውሮፓ ምድር የተስፋፋና ለቢራ ጠመቃና ለልዩ ልዩ የአልክሆል መጠጦች መጥመቂያ የሚያገለግል ነው። ይህንን ሁኔታ ስንመለከት በጥንት ዘመን አንደኛው አገር ከሌላው ሳይኮርጅ በማየት፣ በሙክራና በልምድ ብዙ ነገሮችን እንዳገኘና እንደፈጠረ ለመገንዘብ እንችላለን።

ወደ አባባሌ ስመጣ ከሳይንሳዊ ዕውቀት ጋር ስላልተዋወቅ ነው እንደዚህ ዐይነቱ ወንጀል ለመሰራት የተቻለው ስል ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ማለት የአንድን ህብረተሰብ ምንነት፣ የተጓዘበትንና በሂደት ውስጥ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የተፈጠሩ፣ ይሁንና ደግሞ ለህዝብ ጠቀሚታ ያላቸውን ነገሮች በሙሉ ለመጠናት ባለመቻላቸውና በቁንጽል አስተሳሰብ ላይ ብቻ መረባረብ ስለተጀመረ የማያስፈልግ ግብግብ ውስጥ ለመግባት ቻልን ማለቴ ነው። እንደዚህ ስል ግን የመሬት ላራሹ የመሳሰሉት ነገሮች በተጠናና ፊዩዳል የሚባለውንም የህብረተሰብ ክፍል በማይጎዳ መልክ መታወጅና መተግበር የለባቸውም ማለቴ አይደለም። በማንኛውም አገር፣ በተለይም ደግሞ በካፒታሊስት አገሮች ውስጥም የጥገና ለውጦችና እንዲያም ሲል ገበሬውን ከቀየው ሳያፈናቅሉ የኢንዱስትሪ አብዮት የመሳሰሉትና በአጠቃላይ ሲታይ ኢኮኖሚያዊና ህብረተሰብአዊ ዕድገት ለመምጣት ባልቻለ ነበር። በሌላ ወገን ግን የሚነሳው ጥያቄ ጥገናዊ ለውጥም ሆነ የኢንዱስትሪ አብዮትን ለማካሄድ የግዴታ ገበሬው ከመሬቱ መፈናቀል አለበት ወይ? የሚለው ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። በጊዜው የነበረው አስተሳሰብ ፊዩዳላዊ ስለነበረና ፖለቲካ የሚባለው አስተሳሰብ ስር የሰደደ ስላልነበረና የኃይል አሰላለፉም ለከበርቴው መደብ የሚያደላ ስለነበር ገበሬው ዝም ብሎ ከማየት በስተቀር ሌላ አማራጭ አልነበረውም።  ይሁንና ግን በአጠቃላይ ሲታይ በማንኛውም ህብረተሰብ ውስጥ በተጠና መልክና በዕቅድ አንድን ህብረተሰብ የሚጠቅሙና እንደማህበረሰብም የሚያያዙት ነገሮች ቀሰ በቀስ ተግባራዊ መሆን አለባቸው። ካለጥገናዊ ለውጥ መሻሻልና ዕድገት በፍጹም ሊታዩና ሊመጡ አይችሉም።

በአጠቃላይ ሲታይ የህብረተሰብአዊ ለውጥን ሂደት ስንመለከት ስልጣኔ ሊመጣ የቻለው ጥቂት ምሁራን የማሰብ ኃይልን ከፍተኛ ቦታ በመስጠት ነው። ምክንያቱም የማሰብ ኃይሉን ለመጠቀም የማይችል ሰው ወይም የህብረተሰብ አካል ኃይልን ስለሚያስቀድም የግዴታ በቀላሉ እልባት ሊያገኝ የማይችል ህብረተሰብአዊ ውዝግብ ውስጥ ይገባል። ህብረተሰብአዊ  ውዝግብ ባለበታገር ውስጥ ደግሞ አንደኛው የህብረተሰብ ክፍል በታጠቀው መሳሪያ በመተማመን ረብሻ የሚፈጥር ከሆነ የሰው ልጅ የመፍጠር ኃይል እንዲታፈን ያደርጋል። የእያንዳንዱም ግለሰብ አስተሳስብ በማያስፈልጉና ለራስም ሆነ ለህብረተሰብ በማይጠቅሙ ነገሮች ላይ እንዲጠመድ ያደርጋል። በግሪክ ምድር በጊዜው የነበረውን በተለይም በፈረጠሙ ኃይሎች ይደረግ የነበረውን የእርስ በርስ ሽኩቻ ምክንያቱን ለማወቅ የግሪክ ፈላስፋዎች መነሻ ያደረጉት የጭንቅላትን ሁኔታ በመመራመር ነበር። ፕሌቶ የሚባለው ታላቅ ፈላስፋ በጊዜው የነበረውን ሁኔታ በደንብ ካጠና በኋላ የደረሰበት ድምደማ “የሰው ልጅ ችግር የማሰብ ችግር ነው”( Problem of Thought) በማለት በትክክል ያስቀምጣል። ፕሌቶ ይህንን ምርኩዝ በማድረግ በዕውነተኛ ዕውቀትና በተሳሳተ ዕውቀት መሀከል ያለውን ልዩነት ቁልጭ አድርጎ ያስቀምጣል። በፕሌቶ ዕምነት ትክክለኛ ዕውቀት ከጭንቅላት ውስጥ በማሰብ ወይም በመመራመር ኃይል የሚገኝ ነው። ትክክለኛ ያለሆነ ዕውቀት ግን በምናያቸውና ይህንን ያህልም በጥልቀት ለማስበ በማንችልባቸው(Sense Preception) ነገሮች ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ የዚህ ዐይነት ዕውቀት በማሽተት፣ በማየት፣ በመነካካት ባጭሩ በአምስቱ የሴንስ ኦርጋኖች ላይ በመመርኮዝ የሚገኝ ዕውቀት ነው። ይህ ዐይነቱ ዕውቀት በነገሮች መሀከል መተሳሰብ እንዳለ፣ አንደኛው በሌላኛው ላይ ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችልና፣ በተለይም ደግሞ የታሪክን ሂደትና የሰውም ልጅ በሂደት ውስጥ ያካበታቸውን ነገሮች ከቁጥር ወይም ከግምት ውስጥ የማያስገባ ነው። ባጭሩ ይህ ዐይነቱ ዕውቀት በውጫዊው ዓለም ላይና በዛሬው ላይ ብቻ የሚያተኩር ነው። ስለሆነም ይህ ዐይነቱ የተሳሳተ ዕውቀት ሰለተፈጥሮም ሆነ ስለህብረተሰብ አገነባብ ዕውነተኛ ግንዛቤ ሊሰጠን አይችልም። በዚህ ዐይነት አስተሳስብ መንፈሱ የተቀረፀ ሰው ነገሮችን ከሁለመንታዊ አንፃር ጠጋ ብሎ የመመራመር ኃይል በፍጹም የለውም። ስለሆነም በቁንጽል አስተሳሰብ በመጠመድ ጠቅላላው ህብረተሰብ እንዲናጋ ያደርጋል። በተለይም በዛሬው ወቅት በአገራችንም ሆነ በተቀረው ዓለም የምንመለከተው መወናበድና በየአገሮች ውስጥ ውዝግብ መፈጠር ዋናው ምክንያት በተለይም የኤሊቱ አስተሳሰብ በዚህ ዐይነቱ ቁንጽል አስተሳሰብ ስለተጠመደ ነው።

ከዚህ ሁኔታ ስንነሳ በታሪክ ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ በአንድ አገር ውስጥ ጦርነት፣ ኢ-ፍትሃዊነትና በአጠቃላይ ሲታይ ማህበራዊ ውዝግቦች የሚፈጠሩት ሳይንሳዊ ዕውቀት ባልተስፋፋበትና፣ በተለይም ደግሞ መንግስት የሚባለው አካል ራሱን ከማደለብ ባሻገር ህብረተሰብን በስርዓትና ምርታማ እንዲሆን ለማደራጀት ብቃትነት ወይም አስፈላጊው ዕውቀት የሌለው ከሆነ ብቻ ነው። ስለዚህ ነው ከጥንት ግዜያት ጀምሮ ሰለመንግስት ፍትሃዊ በሆነ መልከ መዋቀር ጉዳይ፣ የመንግስትን መኪና የሚቆጣጠሩ ሰዎች ደግሞ አይ ፈላስፋዎች መሆን እንዳለባቸው አሊያም ደግሞ በፈላስፋዎች የሚመከሩና ሁለ-ገብ ፖሊሲ በማውጣት ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው መሰበክ ወይም ማስተማር የተጀመረው። ይህ ዐይነቱ ያልተቋረጠ ትግልና ምሁራን ደግሞ በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣንን ለመያዝ ሳይሆን የበለጠ መመራመር ያስፈልጋል ብለው በማትኮር ለተለያዩ ለሰው ልጅ የሚጠቅሙ ዕውቀቶችን በማፍለቅና ከአገሮቻቸው አልፈው ዓለም አቀፋዊ ማድረግ የጀመሩት። ስለዚህም ነው በግለሰቦች ጥረትና ምርምር የተነሳ ማቲማቲክስ፣ የተፈጥሮ ሳይንስ፣ ማለትም እንደ ፊዚክስ፣ ባይሎጂና ኬሚስትሪ የመሳሰሉት ዕውቀቶች በሙሉ በመፈጠር ተፈጥሮን የበለጠ በመቃኘትና በመመራመር እንዲሁም ምስጢሩንም በመረዳት በተፈጥሮ ውስጥ የሚገኙ ነገሮችን አውጥቶ ወደ መሳሪያነት በመለወጥ ልዩ ልዩ ነገሮችን መፍጠርና ማመረት የተቻለው። ቀደም ብለው በተለያዩ አገሮች የተፈጠሩት ዕውቀቶች፣ የከተማ አገነባቦች የኋላ ኋላ ለአውሮፓው ስልጣኔና ለካፒታሊዝም ዕድገት መሰረት መጣል እንደቻሉ የሚታወቅ ጉዳይ ነው።

ወደ አገራችን ስንመጣ ግን ከመንግስት አወቃቀር አንስቶ፣ እስከ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች፣ እንዲሁም ስለከተማ ግንባታዎችና መንደሮች አወቃቀር ሁኔታዎችን ስንምረመር የምናገኘው ሀቅ አብዛኛው ነገሮች በአቦሰጡኝ  የተሰሩ እንጂ በከፍተኛ ምርምርና ጥናት እንዳልሆኑ መገንዘብ እንችላለን። ይህንን ለማወቅ ደግሞ የተወለድንባቸውንና ያደግንባቸውን መንደሮችና የገጠሩን ሁኔታ ወደ ኋላ መለስ ብለን ለማየትና ለመመራመር መቻል አለብን። ለምሳሌ በተወለድንበት መንደር ወይም ገጠር ውስጥ በስርዓት ወይም ጥበባዊ በሆነ መልክ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች አሉ ወይ? የትምህርትቤቶችስ አገነባብና ሁኔታ ምን ይመስላል? ቤተመጻህፍቶችስ አሉ ወይ? በተወለድንበትና ባደግንበት መንደር ውስጥ ከትምህርትቤት ውጭ ለመንፈሳችን መዳበር የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች ተዘጋጅተዋል ወይ? እያልን ጥያቄ ለማቅረብ ብንሞክር አብዛኛዎች ነገሮች ካለማሰብ ወይም ከምርምርና ከጥናት ውጭ እንደተሰሩ በቀላሉ ለመገንዘብ እንችላለን። ይህ ዐይነቱ ሁኔታ የግዴታ በአስተሳሰባችንና በአዕምሮአችን ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ  ለማሳደር እንደቻለ ካለብዙ ጭንቀት መገንዘብ ይቻላል።

ይህንን ትተን ወደ ምንማረው ትምህርት ጋ ስንመጣ ትምህርቱ በዚያ መልክ ለምን እንደተዘጋጀና ለምንስ ዓላማ እንደተዋቀረ ሊነግረን የሚችል ሰው የለም። ይሁንና ግን ካለበቂ ጥናትና ካስፈላጊው ሁኔታዎች ውጭ መሰረተ-ትምህርትቤቶችም ሆነ የመለስተኛና የከፍተኛ ትምህርት መስጫ ትምህርትቤቶች እዚህና እዚያ ተቋቁመዋል። ይህ ዐይነቱ ካለብዙ ምርምርና ጥናት እንዲሁም ጭንቅላትን በሁሉም አቅጣጫ እንዲያዳብር ሆኖ ያልተዘጋጀው የትምህርት አሰጣጥና የአስተማሪዎችም ሁኔታ የግዴታ ለጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት መሰረት ሊሆን ችሏል። በዚህ መልቅ የተዋቀረው ጭንቅላታችን የኋላ ኋላ በቁንጸል መልክ ተግባራዊ ከሆነው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ጋር በመዳበል ሳንወድ በግድ አመጸኛ ሊያደርገን በቅቷል። እንዲያም ሲል ለመደማመጥ የማይችልና ነገሮችን ከሁሉም አቅጣጫ ለማየትና ለማንበብ የማይችል ትውልድ በመፈጠሩ ሁሉም ባይሆን የተወሰነው ጥራዝ-ነጠቅ በመሆን አገራችንን ወደ ማይሆን አቅጣጫ ሊመራት ችሏል ማለት ይቻላል። በሌላ አነጋገር፣ የነገሮችን ሂደት፣ በጊዜው የነበረውን የመንግስት መኪና አወቃቀር፣ በአጠቃላይ ሲታይ ፖለቲካ ብለን የምንጠራው፣ ይሁንና ደግሞ ፊዩዳላዊ አስተሳሰብ የሰፈነበት፣ ወይም ፖለቲካ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ግንዛቤ ያለነበረበት ሁኔታና፣ ሁሉም ነገሮች በግብታዊ መልክ ይካሄዱ ስለነበር የኋላ ኋላ አመጸኛ ሊያደርገን በቅቷል ማለት ይቻላል። እነዚህ ነገሮች ደረጃ በደረጃ ሳይጠኑና፣ በተለይም ደግሞ የመንግስትን ምንነትና ሚና ሳይረዱ በአቦ ሰጡኝ የሚወሰዱ ፖሊሲ ነክ እርምጃዎች መንፈሱን ለመሰብሰብና በቅጡ ለማሰብ የማይችል የህብረተሰብ ኃይል እንዲፈጠር ለማድረግ በቅቷል። ይህ ሁኔታ የግዴታ ጥራዝ ነጠቅነትን ከማስፋፋት አልፎ፣ የነገሮችን አመጣጥና ሂደት በጥናት ላይ በመመርኮዝ ሀተታ ከመስጠት ይልቅ ወደ ተሳሳተ ትረካ ላይ ለመድረስ ተችሏል። ለዚህም ነው በጊዜው የመደብ ትግልና የብሄረሰብ ጥያቄ ወይም የጭቆና ጉዳዮች ሊነሱ የቻሉት። እነዚህ ነገሮች በመነሳታቸው፣ እንደፋሽን በመወሰዳቸውና ጭንቅላታችንን በመያዛቸው ነው ለአንድ አገርና ህብረተሰብ ጠቃሚ የሆኑት እንደ ተፈጥሮ ሳይንስ፣ ማቲማቲክስ፣ የከተማ አገነባብ፣ የሶስዮሎጂና የኢኮኖሚ፣ እንዲሁም የስነ-ልቦና ዕውቀቶች አትኩሮ ሊሰጣቸው ያልተቻለው። አሁንም ቢሆን በእነዚህ ዙሪያ ጥናት የሚያካሂድና ሀተታ በማቅረብ ታዳጊውን ትውልድ የሚያስተምር የለም። አብዛኛው የተረት ተረት በማውራት ጊዜውን እንዲያሳልፍና ህዝብን እንዲያደናግር ዕድል ለማግኘት ችሏል።

ከላይ እንዳልኩት እነፕሌቶ በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያለን ችግር ለማጥናት የሞከሩት ትክክለኛ ዕውቀት በሌለበትና የማሰብ ኅይል ባልዳበረበት፣ በተለይም ደግሞ የገዢው መደብ ፍልስፍናዊ ዕውቀት ከሌለው፣ ወይም በፈላስፋዎች የማይመከርና የማይመራ ከሆነ የግዴታ ኢ-ፍትሃዊነትና ያልተሰተካከለ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ነው። ይህም ማለት የገዢው መደብ የተሳሳተና ኢ-ፍትሃዊነት ያለው ፖለቲካ የሚከተለው ወይም አመጽን የሚያስቀድመው ጭንቅላቱ በትክክለኛ ዕውቀት ያልታነፀ ከሆነ ብቻ ነው። ስለሆነም የማህበራዊ ውዝግቦች ዋናው መነሻ በቁንጽል አስተሳሰብ በመመራት ኃይልን ማስቀደም ነው። በሌላ አነጋገር፣ ጭንቅላት ወይም የማሰብ ኃይል ባልዳበረበት አገር ውስጥ ተግባራዊ የሚሆኑ ነገሮችና አንድን ህብረተሰብ ፈሩን እንዲለቅ የሚያደርጉት ነገሮች ታስቦበት(Intentionally) የሚካሄዱ ሳይሆን ካርቆ ማሰብ ጉድለት የሚተገበሩ ስለሚሆኑ ብቻ ነው።

ወደ አገራችን ሁኔታ ስንመጣ በጊዜው የነበሩትን የብሄረሰብን ሁኔታና ሌሎች ኢ-ፍትሃዊ ነገሮችንና፣ በአጠቃላይ ሲታይ ድህነትን ፈልፋይ የሆኑ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን መተግበር ጉዳይ ለመረዳት የተቻለው በቀላሉ ህብረተሰባችን በመደብ ስለተከፋፈልና የመድብ ትግል ስላለና የብሄረሰብ ጭቆና ስለሰፈነ ነው የሚል ነው። ይህ ዐይነቱ ግንዛቤ የአገራችንን አጠቃላይ ሁኔታ ከዕውቀት ማነስ ጋር ለማያያዝ ካለመሞከርና፣ በተለይም ደግሞ በቲዎሪ ደረጃ እንደ ተፈጥሮ ሳይንስ፣ ልዩ ልዩ የኢኮኖሚ ቲዎሪዎችና የሶስይሎጂ ምርምሮች ባልተስፋፉበት አገር ውስጥ ሊከሰቱ እንደሚችሉ ግንዛቤ ውስጥ አለማስገባት ነው። በተለይም የብሄረሰብ ጥያቄ አነሳስ በሚገባ ሳይጠና የተነሳና ማለቂያ ወደሌለው ውዝግብ ውስጥ ወይም ደግሞ ከዚህም ከዚያም ለፈለቁ የዚኸኛው ወይም የዚያኛው ብሄረሰብ መሬ ነኝ ለሚሉ፣ በመሰረቱ ዕውቀት ለሌላቸውና አመጽን ለሚያስቀድሙ መፈንጫ መድረክ የከፈተ ነው ብሎ አፍን ሞልቶ መናገር ይቻላል። ነገሩን የበለጠ ለመረዳት በአፄ ኃይለስላሴ የአገዛዝ ዘመን ተግባራዊ የሆኑት የኢኮኖሚና የትምህርት ፖሊሲዎች በሙሉ አንድን ብሄረሰብ ብቻ ለመጥቀም ተግባራዊ የሆኑ አልነበሩም። ኢ-ሳይንሳዊ የሆነውና ለጥቅላላው ህዝብ ብሄራዊ ሀብት ለማዳበር የማይችለውና ለፈጠራና ለተከታታይ ምርምር መሰረት ሊሆን የማይችለው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ በመሆኑ አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ወይም አብዛኛው  ብሄረሰብ በድህነትና በኢ-ፍትሃዊነት የሚማቅበት ሁኔታ ሊፈጠር ችሏል። ለዚህ ደግሞ የግዴታ ብዙ መማር አያስፈልግም። በቀላል ዕይታና ጥናት የነበረውን ሁኔታ መረዳት ይቻላል። ለማንኛውም ሳይንሳዊ በሆነ መልክ ለማሰብ ባለመቻሉ ወይም ከሳይንሳዊ ዕውቀት ጋር ልምምድ ስለሌለንና የነገሮችን አነሳስና ሂደት ጠጋ ብሎ መመልከት ስለማንፈልግ በተሳሳተ ትረካ ላይ ብቻ በመመርኮዝ ማለቂያ ወደሌለው ግብግብ ውስጥ ለመግባትና አገርን ለማፈራረስ በቅተናል። ባጭሩ የኤፍሬም ማዴቦ ጥያቄ አነሳስና መልስም ለመስጠት ያለመቻል በዚህ መልክ ነው ግልጽ መሆን ያለበት። ስለሆነም የአገራችንንም የተወሳሰቡ ´ችግሮች መፍታት የምንችለው በሳይንሳዊ ዕውቀት እንጂ እዚህና እዚህ ውርውር በማለትና ሰፊውን ህዝብም በማሳሳት አይደለም።

የንቃተ-ህሊና ያለመዳበር ጉዳይ የሚያስከትለው ችግር!

በፈላስፋዎች፣ ንቃተ-ህሊና(Consciousness) ራስን ማወቅ(Self Consciousness) የሚሏቸው ነገሮች አሉ።  አንድን  ነገር በማየት ይህ ነገር እንደዚህ ነው ብለን መናገር እንችላለን። በሌላው ወገን ግን በህብረተሰብ ውስጥ የሚከሰቱ ችግሮችን ወይም በተጨባጭ የሚታዩ ነገሮችን ለመረዳት በቀጥታ ለማየት ከምንችለው የሚያልፍና ቶሎ ብለን ለመገንዘብ የማንችለው ነገር ነው። ለምን አንድ ህብረተሰብ በዚህ መልክ መዋቀር አለበት? ብሎ የሚጠይቅ አንድም ግለሰብ የለም። ሁላቸንም ስንወለድ ቀድሞውኑ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በተዋቀረ ሁኔታ ውስጥ ስለምንወረወርና ስለምናድግ ያደግንበትን፣ ያየነውንና የምንኖርበትን ሁኔታ ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን በጥያቄ ውስጥ ሳናስገባ ዝም ብለን ብቻ በመቀበል ከመንፈሳችን ጋር በማዋሃድ በዚያው እንገፋባታለን። የተወለድንበትንና ያደግንበትን ሁኔታ በስርዓት መዋቀሩና ያለመዋቀሩን ቀስ በቀስ በመጠየቅና በመመራመር ወይም ደግሞ ውጭ አገር ለብዙ ዓመታት ስንኖር ጥያቄ ስናነሳና በማነፃፀር ትክክለኛ ግንዛቤ ማግኘት የምንችለው። ውጭ አገር የምንኖርበትን ከተማ አገራችን ውስጥ ከተወለድንበት መንደር ወይም ከተማ ጋር ለማወዳደር ደግሞ ያኔውኑ በቀጥታ የሚደረስበት ጉዳይ ሳይሆን ብዙ ዓመታት ካሳለፍን በኋላ ብቻ ነው። ይህንንም ለማድረግ የምንችለው ወይም ጥያቄ የምናነሳ ሁላችንም አይደለንም። አሜሪካም ሆነ አውሮፓ ከሰላሳና ከአርባ ዓመታት በላይ ኖረን በአስተሳሰባችን የማንለወጥ ጥቂቶች አይደለንም። በምዕራብ አውሮፓም ሆነ በአሜሪካን  ለብዙ አስርት ዓመታት ኖረን ንቃተ-ህሊናችንን ለማዳበር የማንችልና ጥያቄም ለመጠየቅ የማንችል ብዙዎች ነን።

የንቃተ-ህሊናችን መዳበርም ሆነ ያለመዳበር ጉዳይ በልጅነታችን ወቅት በዕድገት ላይ የሚወሰን ጉዳይ ነው። በተለይም በልጅነታችን ወቅት  በነቃና የህብረተሰብን ምንነት በተገነዘበ ቤተሰብ ውስጥ የተወለድንና ያደግን ከሆነ ንቃተ-ህሊናችምም የመዳበርና አስተሳሰባችንም ጥሩ የመሆን ዕድል ያገጋጥማቸዋል። በተጨማሪም የአካባቢው ሁኔታ ለንቃተ-ህሊና በጥሩ መልክ መዳብርም ሆነ አለመዳበር  ወሳኝ ሚናን ይጫወታል። ከዚህ ሁኔታ ስንነሳ ምን ዐይነት ቤተሰብ ውስጥ እንደተወለድን፣ ምን ዐይነት አስተዳደግ እንደነበረን፣ ጭንቅላታችንን ለማጎልመስ የሚያስችል ዕውቀት ቀስመን ወይም አልቀሰምን እንደሆን፣ በልጅነታችን ብዙ የምንቀሳቀስና ጂምናስትክም የምንሰራ ከሆነ ወይም የማንሰራ ከሆነ፣ በተለይም ደግሞ ከልዩ ልዩ የሙዚቃ መሳሪያዎች ጋር ትውውቅ ካለንና ወይም ከሌለን፣ ...ወዘተ. ወዘተ.
https://amharic.zehabesha.com/archives/189518
https://youtu.be/FWe66cn9Zd0?si=vCsKNFJqNahCmss7

ፋኖ ታምር ሰራ ለምርኮኛው ብርሀኑ ጁላ አድርሱልን

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189511

Monday, March 25, 2024

ግዙፍ ጦር እየመጣ ነው - አዲስ አበባ ሆስፒታሎች ተጨናነቁ | ዘመነ ካሴ ብረት ለበስ ታንኩን አበጋየው | ዛሬም ዋና ጀነራል እና ኮረኔል ተደመሰሱ | ጀነራል አበባው ለአብይ መርዶ ይዞለት ሄደ
https://youtu.be/lLD3LSj4I-A?si=Ei1Szkdz9uI3W0pO

ካሴ ብረት ለበስ ታንኩን አበጋየው | ዛሬም ዋና ጀነራል እና ኮረኔል ተደመሰሱ | ጀነራል አበባው ለአብይ መርዶ ይዞለት ሄደ

 

https://youtu.be/14vTfsZ6abo?si=ST-LpLXxCzvUIPQd
https://amharic.zehabesha.com/archives/189504
https://youtu.be/0BGx0BjWK1Y?si=E5HZ-sJPIT6qCj_U

"አማራነት ወንጀል አይደለም" ህዝቡን ያስከፋው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር!! | Amhara | 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189490
https://youtu.be/0BGx0BjWK1Y?si=E5HZ-sJPIT6qCj_U

"አማራነት ወንጀል አይደለም" ህዝቡን ያስከፋው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር!! | Amhara | 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189490

Sunday, March 24, 2024

አነጋጋሪው የፋኖ መሪ ዘመነ ካሴ ማን ነው | Zehabesha
https://youtu.be/vKomXBvGhXY?si=b7lwpAV_n9nY4tE8

አነጋጋሪው የፋኖ መሪ ዘመነ ካሴ ማን ነው |  Zehabesha
https://amharic.zehabesha.com/archives/189486
አነጋጋሪው የፋኖ መሪ ዘመነ ካሴ ማን ነው | Zehabesha
https://youtu.be/vKomXBvGhXY?si=b7lwpAV_n9nY4tE8

አነጋጋሪው የፋኖ መሪ ዘመነ ካሴ ማን ነው |  Zehabesha
https://amharic.zehabesha.com/archives/189486

Saturday, March 23, 2024

https://youtu.be/TDXw6dMH8Z0?si=AXNnnYF2eZLOBkRZ

 ከፍተኛ የመሳሪያ ግዥ ከህንድ | ቴዎድሮስ ተሾመ ከብርሃኑ ጁላ 1 ቢልዮን ተቀበለ | ኢሰመኮ ሰለ አገዛዙ ያጋለጠው ጥብቅ መረጃ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189481
ፋኖ ተነሳ -ካሳሁን- ደምሴ -Fano Black People Pride : New Ethiopian Music- Kassahun Demsia (official 2024)
https://youtu.be/BFNpV_-mKig?si=H66KShuh0qxK4rU2

 

ፋኖ ተነሳ -ካሳሁን- ደምሴ -Fano Black People Pride : New Ethiopian Music- Kassahun Demsia (official 2024)

 

https://youtu.be/UwOzBq8snm8?si=K7miYVOlVFc_Knug

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189456
የጀነራሉ አስከሬኑ አዲስ አበባ ገባ እነ አብይ ተላቀሱ | በርካታ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ፋኖን ተቀላቀሉ
https://youtu.be/3wOOR6rjyIw?si=DTY8Nu3Y-XGUFqId

 

የጀነራሉ አስከሬኑ አዲስ አበባ ገባ እነ አብይ ተላቀሱ |

 

https://youtu.be/mAtUyIw1qEA?si=1lUCiXEhbcq1g8on
https://amharic.zehabesha.com/archives/189460
አዲስ አበባ ተቀወጠች የቦንብ ጥቃት ተሰነዘረ | ጀግኖቹ 4 መኪና ሰራዊት ደመሰሱ ሻለቃ ሀብቴ ታሪክ ሰራ አዋጊው ተገደለ
https://youtu.be/_JofJM6kYn4?si=VHgMC1FXNjXVxHhg

https://youtu.be/MH2moiDZkSo?si=MH8TJ0Vca-rZDqPs

አዲስ አበባ ተቀወጠች የቦንብ ጥቃት ተሰነዘረ | ጀግኖቹ 4 መኪና ሰራዊት ደመሰሱ ሻለቃ ሀብቴ ታሪክ ሰራ አዋጊው ተገደለ

አዲስ አበባ "ዘመቻ ዉብአንተ"ን ተቀብሏል ‼️

ቢረፍድም አልመሸም!#ዘመቻውብአንተ#አማራ #Amhara #AmharaRevolution #Ethiopia pic.twitter.com/V8kfejaHQU

— Ab-ፋኖ🦅 (@AbAmharaFano) March 22, 2024

https://youtu.be/5R2N7NWPahU?si=sX5KeQXimHdFSvTn
https://amharic.zehabesha.com/archives/189442

Friday, March 22, 2024

ብርጋዴል ጀኔራል ጋዲሳ ዲሮ በፋኖ ተሰዋ | አዲስ አበባ ተናወጠች፣ የአዳነች አበቤ ቤት ተከበበ|ወደ ፋኖ የተቀላቀሉት ሚኒሻወች ያስተላስለፉት ጥሪ
https://youtu.be/b3H_gYONaTM?si=ppjl6vZTM91IemLP

ብርጋዴል ጀኔራል ጋዲሳ ዲሮ በፋኖ ተሰዋ|አዲስ አበባ ተናወጠች፣ የአዳነች አበቤ ቤት ተከበበ|ወደ ፋኖ የተቀላቀሉት ሚኒሻወች ያስተላስለፉት ጥሪ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189449
https://youtu.be/_JofJM6kYn4?si=VHgMC1FXNjXVxHhg

 

አዲስ አበባ ተቀወጠች የቦንብ ጥቃት ተሰነዘረ | ጀግኖቹ 4 መኪና ሰራዊት ደመሰሱ ሻለቃ ሀብቴ ታሪክ ሰራ አዋጊው ተገደለ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189442

Thursday, March 21, 2024

https://youtu.be/40fk35EmxLg?si=IyEKoACn9TDakYCB

ፋኖ ሕዝብ ሲያወያይ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189436
ጀግና ሲወድቅ ጀግና ይተካል
ጀግና ሲወድቅ ጀግና ይተካል

ሰንደቅ አርማውን፣ ዳግሞ ያነሳል።

*ውብ አንተ* ቢያልፍም ውቦች ተነሱ

እግረ መንገዱን ተተኩ በ'ሱ።

የጀግኖች ኮቴ የተከተሉ

በጣይቱ ስም.......

*ቆራጥ እንስቶች* ይህን ፍም እሳት ተቀላቀሉ።

ሊያም በሸዋ በዋና በሩ

፬ ኪሎ ላይ....

ግዜው ተቃርቧል ሊናድ መንበሩ።

እናም.... *ሻለቃ* ሞቷል አትበሉ

*ምኞቱ ይህ ነው.....!*

እሱ ቢሰዋም *አይቀርም ድሉ!*

** ማምሻውን የሻለቃ ው'ባንተ አባተን አሳዛኝ እልፈት ሰምቼ ማለዳ አንድ ወዳጄ ይህንን በሸዋ ጠ/ግዛት የአማራ ፋኖ እዝ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ዘርፍ ጥሪ የሚያሳይ ቪዲዮ ሲያደርሰኝ ትግል እንደ ሩጫ (ዱላ ቅብብሎሽ) ነውና በፅናትና በተስፋ እንድትኖር ያደርግሃል።

*ነብስ ይማር ለጀግናችን!*

*ፅናት ለእህቶቻችን!*

ጀግና ሲወድቅ ጀግና ይተካል

ሰንደቅ አርማውን፣ ዳግሞ ያነሳል።

*ውብ አንተ* ቢያልፍም ውቦች ተነሱ

እግረ መንገዱን ተተኩ በ'ሱ።

የጀግኖች ኮቴ የተከተሉ

በጣይቱ ስም.......

*ቆራጥ እንስቶች* ይህን ፍም እሳት ተቀላቀሉ።

ሊያም በሸዋ በዋና በሩ

፬… pic.twitter.com/EvgUO9TznZ

— Elizabeth Altaye (@AltayeEthiopia) March 20, 2024
https://amharic.zehabesha.com/archives/189425

Wednesday, March 20, 2024

አዲስ አበባ ነባር መንደሮች በፍጥነት እንዲፈርሱ እየተደረገ ነው | አዲስ አበባ የኦሮሞ ብቻ ናት ብሎ የማወጅ ነው” አዳነች
https://youtu.be/qDvLM8wO6Og?si=WQ-v8Hj4zgOXgHID

 አዲስ አበባ ነባር መንደሮች በፍጥነት እንዲፈርሱ እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ ነባር መንደሮች በፍጥነት እንዲፈርሱ እየተደረገ ነው | አዲስ አበባ የኦሮሞ ብቻ ናት ብሎ የማወጅ ነው” አዳነች

https://youtu.be/LUwmSHMyQ5Q?si=TYIgxg60LXQMGvB8
https://amharic.zehabesha.com/archives/189405
መግለጫው የማነው ለሚለው የፋኖ ቃል አቀባዩ :ዶ/ር አብደላ መልስ
https://youtu.be/zD1XojomBiA?si=YQIP_-4G8fiI-9AD

መግለጫው የማነው ለሚለው የቃል አቀባዩ ምላሽና ጥሪ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189397

Tuesday, March 19, 2024

እስክንድር ነጋ እመራዋለሁ የሚለው የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የሚባል አለ ወይ?
ግርማ ካሳ

ይህ ድርጅት፣ በወረቀት እንጂ በተግባር ያለ አይመስለኝም ብዬ ጽፌ ነበር፡፡ "ተሳስተሃል፣ መረጃው ስለሌለህ እንጂ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው" ተብያለሁ፡፡ እርማቱን ተቀብያለሁ፡፡ በመሆኑም "አላውቅም" ከማለት ውጭ "ያለ አይመስለኝም ወይም የለም" ብሎ መነገር አልችልም፡፡ ስለዚህ ብዙ መረጃ ስለሌለኝ እንዲህ ነው እንዲያ ነው ብዬ ለመናገር ይከብደኛል፡፡

ሆኖም ግን መረጃ ስላገኘሁበት ጉዳይ ግን መናገር እችላለሁ፡፡ በነ ሻለቃ መከታው ማሞና መምህር ምንተስኖት የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ከዚህ "የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት" ከሚባለው ጋር ግንኙነት የለውም፡፡ ወንድም እስክንደር ነጋ ፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ወታደራዊም ሆነ ፖለቲካዊ አመራር ውስጥ አንዱም፣ ጋር የለበትም፡፡ ከጎጃም ወደ ሸዋ ሲመጣ፣ የህዝብ ልጅ፣ የአገዛዙ ታርጌት በመሆኑ ጥበቃ ለርሱ መድበው የርሱን ደህንነት ከመጠበቅ፣ አልፎ አልፎ አንዳንድ ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ፣ እንደ ታዋቂ በህዝብ ተወዳጅ ሰው፣ የሸዋ ፋኖዎችን ወክሎ ሳይሆን ራሱን ወክሎ ንግግሮች እንዲያደርግ ከማመቻቸት ውጭ፡፡

ከዚይ ባለፈ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ መሪዎች፣ ሌሎች እንደሚያደርጉት፣ በየቱቡና ሜዲያ ወጥተው የህዝብ ልጆች፣ ታጋዮች ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ተፈልጎ ከሆነ አያደርጉትም፡፡ ልዩነቶች፣ ክፍተቶችም ካለ የውስጥ ጉዳይ ነው በሚል ችግሮችን በውስጥ፣ በውይይት ለመፍታት ይሞክራሉ እንጂ፣ በየሜዲያው ለአገዛዙ ግባት የፖለቲካና የፕሮፖጋንዳ ትርፍ የሚስጥ ስራን አይሰሩም፡፡ የነርሱ ትኩረት አገዛዙ ላይ እንጂ ሌሎች ፋኖዎች፣ ሌሎች ለህዝብ የሚታገሉ ወገኖች ላይ አይደለም፡፡

ከዚህም የተነሳ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝን፣ ከአማራ ህዝባዊ ሰራዊት ከተባለው ጋር በማገናኘት፣ የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የተባለው ስብስብ አመራሮች ለሰሯቸው ወይንም ለሚሰሯቸው ስህተቶች፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ጋር ማገናኘት ተገቢ አይደለም፡፡

በተቃራኒው ደግሞ አንድ ዋሺንገትን ዲሲ ያለ ወንድም አለ፡፡ አገሩን የሚወድ ታጋይ ነው፡፡ ቢያንስ በውጭ፡፡ ግን የፖለቲካ ብስለት የሌለው፣ ምን አልባት የጤና ችግር ያለበት፣ ስራ ፈት ሰው ነው የሚመስለው፡፡ ሺመልስ ለገሰ ይባላል፡፡ ይህ ሰው የ እስክንድር ነጋ የቅርብ ሰው ነኝ ባይ ነው፡፡ ሆኖም የእስክንድር ነጋ የቅርብ ሰው ነው ማለት፣ እስክንድር ነጋ ነው ማለት እንዳልሆነ በትልቁ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ ብዙ ፣ ካድሬ ይመስል፣ "እስክንድር፣ እስክንድር" የሚሉ አሉ፡፡ ይህም ሰው እንደዚያ ነው፡፡ ይህም ሰውም ሆነ በዳያስፖራ ያሉ ቢጤዎቹ፣ ሌላ የራሳቸው አጀንዳ ይኖራቸዋል፡፡ እነርሱ በሚያደርጉት ነገር ግን እስክንድር ነጋ ላይ ማላከክ ተገቢ አይመስለኝም፡፡

እነዚህ ሰዎች "የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ" በዳያስፖራ የድጋፍ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ለእስክንድር ነጋ ጥበቃ ሲያደርግ የነበረና ምን አልባትም ወደሌሎች ጠቅላይ ግዛቶች እስክንድር ካልሄደ፣ ለእስክንድር አሁንም ጥበቃ እያደረገ ያለ መሆኑን ሳያውቁ ቀርተው አይደለም፡፡

ታዲያ፣ " የእስክንድር ነጋ ደጋፊዎች ነን"፣ እያሉ፣ እስክንድር ነጋን እየጠበቀ ያለ ኃይልን አለመደገፍ ፣ እዙ እያደረገ ያለውን የድጋፍ ማሰባሰቢያ ለማጨናገፍ መሞከር ምን ሊባል ይችላል ?? ጸረ እስክንድርነት፣ በእስክንድር ስም የሚደረግ የአብይ አህመድና ዘረኛው አገዛዝ ጥቅም የሚያስጠብቅ ፣ ብልጽግናዊ፣ ኦህድዳዊ አሳፋሪ ስራ ካልተባለ በቀር !!!!

ወገኖች እኔ ይሄንን በምጽፍበት፣ እናንተም በምታነቡበት ጊዜ ፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ውስጥ ያሉ ፍከለ ጦሮች ከአገዛዙ ጋር አንገት ለአንገት እየተናነቁ ነው፡፡ ህይወታቸውን አወራረደው፣ ለአገር፣ ለህዝብ ትልቅ ዋጋ እየከፈሉ ነው፡፡ እነርሱን አለመደገፍ፣ ከነርሱ ጎን አለመቆም አይቻልም፡፡

ከዚህ በታች ያለውን ማስታወቂያ እናንንብ፡፡ ባር ኮዱን በስልካችን ስካን በማድረግ እንዴት መደገፍ እንደሚገባ ወደ ሚያሳይ ገጽ ይሄዳሉ፡፡
https://amharic.zehabesha.com/archives/189394
ወልቃይት ተጀምሯል | እነኮሎኔል ደመቀ ወዴት...? “ከሞት ያመለጥኩት ለጥቂት ነው” አበባው | ጎንደር ፋኖ 2 ከተማ ተቆጣጠረ | ወልቃይት ውጥረት ነግሷል ደ | ኤፌሳር ሙሉ የጁላ ሰራዊት ተደመሰሰ | ከመቀሌ እስከ ሰቆጣ ከፍተኛ የአብይ የጦርነት ዕቅድ |
https://youtu.be/UNgdSIUKbVI?si=L4CnzkCFeSuvj_Bf

https://youtu.be/5X3ZhY9Bsk8?si=-tqH-uecKcvKAGDA

 

 

 

 ወልቃይት ተጀምሯል | እነኮሎኔል ደመቀ ወዴት...?

https://youtu.be/MjEgRq574cE?si=Mrnhynq7i9ejG-1w

https://youtu.be/Ci7yh9H05wI?si=MXhQxgC8_mOiU1sX

 ጎንደር ቀውጢ ሆናለች ፋኖ 2 ከተማ ተቆጣጠረ | ወልቃይት ውጥረት ነግሷል ደመቀ ዘውዱ ነፍጡን አነሳ | ኤፌሳር ሙሉ የጁላ ሰራዊት ተደመሰሰ

 

https://youtu.be/VtV7l2PeRBo?si=bAca3cpvoJFU5E3E

 

 በFSR ተጭኖ የሄደው ሙሉ በሙሉ አለቀ | ከመቀሌ እስከ ሰቆጣ ከፍተኛ የአብይ የጦርነት ዕቅድ | “የአብይን እቅድ በሚገባ አክሽፈናል”

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189366

Monday, March 18, 2024

ወልቃይት ተጀምሯል | እነኮሎኔል ደመቀ ወዴት...? “ከሞት ያመለጥኩት ለጥቂት ነው” አበባው | ጎንደር ፋኖ 2 ከተማ ተቆጣጠረ | ወልቃይት ውጥረት ነግሷል ደ | ኤፌሳር ሙሉ የጁላ ሰራዊት ተደመሰሰ | ከመቀሌ እስከ ሰቆጣ ከፍተኛ የአብይ የጦርነት ዕቅድ |
https://youtu.be/UNgdSIUKbVI?si=L4CnzkCFeSuvj_Bf

https://youtu.be/5X3ZhY9Bsk8?si=-tqH-uecKcvKAGDA

 

 

 

 ወልቃይት ተጀምሯል | እነኮሎኔል ደመቀ ወዴት...?

https://youtu.be/MjEgRq574cE?si=Mrnhynq7i9ejG-1w

https://youtu.be/Ci7yh9H05wI?si=MXhQxgC8_mOiU1sX

 ጎንደር ቀውጢ ሆናለች ፋኖ 2 ከተማ ተቆጣጠረ | ወልቃይት ውጥረት ነግሷል ደመቀ ዘውዱ ነፍጡን አነሳ | ኤፌሳር ሙሉ የጁላ ሰራዊት ተደመሰሰ

 

https://youtu.be/VtV7l2PeRBo?si=bAca3cpvoJFU5E3E

 

 በFSR ተጭኖ የሄደው ሙሉ በሙሉ አለቀ | ከመቀሌ እስከ ሰቆጣ ከፍተኛ የአብይ የጦርነት ዕቅድ | “የአብይን እቅድ በሚገባ አክሽፈናል”

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189366
ጎንደር ፋኖ 2 ከተማ ተቆጣጠረ | ወልቃይት ውጥረት ነግሷል ደ | ኤፌሳር ሙሉ የጁላ ሰራዊት ተደመሰሰ | ከመቀሌ እስከ ሰቆጣ ከፍተኛ የአብይ የጦርነት ዕቅድ |
https://youtu.be/UNgdSIUKbVI?si=L4CnzkCFeSuvj_Bf

 

 

https://youtu.be/Ci7yh9H05wI?si=MXhQxgC8_mOiU1sX

 ጎንደር ቀውጢ ሆናለች ፋኖ 2 ከተማ ተቆጣጠረ | ወልቃይት ውጥረት ነግሷል ደመቀ ዘውዱ ነፍጡን አነሳ | ኤፌሳር ሙሉ የጁላ ሰራዊት ተደመሰሰ

 

https://youtu.be/VtV7l2PeRBo?si=bAca3cpvoJFU5E3E

 

 በFSR ተጭኖ የሄደው ሙሉ በሙሉ አለቀ | ከመቀሌ እስከ ሰቆጣ ከፍተኛ የአብይ የጦርነት ዕቅድ | “የአብይን እቅድ በሚገባ አክሽፈናል”

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189366

Sunday, March 17, 2024

መቶ አለቃው የኮማንዶ አዛዥ ተማረከ | ከጎጃም ምደር የተሰማ ሰበር ዜና | አብይ 3ቱን ጀኔራሎች አጣ 4ኪሎ ትርምስ ተፈጥሯል | የታሰሩ በርካታ ፖሊሶች በፋኖ ኦፕሬሽን ተፈቱ |
https://youtu.be/grAXGuqp3O8?si=CAgJRwTVnSH0JWfr

 

https://youtu.be/A701KMOT3LE?si=PMRZ-kcBIel55Yc-

 

 

አብይ 3ቱን ጀኔራሎች አጣ 4ኪሎ ትርምስ ተፈጥሯል | የታሰሩ በርካታ ፖሊሶች በፋኖ ኦፕሬሽን ተፈቱ |

https://youtu.be/bt5CLbgIOQo?si=CW8uctJh6-lIgV49

የታሰሩ በርካታ ፖሊሶች በፋኖ ኦፕሬሽን ተፈቱ |
https://amharic.zehabesha.com/archives/189351
መቶ አለቃው የኮማንዶ አዛዥ ተማረከ | ከጎጃም ምደር የተሰማ ሰበር ዜና | አብይ 3ቱን ጀኔራሎች አጣ 4ኪሎ ትርምስ ተፈጥሯል | የታሰሩ በርካታ ፖሊሶች በፋኖ ኦፕሬሽን ተፈቱ |
https://youtu.be/grAXGuqp3O8?si=CAgJRwTVnSH0JWfr

 

https://youtu.be/A701KMOT3LE?si=PMRZ-kcBIel55Yc-

 

 

አብይ 3ቱን ጀኔራሎች አጣ 4ኪሎ ትርምስ ተፈጥሯል | የታሰሩ በርካታ ፖሊሶች በፋኖ ኦፕሬሽን ተፈቱ |

https://youtu.be/bt5CLbgIOQo?si=CW8uctJh6-lIgV49

የታሰሩ በርካታ ፖሊሶች በፋኖ ኦፕሬሽን ተፈቱ |
https://amharic.zehabesha.com/archives/189351

Saturday, March 16, 2024

‹‹አብይ ማደሪያ የለው፣ ግንድ ይዞ ይዞራል!!!›› አንድ ለእናቱ እስክንድር ነጋ!!! እና የደም ነጋዴዎች!!!  (ክፍል ሁለት)
ኢት-ኢኮኖሚ  /ET- ECONOMY

ሚሊዮን ዘአማኑኤል (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

(ለሻለቃ መሣፍንት ልጅ መታሰቢያ ትሁን)

የኃላው ከሌለ የፊቱ የለም!!! ታሪክ አልባዋ ከተማ A City Without Its Past

‹‹ወይ አዲስአበባ፣ ወይ አራዳ ሆይ፣

አገርም እንደሰው፣ ይናፍቃል ወይ!!!

አዲስ አበባ ከተማ ያለ ጥንታዊ ታሪክ!!! A City Without Its Past ………. Demography Change የእስክንድር ቃል ጠብ አላለችም!!! ‹‹ከሰው በፊት የአዲስ አበባ ህዝብን አታፈናቅሉ፣ ቅርሳችንን አታውድሙ፣ አረንጎዴ፣ቢጫ ቀይ ባንዲራችንን አትንኩ፣ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት እየተደረገ ነው›› እያለ በአገር ውስጥ በአደባባይ የሞገተ፣ ዘጠኜ የታሠረ፣ በዓለም አቀፍ አደባባይ በተባበሩት መንግሥታት ፊት ከፕሮፊሰር ጌታቸው ኃይሌ ጋር የአማራን ጀኖሳይድ ያስመዘገበ ባለ ራአዩ የጥንት የጠዋቱ ቆራጥ ታጋይ ታላቁ እስክንድር ያሉት ፕሮፊሰር መስፍን ወለወደማርያም ናቸው፡፡ የእስክንድር ስምና ብዕር ለመለስ ዜናዊ ለወያኔ ኢህአዴግ ፋሽስታዊ አገዛዝ መቅሰፍት ነበረች፣ የእስክንድር ስምና ብዕር ለኮነሬል አብይ አህመድ የኦህዴድ ብልፅግናም ዘረኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ የማትዋጥ የማትተፋ መርዝ ናት፡፡ የታላቁ እስክንድር ትንቢተ ቃል ተፈፅሞል…..በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት (ጀኖሳይድ) ተፈፅሞል!!!

 

እስክንድር የሞቀ ትዳሩንና ቤቱን ከሃገረ አሜሪካ ጥሎ አገር ቤት በርሃ ወርዶ፣ ህዝብቀስቅሶ፣ ፋኖን አደራጅቶ ባይመክት የአማራ ህዝብ ዛሬ ለኦሮሙማ ሥርዓት! ለኦህዴድ ብልፅግና እንቁላል ይገብር ነበር፡፡ የእስክንድር ብዕር ኮነሬል አብይን አሥር ክፍለጦር ድባቅ ይመታል፣ እስክንድር የህዝብ መከታና የደሃ አሌንታ፣ ሰው ሰው የሸተተ ስብእና የተላበሰ የህዝብ ልጅ በወያኔ፣ ኦህዴድና ብአዴን ማንም ምናምቴ ስሙ አይጠራም፡፡ እስክንድር በብዕሩ ሲወድቅ ሲነሳ፣ ሲታሰር ሲፈታ፣ ለዴሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለነፃነት እድሜ ልኩን የታገለ የኢትዮጵያ ፋኖ አርበኛ ነው፡፡  አንድ ለእናቱ! እስክንድር ዱር ቤቴ ብሎ እናንተን አምኖ፣ ለእናንተ ለመሞት፣  የዘር ፍጅትን ለማስቆም፣ የሃገር ጥፋትን ለማስቆም፣ ሁላችንም ፈርተን በራድን ጊዜ፣ ለኮነሬል አብይ አገዛዝን እንቢ አሻፈረኝ  ያለ ለመሠረታዊ ለውጥ የታገለ ጀግና የጥንት የጠዋቱ እሱ ብቻ ነው፡፡ ቤታችንን ሲያፈርሱ ከእኛ ጋር ነበር!!!.......... ሲርበን ሲጠማን ከእኛ ጋር ነበር!!! ባንዲራችንን ሲያወርዱ የሰቀለ እሱ ነበር፡፡ የእስክንድር ግፍ ብዙ አለብን!!! ከሰው በፊት የተገለጠለት እሱ ነበር!!!……….የእስክንድር ራዕይ ህዝብን ለማዳን እንጂ ለሥልጣን አልነበረም፡፡   ኮነሬል አብይ እስክንድርን ለማስገደል ዶልቶ፣ ከጎጃም ምድር ፣ አንዴ አሳፍኖ ሊወስደው ሲል ህዝብ አስለቀቀው እስክንድር የህዝብ ልጅ ነውና!!! ኮነሬል አብይ ሴጣን ካልገደለ አይተኛምና እስክንድርን ከደብረ ኤልያስ ገዳም በደም ነጋዴዎች ጠቆሚነት አሳዶ ሊገለው ሲል በጎዶቹ ብርታት አመለጠ፡፡ እስክንድር

‹‹በርከክ በርከክ አሉ፣ አውሬ መስያቸው

ከሰው መፈጠሬን ማን በነገራቸው

ወንደድሙን ሲገለው፣ ወንድሙን ካልከፋው፡፡

ሱሪውን አምጡለት፣ ደሙ እንዲከረፋው›› ተባለለት፡፡

እስክንድር የሃገሪቱ ታሪካዊ ቅርሶች በኮነሬል አብይ አህመድ ኦህዴድ ብልፅግና ካድሬዎች እየፈረሰ ነው ህዝብ ተነስ ተቃውሞህን አሰማ ብሎ ከፊት እመራ ሲታገል ሁሉም ፈርቶ፣ተከታይ አጣ፡፡ ዛሬ ሜክሲኮ ሠንጋተራ አካባቢ ሸበሌ ሆቴል ጎን የፈረሰው የዘጠና አመት ያስቆጠረው ቅርስ ሎምባርዲያ ሬስቶራንት ህንፃ  በዓይናችን አይተናል፡፡ ዛሬ ለገሃር አካባቢ የፈረሰው ቅርብ ጊዜ የተሠራው የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅትና፣ የቬርኔሮ ህንፃ መኪና ተራ ጎን የነበረ ህንፃ ወደ አመድነት ተቀይረው፣ በዓይናችን አይተናል፡፡ ለአረብ ኢምሬትስ ኤግልስ ሄልስ ፕሮጀክት (Eagle Hills project – La Gare in Ethiopia) በስድስት አመት ተሰርቶ የሚያልቅ ህንፃዎች ሰዕልለላንቲካ የሚሆን ፎቶግራፍ አሳይተውን ወፍም የለ!!! አብይ ሦስት ሽህ ስድስት መቶ ሜትር ካሬ ቦታ ለአረብ ወዳጆቹ ሸጠ፡፡ ዛሬ አራት ኪሎ የተፈጥሮ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ የሚገኝ ህንፃ አፈረሰው፡፡

የሥነ-ሕዝብ ለውጥ (Demography Change) የኮነሬል አብይ መንግሥት የአዲስ አበባ ህዝብ የሥነ-ህዝብ ለውጥ ማድረግ የፈለገው የአዲስ አበባ ብሔር ብሔረስብ ስብጥር በ2007 እኤአ Ethnic groups of Addis Ababa (2007) አማራ Amhara (47.05%)፣ ኦሮሞ Oromo (19.51%)፣ ጉራጌ  Gurage (16.34%)፣ ትግራይ  Tigrayan (6.18%)፣ ስልጤ  Silt'e (2.94%)፣ ጋሞ Gamo (1.68%)፣ ልዩ ልዩ Other (6.3%) በመሆኑ የአማራ፣ የጉራጌ ህዝብ ቁጥር በቤት ማፍረስ ለመቀነስ፣ ከአዲስ አበባ ለማስወጣት ብሎም የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር ለመጨመር በአዲስ አበባ ማስፈር ጀመሩ፡፡ ኮነሬል አብይ መንግሥትን የኦሮሞ ህዝብ አንቅሮ ስለተፋው እቅዳቸው ከሽፎል፣ በፍቅርና በአንድነት የኖረውን የኢትዮጵያን ህብረ-ብሔር ህዝብ መለያየት የኦህዴድ ብልፅግና ካድሬ  አይችልም፡፡ የወያኔ ኢህአዴግ ካድሬም ወድቆልና!!!

 

2019 እኤአ ጀምሮ የኮነሬል አብይ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ ዘመን ከፍተኛ የቤት ማፍረስ ዘመቻ በ‹‹ህገወጥ ንብረት ስም››በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሰበታ፣ ቡራዩ፣ ለገጣፎ፣ለገዳዲ፣ሱሉልታ፣ኢልሞጆና፣ ገላን ከተሞች ንዎሪዎች የነበሩ አስራሁለት ሽህ አባወራዎች ቤት ፈረሰ፡፡ እስክንድርና ባልደራስ ድርጅት ብቻ ነበሩ በግንባር ቀደምትነት የቤት ፈረሳውን የተቃወሙት፡፡ Since early 2019, the Ethiopian government under Abiy Ahmed administration begun large-scale house demolition that deemed "illegal property" in Addis Ababa and the Oromia Region in the area of Sebeta, Buraryu, Legetafo, Legedadi, Sululta, Ermojo, and Galan towns, with 12,000 houses destroyed by the government, which led to further unrest in the country…………………..(1)

 

በፌብሪዎሪ 19 ቀን 2019እኤአ ማለዳ ጠዋት የለገጣፎ ከተማን ቡልዶዘሮች ወረሮት የሦስት ሽህ አባወራዎችን ቤቶች ዶጋ አመድ አደረጉት፡፡ ሦስት ሽህ ቤት አልባ ዜጎች፣ ከነመተዳደሪያ ንግድ ቤታቸው ተዘጉ፡፡ የለገዳዲና ለገጣፎ ከተሞች ከንቲባ ሐቢባ ሲራጂ የቤቶቹ መፍረስ በ2017 እኤአ ማስተር ፕላን መሰረት የከተማ ስትራቴጂ መሆኑን በመደገፍ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠጭ፡፡ On 19 February 2019, bulldozers were raid into Legetafo area and demolished 3,000 homes, leading to thousands homelessness and ruin business activities. Mayor of Legetafo Legedadi Habiba Sirajs supported the demolition as a necessary steps corresponding to the 2017 master plan, which was part of urban strategies.

 

ኮነሬል አብይ አህመድ ሃገር ለመሸጥ፣ የሰው ጎጆ ለማፍረስ፣ እናቶችን ለማስለቀስ የመጣ ሴጣን ነው፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ደሓዎቹን ጠራርጎ በማፈናቀል ለዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ኤግል ሒልስ ኩባንያ (Eagle Hills) 360000 (ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ) ካሬ መሬት ቦታ የሸጠ ነውረኛ ሰው ነው፡፡ ለኤግልስ ሒልስ ፕሮጀክት ሲባል የፈረሱ ህንፃዎች ከላይ ከፎቶግራፍ ላይ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ማየት ይቻላል፡፡ ኢምሬትስ ኤግል ሒልስ በፈረሰው ቦታ ላይ ከአንድ ፎቅ ሌላ የሠራው የለም፡፡ ቦታው ድረስ ሄዶ በማየት ኦህዴድ ብልጽግና መንግሥት አብይ፣ አዳነች አቤቤ፣ ሥልጣን ከያዙ ጀምሮ የአዲስ አበባን ከተማ ንዋሪዎች በማፈናቀል ላይ እንዳሉ መገንዘብ ያሻል፡፡

 

{1} በዳግማዊ ዐፄ ምኒሊክ ዘመን በ1917እኤአ የተገነባው የመቶ አመታት ታሪካዊው ፍራንኮ ኢትዮጵያ ምድር ባቡር  ይፈርሳል፣ ኮነሬል አብይ የምኒልክን ታሪካዊ ውርስና ቅርስ በማጥፋት ቤተመንግስታቸውን በአንድነት ፓርክ ብሎ ሰይሞታል፣ ከመቶ አመታት ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ መንግሥት ምድር ባቡር ቅርስ አጥፍተዋል፣

{2} የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ብዙ መቶ ሚሊዩን ብር የወጣበት አዲስ ህንጻ ፈርሷል፣

{3} የቡፌ ደ ላጋር ታሪካዊ ባህላዊና ዘመናዊ የመዝናኛ ሥፍራ ፈርሷል፣

{4} የቬርኔሮ ህንፃ ባለ ስድስት ፎቅ ህንፃ  ፈርሷል፣

{5} የሞዓ አንበሳ ሃውልት  ከጣልያን ሃገር የተመለሰው ሐውልት፣ በሮም የጀግናው ዘርዓይ ድረስ የተሠዋበት ታሪካዊ ሃውልት በደንብ አልተያዘም፣ ወዘተ

 

ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ (United Arab Emirates)፡- የአቡ ዳቢ ኩባንያ፣ ኤግል ሒልስ  (Eagle Hills launches project – La Gare in Ethiopia) በአዲስ አበባ ከተማ ለገሃር  ሠፈር  ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት 360,000 sq metres  (ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ) ካሬ  ሜትር ባለ ይዛታ ሲሆን የቦታው የስፋቱ ትልቅነት ሃምሳ የአዲስ አበባ ስታዲየምን ያክላል፡፡ ኤግልስ ሒልስ ኩባንያ በተሰጠው ቦታ ላይ ባለ አራትና አምስት ኮኮብ ሆቴሎች ለመገንባት፣ የመዝናኛ ሥፍራዎች ለመስራት፣ አራት ሽህ ቤቶች ለመስራት እቅድ ነድፎ ነበር፡፡ ኤግልስ ሒልስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ወጪ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት 27% (ሃያ ሰባት) በመቶ ድርሻ አለው ተብሎል ነበር፡፡ ኤግልስ ሒልስ ኩባንያ ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ በጀት በመመደብ ለአንድ ሽህ ስድስት መቶ አባወራዎች የመኖሪያ ቤቶች እንደሚሰራና ምንም ዓይነት መፈናቀል እንደማይኖር ለንዋሪዎቹ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ ኤግልስ ሒልስ ኩባንያ የለገሃር ፕሮጀክት ለሃያ አምስት ሽህ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥርና በሰባት አመት ፕሮጀክቱ ተሠርቶ እንደሚያልቅ ተገልጾ ነበር፡፡ ወፍም የለ!!! ወሬ ነው ኮነሬል አብይ አገር የሸጠ ባንዳ መውደቂያው ደርሶል፡፡ “Abu Dhabi firm, Eagle Hills has launched a massive integrated community development project, La Gare in Ethiopia. La Gare will cover 360,000 sq metres of the Ethiopian capital, Addis Ababa and would include multi-star hotels, leisure outlets, commercial units, and 4000 homes. The estimated value of La Gare is $2 billion and the Ethiopian government is reported to hold a 27% share in the project. According to the Ethiopian Prime Minister, Abiy Ahmed, Eagle Hills has set aside an additional budget of $68 million for 1600 households that would be uprooted during the development process……..Reportedly, apart from creating a new city center, La Gare would also lead to an increase of approximately 25,000 jobs. The project is said to finish its first phase of development, mainly the construction of malls, in three years. The overall estimated time for project completion is reported to be seven years.”………………………………….(2)

 

ኤግልስ ሒልስ (Eagle Hills)፡- የጡት አባታቸው ኮነሬል አብይ አህመድ በተገኘበት  አቡዳቢ መሠረቱን ያደረገ የግል ሪል ስቴት ኢንቬስተር ወደ ኢትዮጵያ ምድርና ንግዱ ህብረተሰብ ሠተት ብሎ ገባ፡፡ በአዲስ አበባ ለገሐር ባቡር ጣቢያ እንዲከትም ኮነሬል አብይ ኢንቨስት እንዲያደርግ ተመቻቸለት፡፡ በለገሐር ባቡር ጣቢያ ሦስት ሽህ ስድስት መቶ ካሬ ሜትር ኩታ ገጠም ቦታ በኮነሬሉ ያለ አንዳች ጨረታ ገጸ-በረከት ተበረከተለት፡፡ የለገሃር አራት ሽህ ንዋሪዎችን ያፈናቀለ ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት ለንዋሪዎች መኖሪያ ቤት ይሠራል ተብሎ በውሸት ተሰበከ፡፡

ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት በስድስት አመታት የግንባታ ጉዞው አንድ የመኖሪያ ኮንዶሚኒየም በመስራት ገና ተጠናቆ ሳያልቅ በሙሉ መሸጡ ታውቆል፡፡  ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት የገነባውን እየሸጠ በሚያገኘው ገንዘብ ሌላ በመገንባት ላይ የሚገኝ ደሃ ደላላ ድርጅት ነው፡፡ ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት ሌላ ቦታ አንድ አምስት የመሠረት ግንባታ የሠራባቸው ሥፍራዎች በተለያዩ ሳይቶች ይስተዋላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ጋዜጠኞች፣ የማህበራዊ ሚዲያ አክቲቪስቶች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የከተማችን የፓርላማ አባሎች ካሉ ይሄን ሥፍራ ጎብኝተው፣ የሚሠራውን የወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት  ላለፉት ስድስት አመታት የተሠራ  የኤግል ሒልስ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት በመመልከት ኃላፊነታቸውን እንዳልተወጡ ማስተዋል ይቻላል፡፡ ኤግል ሒልስ ሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ድርጅት ሥፍራውን ተነጥቆ  ለኢትዮጵያዊያን  አገር በቀል ሪል ስቴት ኢንቨስተሮች በጨረታ ቦታውን እንዲያለሙ እድል ቢያገኙ ተዓምር መሥራት ይችልሉ፡፡ አገር በቀል ሪል ስቴት ኢንቨስተሮች፣ ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ ካሬ ሜትር  ቦታ ሊዝ ገዝተው እንዲያለሙና በግፍ ለተፈናቀሉ ደሃ የህብረተሰብ ቤት ጨምሮ በመገንባት፣ ኤግል ሒልስ ከአገር እንዲወጣ ማድረግ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው እንላለን፡፡  የኮነሬል አብይ አህመድና የሼክ መሃመድ ቢን ዛአይድ አል ናህያን ሚስጢራዊ ግንኙነት አገራችንን  ወደ ማያባራ ጦርነት በማሸጋገር ላይ ይገኛል፣ ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ደግሞ ሰው አልባ ድሮውን በመስጠት  ንፁሃን ዜጎች እንዲጨፈጨፉ አድርገዋል፡፡ ዲያስፖራው በየአረብ ኢምሬትስ ኢንባሲዎች ሠላማዊ ሠልፍ በማድረግ ሼክ መሃመድ ቢን ዛአይድ  የኮነሬል አብይ አህመድን መንግስት መቃወም ይገባቸዋል፡፡  ኢምሬትስ ሰው ዓልባ አውሮፕላኖች በመስጠትና በመሸጥ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን ጦርነት በማቀጣጠል እንድትወገዝ ማድረግ ያሻል፡፡  የኢትዮጵያ ህዝብ ተቃውሞውን ማሰማት ይጠበቅበታል እንላለን፡፡

 

እስክንድር ነጋ ዳግማዊው ጥቁር ሰው በአማራ ለመሠረታዊ ለውጥ፣ ጠቅላይ ጦር ሠፈሩን አውድም (Bombard the Headquarter) የወያኔን የኦህዴድና ብአዴን ካድሬዎች ለፍርድ እናቅርብ!!! የሻለቃ መሣፍንት ልጅ መሆንን በሰማን ጊዜ ልባችን ክፉኛ አዘነ፣ እኛ ተቀምጠን የአስራሰባት አመት ልጅ ስለእኛ መሞቱ በምን እዳው አስባለን፤ መልካም አገር አላወረስናችሁም እና አዘንን፣ በጀግንነትህ በኮነሬል አብይ መቃብር ላይ ከአዲስ አበባ የአንተን ኃውልት የፋኖ አርበኛ እሸቴ ሞገስና የልጅ የታገሱ እሸቴ ኃውልት እናቆማለን፡፡ በኮነሬል አብይ ፋሽታዊ አገዛዝ በማያባራ ጦርነት ልጃቻቸውን የተነጠቁ የትግራ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ ወዘተ እናቶች የልጆቻችሁን ኃውልት በኮነሬል አብይ መቃብር ላይ እናቆማለን፡፡ የልጆቻችሁ  ታሪክ በወርቅ ቀለም ይፃፋል፡፡ ትላንት የፋሽስቱ ኮነሬል መንግሥቱ የቀይ ሽብር ሠማእታት የጋራ ኃውልት ቆሞልና፡፡ ቃል ለምድር ለሠማይ!!! ይህ ጊዜም ያልፋልና!!!

 

የእስክንድር ትንቢተ-ራዕይ ከሩቅ ይሰማል!!! የአማራን ጀኖሳይድ እናስቁም፣ የቤት ፈረሳን እናስቁም!!! ህዝባዊ መንግስት እንመሠርታለን፣ የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ እናብስ!!! ለሥልጣን አንጣላ፣ ሥልጣን በህዝብ ምርጫ የሚመጣ ታላቅ ኃላፊነት ነው፡፡ የደም ነጋዴዎች ሴራን እንበጣጥስ!!!  ስልጣን ከእውቀት ጋር ለአዲሱ የዲጂታል ቴክኖሎጅ ዘመን ወጣት ፖለቲከኞች የሃገራችንን ችግሮች በጠረጴዛ ዙሪያ ብቻ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት ብቃት ያላችሁ አዲስ ትውልድ ስልጣኑን መጨበጥ ታሪክ የጣለባችሁ አደራ ነው፡፡ አንባገነኑ የኮነሬል አብይ መንግሥት በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች ከ111(መቶ አስራአንደ) ሽህ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ አስታውቆል፡፡ ግማሽ ሚሊዮኝ ህዝብ ተፈናቅሎል፡፡ ገና የኮነሬል አብይ ቤተመንግሥትና የሽመልስ አብዲሳ ቤተመንግሥት ሲገነባ የሚሊዮኖች ቤት ፈርሶ ተፈናቃዬች ቁጥር የትየለሌ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ከፋኖ አርበኛ  ጋር ዛሬውኑ ቆርጠ ለትግል በመነሳት  የኮነሬል አብይ መንግሥት   ግፍ ማስቆም ታሪካዊ አደራ አለብን፡፡ የፖለቲካ እስረኞችን ጋዜጠኞችን፣ ምሁራኖች የእስር ቤቶቸ በር ሠብረን ማስፈታት ታሪካዊ ስራ አለብን!!! የእስክንድር ግፍ ብዙ አለብን ….ብዙ አለብን…. እስክንድርን ከነ ድክመቱ እንውደደው፣ እናርመው፣ እንደግፈው፣ የኃላው ከሌለ፣ የፊቱም የለምና!!!   እንበል አሥራሁለት!!!

 

የኮነሬል አብይ ኦህዴድ ብልፅግና መንግሥት ከአማራ ክልል ይውጣ!!! ከትግራይ ክልል እንደወጣ ሁሉ!!!

 

ምንጭ

House demolition in Ethiopia (2019–present)

(2)Abu Dhabi Based Eagle Hills Invests in Ethiopia/By  D&B Bureau/  November 21, 2018
https://amharic.zehabesha.com/archives/189355
‹‹አብይ ማደሪያ የለው፣ ግንድ ይዞ ይዞራል!!!›› አንድ ለእናቱ እስክንድር ነጋ!!! እና የደም ነጋዴዎች!!!  (ክፍል ሁለት)
ኢት-ኢኮኖሚ  /ET- ECONOMY

ሚሊዮን ዘአማኑኤል (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

(ለሻለቃ መሣፍንት ልጅ መታሰቢያ ትሁን)

የኃላው ከሌለ የፊቱ የለም!!! ታሪክ አልባዋ ከተማ A City Without Its Past

‹‹ወይ አዲስአበባ፣ ወይ አራዳ ሆይ፣

አገርም እንደሰው፣ ይናፍቃል ወይ!!!

አዲስ አበባ ከተማ ያለ ጥንታዊ ታሪክ!!! A City Without Its Past ………. Demography Change የእስክንድር ቃል ጠብ አላለችም!!! ‹‹ከሰው በፊት የአዲስ አበባ ህዝብን አታፈናቅሉ፣ ቅርሳችንን አታውድሙ፣ አረንጎዴ፣ቢጫ ቀይ ባንዲራችንን አትንኩ፣ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት እየተደረገ ነው›› እያለ በአገር ውስጥ በአደባባይ የሞገተ፣ ዘጠኜ የታሠረ፣ በዓለም አቀፍ አደባባይ በተባበሩት መንግሥታት ፊት ከፕሮፊሰር ጌታቸው ኃይሌ ጋር የአማራን ጀኖሳይድ ያስመዘገበ ባለ ራአዩ የጥንት የጠዋቱ ቆራጥ ታጋይ ታላቁ እስክንድር ያሉት ፕሮፊሰር መስፍን ወለወደማርያም ናቸው፡፡ የእስክንድር ስምና ብዕር ለመለስ ዜናዊ ለወያኔ ኢህአዴግ ፋሽስታዊ አገዛዝ መቅሰፍት ነበረች፣ የእስክንድር ስምና ብዕር ለኮነሬል አብይ አህመድ የኦህዴድ ብልፅግናም ዘረኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ የማትዋጥ የማትተፋ መርዝ ናት፡፡ የታላቁ እስክንድር ትንቢተ ቃል ተፈፅሞል…..በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት (ጀኖሳይድ) ተፈፅሞል!!!

 

እስክንድር የሞቀ ትዳሩንና ቤቱን ከሃገረ አሜሪካ ጥሎ አገር ቤት በርሃ ወርዶ፣ ህዝብቀስቅሶ፣ ፋኖን አደራጅቶ ባይመክት የአማራ ህዝብ ዛሬ ለኦሮሙማ ሥርዓት! ለኦህዴድ ብልፅግና እንቁላል ይገብር ነበር፡፡ የእስክንድር ብዕር ኮነሬል አብይን አሥር ክፍለጦር ድባቅ ይመታል፣ እስክንድር የህዝብ መከታና የደሃ አሌንታ፣ ሰው ሰው የሸተተ ስብእና የተላበሰ የህዝብ ልጅ በወያኔ፣ ኦህዴድና ብአዴን ማንም ምናምቴ ስሙ አይጠራም፡፡ እስክንድር በብዕሩ ሲወድቅ ሲነሳ፣ ሲታሰር ሲፈታ፣ ለዴሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለነፃነት እድሜ ልኩን የታገለ የኢትዮጵያ ፋኖ አርበኛ ነው፡፡  አንድ ለእናቱ! እስክንድር ዱር ቤቴ ብሎ እናንተን አምኖ፣ ለእናንተ ለመሞት፣  የዘር ፍጅትን ለማስቆም፣ የሃገር ጥፋትን ለማስቆም፣ ሁላችንም ፈርተን በራድን ጊዜ፣ ለኮነሬል አብይ አገዛዝን እንቢ አሻፈረኝ  ያለ ለመሠረታዊ ለውጥ የታገለ ጀግና የጥንት የጠዋቱ እሱ ብቻ ነው፡፡ ቤታችንን ሲያፈርሱ ከእኛ ጋር ነበር!!!.......... ሲርበን ሲጠማን ከእኛ ጋር ነበር!!! ባንዲራችንን ሲያወርዱ የሰቀለ እሱ ነበር፡፡ የእስክንድር ግፍ ብዙ አለብን!!! ከሰው በፊት የተገለጠለት እሱ ነበር!!!……….የእስክንድር ራዕይ ህዝብን ለማዳን እንጂ ለሥልጣን አልነበረም፡፡   ኮነሬል አብይ እስክንድርን ለማስገደል ዶልቶ፣ ከጎጃም ምድር ፣ አንዴ አሳፍኖ ሊወስደው ሲል ህዝብ አስለቀቀው እስክንድር የህዝብ ልጅ ነውና!!! ኮነሬል አብይ ሴጣን ካልገደለ አይተኛምና እስክንድርን ከደብረ ኤልያስ ገዳም በደም ነጋዴዎች ጠቆሚነት አሳዶ ሊገለው ሲል በጎዶቹ ብርታት አመለጠ፡፡ እስክንድር

‹‹በርከክ በርከክ አሉ፣ አውሬ መስያቸው

ከሰው መፈጠሬን ማን በነገራቸው

ወንደድሙን ሲገለው፣ ወንድሙን ካልከፋው፡፡

ሱሪውን አምጡለት፣ ደሙ እንዲከረፋው›› ተባለለት፡፡

እስክንድር የሃገሪቱ ታሪካዊ ቅርሶች በኮነሬል አብይ አህመድ ኦህዴድ ብልፅግና ካድሬዎች እየፈረሰ ነው ህዝብ ተነስ ተቃውሞህን አሰማ ብሎ ከፊት እመራ ሲታገል ሁሉም ፈርቶ፣ተከታይ አጣ፡፡ ዛሬ ሜክሲኮ ሠንጋተራ አካባቢ ሸበሌ ሆቴል ጎን የፈረሰው የዘጠና አመት ያስቆጠረው ቅርስ ሎምባርዲያ ሬስቶራንት ህንፃ  በዓይናችን አይተናል፡፡ ዛሬ ለገሃር አካባቢ የፈረሰው ቅርብ ጊዜ የተሠራው የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅትና፣ የቬርኔሮ ህንፃ መኪና ተራ ጎን የነበረ ህንፃ ወደ አመድነት ተቀይረው፣ በዓይናችን አይተናል፡፡ ለአረብ ኢምሬትስ ኤግልስ ሄልስ ፕሮጀክት (Eagle Hills project – La Gare in Ethiopia) በስድስት አመት ተሰርቶ የሚያልቅ ህንፃዎች ሰዕልለላንቲካ የሚሆን ፎቶግራፍ አሳይተውን ወፍም የለ!!! አብይ ሦስት ሽህ ስድስት መቶ ሜትር ካሬ ቦታ ለአረብ ወዳጆቹ ሸጠ፡፡ ዛሬ አራት ኪሎ የተፈጥሮ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ የሚገኝ ህንፃ አፈረሰው፡፡

የሥነ-ሕዝብ ለውጥ (Demography Change) የኮነሬል አብይ መንግሥት የአዲስ አበባ ህዝብ የሥነ-ህዝብ ለውጥ ማድረግ የፈለገው የአዲስ አበባ ብሔር ብሔረስብ ስብጥር በ2007 እኤአ Ethnic groups of Addis Ababa (2007) አማራ Amhara (47.05%)፣ ኦሮሞ Oromo (19.51%)፣ ጉራጌ  Gurage (16.34%)፣ ትግራይ  Tigrayan (6.18%)፣ ስልጤ  Silt'e (2.94%)፣ ጋሞ Gamo (1.68%)፣ ልዩ ልዩ Other (6.3%) በመሆኑ የአማራ፣ የጉራጌ ህዝብ ቁጥር በቤት ማፍረስ ለመቀነስ፣ ከአዲስ አበባ ለማስወጣት ብሎም የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር ለመጨመር በአዲስ አበባ ማስፈር ጀመሩ፡፡ ኮነሬል አብይ መንግሥትን የኦሮሞ ህዝብ አንቅሮ ስለተፋው እቅዳቸው ከሽፎል፣ በፍቅርና በአንድነት የኖረውን የኢትዮጵያን ህብረ-ብሔር ህዝብ መለያየት የኦህዴድ ብልፅግና ካድሬ  አይችልም፡፡ የወያኔ ኢህአዴግ ካድሬም ወድቆልና!!!

 

2019 እኤአ ጀምሮ የኮነሬል አብይ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ ዘመን ከፍተኛ የቤት ማፍረስ ዘመቻ በ‹‹ህገወጥ ንብረት ስም››በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሰበታ፣ ቡራዩ፣ ለገጣፎ፣ለገዳዲ፣ሱሉልታ፣ኢልሞጆና፣ ገላን ከተሞች ንዎሪዎች የነበሩ አስራሁለት ሽህ አባወራዎች ቤት ፈረሰ፡፡ እስክንድርና ባልደራስ ድርጅት ብቻ ነበሩ በግንባር ቀደምትነት የቤት ፈረሳውን የተቃወሙት፡፡ Since early 2019, the Ethiopian government under Abiy Ahmed administration begun large-scale house demolition that deemed "illegal property" in Addis Ababa and the Oromia Region in the area of Sebeta, Buraryu, Legetafo, Legedadi, Sululta, Ermojo, and Galan towns, with 12,000 houses destroyed by the government, which led to further unrest in the country…………………..(1)

 

በፌብሪዎሪ 19 ቀን 2019እኤአ ማለዳ ጠዋት የለገጣፎ ከተማን ቡልዶዘሮች ወረሮት የሦስት ሽህ አባወራዎችን ቤቶች ዶጋ አመድ አደረጉት፡፡ ሦስት ሽህ ቤት አልባ ዜጎች፣ ከነመተዳደሪያ ንግድ ቤታቸው ተዘጉ፡፡ የለገዳዲና ለገጣፎ ከተሞች ከንቲባ ሐቢባ ሲራጂ የቤቶቹ መፍረስ በ2017 እኤአ ማስተር ፕላን መሰረት የከተማ ስትራቴጂ መሆኑን በመደገፍ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠጭ፡፡ On 19 February 2019, bulldozers were raid into Legetafo area and demolished 3,000 homes, leading to thousands homelessness and ruin business activities. Mayor of Legetafo Legedadi Habiba Sirajs supported the demolition as a necessary steps corresponding to the 2017 master plan, which was part of urban strategies.

 

ኮነሬል አብይ አህመድ ሃገር ለመሸጥ፣ የሰው ጎጆ ለማፍረስ፣ እናቶችን ለማስለቀስ የመጣ ሴጣን ነው፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ደሓዎቹን ጠራርጎ በማፈናቀል ለዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ኤግል ሒልስ ኩባንያ (Eagle Hills) 360000 (ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ) ካሬ መሬት ቦታ የሸጠ ነውረኛ ሰው ነው፡፡ ለኤግልስ ሒልስ ፕሮጀክት ሲባል የፈረሱ ህንፃዎች ከላይ ከፎቶግራፍ ላይ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ማየት ይቻላል፡፡ ኢምሬትስ ኤግል ሒልስ በፈረሰው ቦታ ላይ ከአንድ ፎቅ ሌላ የሠራው የለም፡፡ ቦታው ድረስ ሄዶ በማየት ኦህዴድ ብልጽግና መንግሥት አብይ፣ አዳነች አቤቤ፣ ሥልጣን ከያዙ ጀምሮ የአዲስ አበባን ከተማ ንዋሪዎች በማፈናቀል ላይ እንዳሉ መገንዘብ ያሻል፡፡

 

{1} በዳግማዊ ዐፄ ምኒሊክ ዘመን በ1917እኤአ የተገነባው የመቶ አመታት ታሪካዊው ፍራንኮ ኢትዮጵያ ምድር ባቡር  ይፈርሳል፣ ኮነሬል አብይ የምኒልክን ታሪካዊ ውርስና ቅርስ በማጥፋት ቤተመንግስታቸውን በአንድነት ፓርክ ብሎ ሰይሞታል፣ ከመቶ አመታት ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ መንግሥት ምድር ባቡር ቅርስ አጥፍተዋል፣

{2} የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ብዙ መቶ ሚሊዩን ብር የወጣበት አዲስ ህንጻ ፈርሷል፣

{3} የቡፌ ደ ላጋር ታሪካዊ ባህላዊና ዘመናዊ የመዝናኛ ሥፍራ ፈርሷል፣

{4} የቬርኔሮ ህንፃ ባለ ስድስት ፎቅ ህንፃ  ፈርሷል፣

{5} የሞዓ አንበሳ ሃውልት  ከጣልያን ሃገር የተመለሰው ሐውልት፣ በሮም የጀግናው ዘርዓይ ድረስ የተሠዋበት ታሪካዊ ሃውልት በደንብ አልተያዘም፣ ወዘተ

 

ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ (United Arab Emirates)፡- የአቡ ዳቢ ኩባንያ፣ ኤግል ሒልስ  (Eagle Hills launches project – La Gare in Ethiopia) በአዲስ አበባ ከተማ ለገሃር  ሠፈር  ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት 360,000 sq metres  (ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ) ካሬ  ሜትር ባለ ይዛታ ሲሆን የቦታው የስፋቱ ትልቅነት ሃምሳ የአዲስ አበባ ስታዲየምን ያክላል፡፡ ኤግልስ ሒልስ ኩባንያ በተሰጠው ቦታ ላይ ባለ አራትና አምስት ኮኮብ ሆቴሎች ለመገንባት፣ የመዝናኛ ሥፍራዎች ለመስራት፣ አራት ሽህ ቤቶች ለመስራት እቅድ ነድፎ ነበር፡፡ ኤግልስ ሒልስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ወጪ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት 27% (ሃያ ሰባት) በመቶ ድርሻ አለው ተብሎል ነበር፡፡ ኤግልስ ሒልስ ኩባንያ ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ በጀት በመመደብ ለአንድ ሽህ ስድስት መቶ አባወራዎች የመኖሪያ ቤቶች እንደሚሰራና ምንም ዓይነት መፈናቀል እንደማይኖር ለንዋሪዎቹ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ ኤግልስ ሒልስ ኩባንያ የለገሃር ፕሮጀክት ለሃያ አምስት ሽህ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥርና በሰባት አመት ፕሮጀክቱ ተሠርቶ እንደሚያልቅ ተገልጾ ነበር፡፡ ወፍም የለ!!! ወሬ ነው ኮነሬል አብይ አገር የሸጠ ባንዳ መውደቂያው ደርሶል፡፡ “Abu Dhabi firm, Eagle Hills has launched a massive integrated community development project, La Gare in Ethiopia. La Gare will cover 360,000 sq metres of the Ethiopian capital, Addis Ababa and would include multi-star hotels, leisure outlets, commercial units, and 4000 homes. The estimated value of La Gare is $2 billion and the Ethiopian government is reported to hold a 27% share in the project. According to the Ethiopian Prime Minister, Abiy Ahmed, Eagle Hills has set aside an additional budget of $68 million for 1600 households that would be uprooted during the development process……..Reportedly, apart from creating a new city center, La Gare would also lead to an increase of approximately 25,000 jobs. The project is said to finish its first phase of development, mainly the construction of malls, in three years. The overall estimated time for project completion is reported to be seven years.”………………………………….(2)

 

ኤግልስ ሒልስ (Eagle Hills)፡- የጡት አባታቸው ኮነሬል አብይ አህመድ በተገኘበት  አቡዳቢ መሠረቱን ያደረገ የግል ሪል ስቴት ኢንቬስተር ወደ ኢትዮጵያ ምድርና ንግዱ ህብረተሰብ ሠተት ብሎ ገባ፡፡ በአዲስ አበባ ለገሐር ባቡር ጣቢያ እንዲከትም ኮነሬል አብይ ኢንቨስት እንዲያደርግ ተመቻቸለት፡፡ በለገሐር ባቡር ጣቢያ ሦስት ሽህ ስድስት መቶ ካሬ ሜትር ኩታ ገጠም ቦታ በኮነሬሉ ያለ አንዳች ጨረታ ገጸ-በረከት ተበረከተለት፡፡ የለገሃር አራት ሽህ ንዋሪዎችን ያፈናቀለ ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት ለንዋሪዎች መኖሪያ ቤት ይሠራል ተብሎ በውሸት ተሰበከ፡፡

ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት በስድስት አመታት የግንባታ ጉዞው አንድ የመኖሪያ ኮንዶሚኒየም በመስራት ገና ተጠናቆ ሳያልቅ በሙሉ መሸጡ ታውቆል፡፡  ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት የገነባውን እየሸጠ በሚያገኘው ገንዘብ ሌላ በመገንባት ላይ የሚገኝ ደሃ ደላላ ድርጅት ነው፡፡ ኤግል ሒልስ ፕሮጀክት ሌላ ቦታ አንድ አምስት የመሠረት ግንባታ የሠራባቸው ሥፍራዎች በተለያዩ ሳይቶች ይስተዋላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ጋዜጠኞች፣ የማህበራዊ ሚዲያ አክቲቪስቶች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የከተማችን የፓርላማ አባሎች ካሉ ይሄን ሥፍራ ጎብኝተው፣ የሚሠራውን የወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት  ላለፉት ስድስት አመታት የተሠራ  የኤግል ሒልስ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት በመመልከት ኃላፊነታቸውን እንዳልተወጡ ማስተዋል ይቻላል፡፡ ኤግል ሒልስ ሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ድርጅት ሥፍራውን ተነጥቆ  ለኢትዮጵያዊያን  አገር በቀል ሪል ስቴት ኢንቨስተሮች በጨረታ ቦታውን እንዲያለሙ እድል ቢያገኙ ተዓምር መሥራት ይችልሉ፡፡ አገር በቀል ሪል ስቴት ኢንቨስተሮች፣ ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ ካሬ ሜትር  ቦታ ሊዝ ገዝተው እንዲያለሙና በግፍ ለተፈናቀሉ ደሃ የህብረተሰብ ቤት ጨምሮ በመገንባት፣ ኤግል ሒልስ ከአገር እንዲወጣ ማድረግ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው እንላለን፡፡  የኮነሬል አብይ አህመድና የሼክ መሃመድ ቢን ዛአይድ አል ናህያን ሚስጢራዊ ግንኙነት አገራችንን  ወደ ማያባራ ጦርነት በማሸጋገር ላይ ይገኛል፣ ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ደግሞ ሰው አልባ ድሮውን በመስጠት  ንፁሃን ዜጎች እንዲጨፈጨፉ አድርገዋል፡፡ ዲያስፖራው በየአረብ ኢምሬትስ ኢንባሲዎች ሠላማዊ ሠልፍ በማድረግ ሼክ መሃመድ ቢን ዛአይድ  የኮነሬል አብይ አህመድን መንግስት መቃወም ይገባቸዋል፡፡  ኢምሬትስ ሰው ዓልባ አውሮፕላኖች በመስጠትና በመሸጥ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን ጦርነት በማቀጣጠል እንድትወገዝ ማድረግ ያሻል፡፡  የኢትዮጵያ ህዝብ ተቃውሞውን ማሰማት ይጠበቅበታል እንላለን፡፡

 

እስክንድር ነጋ ዳግማዊው ጥቁር ሰው በአማራ ለመሠረታዊ ለውጥ፣ ጠቅላይ ጦር ሠፈሩን አውድም (Bombard the Headquarter) የወያኔን የኦህዴድና ብአዴን ካድሬዎች ለፍርድ እናቅርብ!!! የሻለቃ መሣፍንት ልጅ መሆንን በሰማን ጊዜ ልባችን ክፉኛ አዘነ፣ እኛ ተቀምጠን የአስራሰባት አመት ልጅ ስለእኛ መሞቱ በምን እዳው አስባለን፤ መልካም አገር አላወረስናችሁም እና አዘንን፣ በጀግንነትህ በኮነሬል አብይ መቃብር ላይ ከአዲስ አበባ የአንተን ኃውልት የፋኖ አርበኛ እሸቴ ሞገስና የልጅ የታገሱ እሸቴ ኃውልት እናቆማለን፡፡ በኮነሬል አብይ ፋሽታዊ አገዛዝ በማያባራ ጦርነት ልጃቻቸውን የተነጠቁ የትግራ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ ወዘተ እናቶች የልጆቻችሁን ኃውልት በኮነሬል አብይ መቃብር ላይ እናቆማለን፡፡ የልጆቻችሁ  ታሪክ በወርቅ ቀለም ይፃፋል፡፡ ትላንት የፋሽስቱ ኮነሬል መንግሥቱ የቀይ ሽብር ሠማእታት የጋራ ኃውልት ቆሞልና፡፡ ቃል ለምድር ለሠማይ!!! ይህ ጊዜም ያልፋልና!!!

 

የእስክንድር ትንቢተ-ራዕይ ከሩቅ ይሰማል!!! የአማራን ጀኖሳይድ እናስቁም፣ የቤት ፈረሳን እናስቁም!!! ህዝባዊ መንግስት እንመሠርታለን፣ የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ እናብስ!!! ለሥልጣን አንጣላ፣ ሥልጣን በህዝብ ምርጫ የሚመጣ ታላቅ ኃላፊነት ነው፡፡ የደም ነጋዴዎች ሴራን እንበጣጥስ!!!  ስልጣን ከእውቀት ጋር ለአዲሱ የዲጂታል ቴክኖሎጅ ዘመን ወጣት ፖለቲከኞች የሃገራችንን ችግሮች በጠረጴዛ ዙሪያ ብቻ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት ብቃት ያላችሁ አዲስ ትውልድ ስልጣኑን መጨበጥ ታሪክ የጣለባችሁ አደራ ነው፡፡ አንባገነኑ የኮነሬል አብይ መንግሥት በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች ከ111(መቶ አስራአንደ) ሽህ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ አስታውቆል፡፡ ግማሽ ሚሊዮኝ ህዝብ ተፈናቅሎል፡፡ ገና የኮነሬል አብይ ቤተመንግሥትና የሽመልስ አብዲሳ ቤተመንግሥት ሲገነባ የሚሊዮኖች ቤት ፈርሶ ተፈናቃዬች ቁጥር የትየለሌ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ከፋኖ አርበኛ  ጋር ዛሬውኑ ቆርጠ ለትግል በመነሳት  የኮነሬል አብይ መንግሥት   ግፍ ማስቆም ታሪካዊ አደራ አለብን፡፡ የፖለቲካ እስረኞችን ጋዜጠኞችን፣ ምሁራኖች የእስር ቤቶቸ በር ሠብረን ማስፈታት ታሪካዊ ስራ አለብን!!! የእስክንድር ግፍ ብዙ አለብን ….ብዙ አለብን…. እስክንድርን ከነ ድክመቱ እንውደደው፣ እናርመው፣ እንደግፈው፣ የኃላው ከሌለ፣ የፊቱም የለምና!!!   እንበል አሥራሁለት!!!

 

የኮነሬል አብይ ኦህዴድ ብልፅግና መንግሥት ከአማራ ክልል ይውጣ!!! ከትግራይ ክልል እንደወጣ ሁሉ!!!

 

ምንጭ

House demolition in Ethiopia (2019–present)

(2)Abu Dhabi Based Eagle Hills Invests in Ethiopia/By  D&B Bureau/  November 21, 2018
https://amharic.zehabesha.com/archives/189355

Friday, March 15, 2024

 ህብረት ይሻላል (Better Together) ጥሪ ለኢትዮጵያውያን ሁሉ!
መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓመተ ምህረት

ምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ላይ የተሰየመችው ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካሉ እድሜ ጠገብ ሃገራት መካከል ቀዳሚ ሃገር ናት። ይህቺ ሃገር በአፍሪካ ክፍለ ዓለም ውስጥ እንደ በረሃ አበባ ብቻዋን በቅላ ብቻዋን ነጻ ሃገር ሆና የኖረች ብርቅዬና የነጻነት ምልክት ናት። በተለይ በቅኝ ግዛት የማቀቁ የአፍሪካ ሃገራት በሥሥት የሚያዩዋት እናታቸው ናት።

ኢትዮጵያ በረጅም ጊዜ ታሪኳ ውስጥ ከውጭ የሚመጣባትን ጥቃት ለማለፍ አያሌ ውጣ ውረዶችን ብታልፍም፣ ውስጣዊ አለመረጋጋቶች ብዙ ዋጋ ቢያስከፍሏትም በየዘመኑ የተፈጠሩ ልጆቿ “ህብረታችን ይበልጣል በሚል ሃያል መረዳት ሁል ጊዜም አብረው ታግለው አኩሪ የነጻነት ታሪክ ጽፈዋል። በአድዋ ተራሮች ላይ በአባቶቻችን ደም የተጻፈው ታሪክ ህብረታችን! ኢትዮጵያችን! እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝ የሚሉ ሃይለ ቃሎች ናቸው። ካራማራ ተራሮች ላይ የተጻፈው የዚህኛው ዘመን ታሪካችም እንደዚሁ ተመሳሳይ ሃይለ ቃል ያስተጋባል። ህብረታችን! ኢትዮጵያችን! እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝ የሚለው የአድዋው መሪ ቃል ነው ካራማራ ላይም የተደገመው። ለዚህ ነው የካራማራው ድላችን ዳግማዊ አድዋ እየተባለ የሚጠራው።

 

ኢትዮጵያ የእድሜዋንና የስልጣኔ ፈርቀዳጅነቷል ያህል ለመራመድ እንዳትችል ያደረጋት ነገር፣ በአንድ በኩል ከውጪ የሚነሱ ጦሮችን ለመመከት ዘወትር ዘብ ቆማ የቆየች ሲሆን በሌላ በኩል የውስጥ አለመረጋጋቶች ሃገረ መንግስቱን እገጭ እጓ እንዲል እያደረጉት ስለቆዩ ነው።

ከሁሉም የሚከፋው ግን ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ልጆች በህብረት የጻፉት ታሪክ አያሌ ቢሆንም በቅርብ ጊዜ ታሪካችን አዲስ ህገ መንግስት ስንጽፍ አብሮነታችንንና ህብረታችንን አቃሎ ልዩነቶቻችንን የሚያደምቅ ሆነ። ያቺን ሃያል ሀገር እንደ አንድ የማትከፋፈል ሃያል አገር ሳይሆን እንደ ዛኔ ጋባ ቤት፣ አንዳችን ባኮረፍን ጊዜ አፍርሰናት የምንሄድባት ጊዚያዊ ቤት አድርገን ሰራን። “ህብረት ይሻላል” የሚለው የኢትዮጵያውያን ሃይለ ቃል ተገስሶ ልዩነት ይልቃል ወደሚል ማህበረ ፖለቲካ መውረዳችን በአራቱም አቅጣጫ ያለንን ኢትዮጵያውያንን ሁሉ አንገት ያስደፋ የታሪክ ጠባሳችን ነው።

ይህ ልዩነትን የሚያጎላው አስተምህሮ ተቀይሮ ልዩነትም አንድነትም እርስ በርስ ሳይፈራረሱ የሚኖሩበትን የፖለቲካ ምህዋር ማቆም የሚገባን ቢሆንም ዛሬ ድረስ ልዩነቶች እየሰፉ ኢትዮጵያዊ ህብረታችን እየተሸረሸረ እየተሸረሸረ እየተሸረሽረ መጥቷል።

ሃገችንን ለዚህ አደገኛ የህብረት መሰረት መናጋት የጣላት ዋና ችግር አንዱ ይህ ህገ መንግስት ላይ የተጻፈው ህብረታችንን ፈራሽ ያደረገው ክፉ ሃሳብ ሲሆን በሌላ በኩል መንግስት የሚጠቀመው የከፋፍለህ ግዛ የአገዛዝ ስልት ነው። በተለምዶ ከፋፍለህ ግዛ የሚለው ፍልስፍና ከመቼውም ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ ሆኗል። የወቅቱ ጠቃላይ ሚንስትር  ዶክተር አብይ አህመድ ዋና የአገዛዝ ስልት ይሄ ነው። ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ህዝብ ለውጥ ፈልጎ ከፍተኛ ትግል ያደረገ ቢሆንም የቀድሞው የኢንሳ ድሬክተር የነበሩት አብይ አህመድ የኢትዮጵያውያንን ለውጥ በመጥለፍ ወደ ስልጣን በመጡ በወራት የመንግስትን መዋቅር የሚጠልፍ (state capture የሚያደርግ) የደህንነት መዋቅር ፈጥረው ስሙን ኮሬ ነጌኛ ብለው የኢትዮጵያውያንን የዴሞክራሲና የሽግግር ተስፋ አጨናግፈዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን እኚህ ሰው ወደ ስልጣን ከመጡ ማግስት ጀምሮ ችግሮችን በብልሃት ከመፍታት ይልቅ በኮሬ ነጌኛ ኮሚቴው አማካኝነት በሴራና በመጠላልፍ ዘዴ ስልጣን ላይ ለመቆየት በመሞከራቸው ኢትዮጵያውያን እርስ በርስ ተዋግተው በትግራይ ጦርነት ወቅት አያሌ ዜጎች ረገፉ፣ የብዙ ወገኖቻችን ቤት ተዘጋ፣ ረሃብና መፈናቀልን አተረፍን። ህብረት ይበልጥብናል፣ እኔ የመንድሜ ጠባቂ ነኝ የሚሉ ሃይለ ቃሎች በአባቶቻችን ደም የተከተበባቸው የአድዋ ተራሮች ላይ እርስ በርስ ተዋግተን አንገት የሚያስደፋ ታሪክ አስጽፈውናል። የኮሬ ነጌኛው መሪ አብይ አህመድ የትግራዩ ጦርነት ጋብ ባለ በማግስቱ ከአማራ ህዝብ ጋር ሌላ ጦርነት ውስጥ ገብቶ ይታያል። የዚህን ህዝብ ጥያቄ ለመፍታት ፖለቲካዊ መፍትሄ እንደመፈለግ በጦር ሃይል አንበርክኬ እገዛዋለሁ በማለቱ ዛሬ የአማራ ህዝብ በከፍተኛ ሁኔታ ከአብይ አህመድ አገዛዝ ጋር መራራ ትግል ላይ ይገኛል።

ኮሬ ነጌኛ የተሰኘው ህቡዕ ኮሚቴ ዋና ማዕከሉን አድርጎ የነበረው የኦሮሞን ህዝብ በመሆኑ ዛሬ ኦሮምያ ውስጥ ቅጥ ያጣ አስተዳደር፣ ዝርፊያና እንግልት፣ እስራትና ግድያ ቁም ስቅሉን እያሳየው ይገኛል። የኦሮሞ ህዝብ የሚያነሳው የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄ የጠለፉት ኮሬ ነጌኛዎች ይህ ህዝብ የሞተላትን ሃገሩን እያጠቁበት ይገኛሉ። ከሌላው ወገኑ ጋር እንዲጋጭና የስርዓቱ ዘበኛ እንዲሆን በኦሮምኛ ቋንቋ እየተናገሩ ሌት ከቀን ሊከፋፍሉት ይሞክራሉ።

የደቡቡ ወገናችንን ሁናቴ ስናይ አንዴ ጋሞን፣ አንዴ ወላይታን፣ አንዴ ሲዳማን ወዘተ. በየተራ የአብይ አህመድ መንግስት በኮሬ ነጌኛ አሰራሩ ቁም ስቅሉን እያሳየው ነው። ረሃብና መፈናቀል በዙር መከራውን እያሳየው ነው። አብይ አህመድ ስልጣን ላይ በመጣ በጥቂት ጊዚያት የጌዲኦ ወገኖቻችን ተፈናቅሎ መከራና ስቃይ ማየቱ አይዘነጋም። ጋምቤላ ውስጥ አኙዋክን ከኑየር ለማጋጨት የዚያን አካባቢ ህዝብ አንድነትና ሰላም በመንሳት የተባበረ የልማትና የሰላም ጥያቄ እንዳያነሳ ሁል ጊዜም ይጥራል። ይህ ክልል ከፍተኛ የተፈጥሮ ጸጋ ያለው ቢሆንም መንግስት ከልማት ይልቅ ግጭት ጠመቃ ላይ ተጥዶ በመኖሩ ዛሬ በዚህ ክልል ውስጥ ሰላም ወጥቶ መግባት፣ አምርቶ በምርት መደሰት የማይቻልበት ክልል ሆኗል። የሶማሌ ክልል ወገናችን በግጭትና በመገናቀል በረሃብ ይሰቃያል። በተለይ ባለፉት አምስት ዓመታት ግጭት፣ መፈናቀል፣ ረሃብ ያላገኘው የሃገራችን ክፍል ከቶ የትኛው ነው? የግጭትና የመፈናቀል መራራ ጽዋ ያልጠጣ ከቶ የትኛው ብሄር፣ ከቶ የትኛው ክልል ነው?

እውነት ነው ይህ ህዝብ በየፊናው ብዙ ዋጋ እየከፈለ ባለበት በዚህ ሰዓት እንደገና የስርዓት ለውጥ ለማምጣት ትግል ላይ ነው። ይሁን እንጂ ትግላችን በየብሄራችን የታጠረ በመሆኑ በአንድ በኩል የስርዓት ለውጥና የሽግግር ጊዜ ፈጥረን እፎይ ለማለት እንዳንችል፣ በጋራ ታግለን በፍጥነት የተሻለ ስርዓት ለመገንባት እንዳንችል አድርጎናል። በሌላ በኩል ይህ የተበጣጠሰ የትግል መስመራችን ድንገት የመንግስት መውደቅ ቢከሰት እንደገና በተባበር ሁኔታ አዲስ የሽግግር ስርዓት ለመፍጠር እንዳንችል የሚያደርግ ስጋትን ደቅኖብናል። በዚያም አለ በዚህ የኢትዮጵያውያን ትግል መከፋፈሉ የጠቀመው ስልጣን ላይ ላለው ኮሪ ነጌኛ ብቻ ነው። መከፋፈላችንና ትግላችን መበጣጠሱ የኮሬ ነጌኛ ኮሚቴ ህልም እስካሁን እንዲቆይ አድርጎብናል።

ኢትዮጵያውያን ጋሞዎች፣ አኙዋኮች፣ ኮንሶዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ትግራዮች፣ አማሮች ወዘተ እንደ ከበረ  እንቁ ይዘነው የነበረው አብሮነታችን፣ ህብረታችን እነሆ ዛሬ በብሄር ፖለቲካና በኮሬ ነጌኛ መዋቅር ምስጦች እየተበላና እየተሸረሸረ አገራችን አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ወድቃብናለች ። መንግስት ከፋፍለህ ግዛ የሚለውን ስልት ሲጠቀም ኢትዮጵያውያን ሊኖራቸው የሚገባው የትግል ስልት የመንግስትን ስልት የተቃረነ አደረጃጀት በመፍጠርና ተከፋፍሎ ለመገዛት አለመመቸት ነው።  ህብረትን የበለጠ ማጥበቅ ነው የትግሉ መጀመሪያ። ይህ የትግል ስልት ነው ጌም ቸንጀር የትግል ስልት የምንለው። በብሄር እየከፋፈለ ሊገዛን ያሰበውን ስርዓት ለመታገል ከተለያዬ ብሄር የመጣን የኢትዮጵያ ልጆች በአንድነት በህብረት ቆመን ከተነሳን ያን ጊዜ አሸንፈን ተነሳን ማለት ነው። የፖለቲካ አሸናፊ ሆነን ተነሳን ማለት ነው።

እኛ ኢትዮጵያውያን ህብረታችን የተጎዳው በመንግስት ከፋፍለህ ግዛው ስልት ብቻ ሳይሆን ከፍ ሲል እንደተጠቆመው አንዱ ስለራሱ ብቻ ሳይሆን ስለሌላው የሚያኖር ህገ መንግስት ስለሌለን ነው። ሃገር የሚባለው ስብስብ ሲቋቋም ዋና መተሳሰሪያ መርሆ መሆን ያለበት እንደ ብሄር ለራስ ብቻ ሳይሆን ስለሌላው መኖር ትልቅ ዋጋ የሚሰጠውና የህብረታችን መልህቅ ሆኖ መቀረጽ አለበት። አንዱ ስለ ራሱ ብቻ ሳይሆን ስለሌላውም የሚያኖረው ስርዓት ያልገነባ ሃገር ህብረቱ እንደምን አይፈርስም? እንዲህ ዓይነት ደካማ መተሳሰሪያ መርሆ ከጫንቃው ላይ የተጫነበት ህዝብ የገዛ ህብረቱ ሁልጊዜም አንካሳ ይሆናል።  የጋራ ተብሎ የተሰራለት ቤትም በአሸዋ ላይ የተሰራ የሰነፍ ሰው ቤትን የሚመስል ይሆናል። እንዲህ አይነት መተሳሰብ የጎደለው ህገ መንግስት የተጫነበት ህዝብ ጠንካራ የጋራ ተቋማትን ዘርግቶ ወደ ልማትና ወደ ሰላም እንደምን አድርጎ ወደፊት  መራመድ ይችላል? ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ዛሬ ስለ ህብረታችን በጥብቅ የምናስብበት ወሳኝ የታሪክ መታጠፊያ ምዕራፍ ላይ ነን። መዘናጋትና መታለል በቅቶ የህብረታችንን ስጋቶች ለመቅረፍ የምንነቃበት ወሳኝ ወቅት ላይ ነን። የተጫነንን ነገር ሁሉ ፈንቅለን ተነስተን ህብረት! ህብረት! ህብረት! የምንልበት ጊዜ ላይ ነን።  ለስርዓት ለውጥ የሚደረጉ ትግሎችን ሁሉ  እርስ በእርስ ለማያያዝ ደፋ ቀና የምንልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ነን።

ዛሬ በአማራ ክልል አካባቢ የተነሳውን የፋኖ ትግል ሁላችን ልንደግፍና አንድ ላይ ሆነን ይህንን ትግል የጋራ አድርገን ልንቀርጸው ይገባል። አንዱ ወገናች ትግል ሲጀምር ህብረትን ማሳየት፣ አብሮነትን ማሳየት ይገባል እንጂ አንዱ የአንዱን ትግል አይጥለፈው። የኦሮሞው ትግልና የአማራው ትግል፣ የትግራዩ ትግልና የደቡቡ ትግል፣ የጋምቤላው ትግልና የሃረሬው ትግል ሁሉ መደጋገፍና አንድ ትልቅ ጥላ ወደ መፍጠር ማደግ አለበት። ኢትዮጵያዊ ጥላ ፈጥረን ትግሎችንን አሰባስበን ህብረታችንን አጠናክረን እነሆ ከወደቅንበት ልንነሳ ይገባል። ፋኖነት አኙዋክነት፣ ኑየርነት፣ አማራነት፣ ኦሮሞነት፣ ጋሞነት፣ ወላይታነት፣ ቡርጂነት፣ ትግራይነት፣ ወዘተ ነው። ሁላችን ኢትዮጵያውያን ህብረታችንን እንደገና ለማደስ የተበላሸውን ሽግግር እንደገና ቀና ለማድረግ ህብረታችንን እንጠብቅ። ህብረት ይሻላል (better together) የሚለው ስሜት በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሃይለ ቃል ሆኖ ይግነን፣። መለያየትና እርስ በርስ ያለመናበብ የተሻለ ስርዓት እንዳንገነባ አድርጎናል። የዴሞክራሲ ትግላችንን እድሜውን አስረዝሞታል።የተለያዬና የተበጣጠሰ ትግል ውስጥ ገብተን አንድ አሸናፊ ሃይል ስልጣን ቢይዝም የረጋ ሃገረ መንግስት ሳንገነባ ቀርተን እንዲሁ በግጭት ውስጥ እንቆያለን።

ውድ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ይህንን ደብዳቤ የምንጽፈው ኢትዮጵያውያን አንዳንዶቻችን የጋሞ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የአኙዋክ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የኑየር ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የትግራይ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የኦሮሞ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የሲዳማ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የአማራ ልጆች ነን.... ሁላችንም ከአራቱም ማዕዘናት የመጣን የተለያዬ ቋንቋ ተናጋሪ ብሄር የመጣን የኢትዮጵያ ልጆች ነን።  እኛ ከተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ ማህበረሰብ የመጣን ኢትዮጵያውያን ዛሬ እነሆ ህብረት ይሻላል (better together) የሚለውን መሪ ቃል ይዘን የተበጣጠሰውን የኢትዮጵያውያንን ትግል ለማሰባሰብ ቆርጠን ተነስተናል። ከተለያዬ ብሄር የተገኘነው እኛ ኢትዮጵያውያን የአንድ እናት ልጆች ነን። ህብረታችንን ነው እናታችን የምንለው። ህብረታችን ሲጎዳ እናታችንን ጎዳን እንላለን። ስለዚህ እኛ የኢትዮጵያ ልጆች በአንድ በኩል የተበጣጠሰውን ትግል በማቀናጀት ለጋራው በጎነት (common good) ትልቅ ሃይል ሆኖ እንዲወጣ የምንጥረው ጥረት የሚቀጥል ሆኖ በሌላ በኩል ይህ በአብይ አህመድ የሚመራው ስርዓት ሲወገድ ሊመጣ የሚችለውን የመከፋፋል አደጋ ቀልብሶ ህብረትን ለመጠበቅ የሽግግር ፍኖቶች ላይ ለመስራት አበክረን እንሰራለን። ስለዚህ ህብረታችን ለሁለት ታላላቅ ግቦች ያስፈልጋል። አንደኛው ለተባበረ ትግል መሰባሰብ ሲሆን ሌላው ስርዓት ለመገንባት የኢትዮጵያን ትንሳኤና ሽግግር ለማሳለጥ የተሻለ ስርዓት ለመትከል ነው።

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን! ዛሬ ይህንን የህብረት ሀይል ቃል መልዕክት የምናስተላልፈው ኢትዮጵያውያን በአራቱም ማዕዘናት ያላችሁ በተለይም ወጣቶች ህብረት ይሻላል፣ ህብረት ይልቃል (better together) የሚለውን ሃይለ ቃል ከፍ አድርጋችሁ እርስ በእርስ መተሳሰብን እንድታዳብሩ፣ ህብረትን ከፍ እንድታደርጉ ለማበረታታት ነው። በተለያዩ የትግል አውድማ ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ህብረት ይሻላል የሚለውን መሪ ቃል ከፍ አድርጋችሁ በመያዝ የትብብር ጥሪ እንድታደርጉ ነው። ምሁራን፣ ተማሪዎች፣ ገበሬዎች፣ ሁላችን ኢትዮጵያውያን ህብረትን ከፍ እናድርግ። በልቦናችን ውስጥ እንጻፈው። በቤታችን ግድግዳ ላይ፣ በጊቢያችን አጥር ላይ እንጻፈው። ህብረት ይሻላል! Better together! ወቅቱ ክፉ ጊዜ ነውና ሁላችን ተጠጋግተን እንቁም፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን ህብረት፣ ህብረት፣ ህብረት እንበል።

Better together

Teko Hatanu !

እስፔተስ ሎኦ !

ዳቶ ቢር !

ህብረት ይጮኝኖ !

ብሐባር  ይሐይሽ !

ህብረት ይሻላል !

መልዕክት ካለዎ bettertogetherethiopia@gmail.com ያግኙን

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189331
 ህብረት ይሻላል (Better Together) ጥሪ ለኢትዮጵያውያን ሁሉ!
መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓመተ ምህረት

ምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ላይ የተሰየመችው ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካሉ እድሜ ጠገብ ሃገራት መካከል ቀዳሚ ሃገር ናት። ይህቺ ሃገር በአፍሪካ ክፍለ ዓለም ውስጥ እንደ በረሃ አበባ ብቻዋን በቅላ ብቻዋን ነጻ ሃገር ሆና የኖረች ብርቅዬና የነጻነት ምልክት ናት። በተለይ በቅኝ ግዛት የማቀቁ የአፍሪካ ሃገራት በሥሥት የሚያዩዋት እናታቸው ናት።

ኢትዮጵያ በረጅም ጊዜ ታሪኳ ውስጥ ከውጭ የሚመጣባትን ጥቃት ለማለፍ አያሌ ውጣ ውረዶችን ብታልፍም፣ ውስጣዊ አለመረጋጋቶች ብዙ ዋጋ ቢያስከፍሏትም በየዘመኑ የተፈጠሩ ልጆቿ “ህብረታችን ይበልጣል በሚል ሃያል መረዳት ሁል ጊዜም አብረው ታግለው አኩሪ የነጻነት ታሪክ ጽፈዋል። በአድዋ ተራሮች ላይ በአባቶቻችን ደም የተጻፈው ታሪክ ህብረታችን! ኢትዮጵያችን! እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝ የሚሉ ሃይለ ቃሎች ናቸው። ካራማራ ተራሮች ላይ የተጻፈው የዚህኛው ዘመን ታሪካችም እንደዚሁ ተመሳሳይ ሃይለ ቃል ያስተጋባል። ህብረታችን! ኢትዮጵያችን! እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝ የሚለው የአድዋው መሪ ቃል ነው ካራማራ ላይም የተደገመው። ለዚህ ነው የካራማራው ድላችን ዳግማዊ አድዋ እየተባለ የሚጠራው።

 

ኢትዮጵያ የእድሜዋንና የስልጣኔ ፈርቀዳጅነቷል ያህል ለመራመድ እንዳትችል ያደረጋት ነገር፣ በአንድ በኩል ከውጪ የሚነሱ ጦሮችን ለመመከት ዘወትር ዘብ ቆማ የቆየች ሲሆን በሌላ በኩል የውስጥ አለመረጋጋቶች ሃገረ መንግስቱን እገጭ እጓ እንዲል እያደረጉት ስለቆዩ ነው።

ከሁሉም የሚከፋው ግን ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ልጆች በህብረት የጻፉት ታሪክ አያሌ ቢሆንም በቅርብ ጊዜ ታሪካችን አዲስ ህገ መንግስት ስንጽፍ አብሮነታችንንና ህብረታችንን አቃሎ ልዩነቶቻችንን የሚያደምቅ ሆነ። ያቺን ሃያል ሀገር እንደ አንድ የማትከፋፈል ሃያል አገር ሳይሆን እንደ ዛኔ ጋባ ቤት፣ አንዳችን ባኮረፍን ጊዜ አፍርሰናት የምንሄድባት ጊዚያዊ ቤት አድርገን ሰራን። “ህብረት ይሻላል” የሚለው የኢትዮጵያውያን ሃይለ ቃል ተገስሶ ልዩነት ይልቃል ወደሚል ማህበረ ፖለቲካ መውረዳችን በአራቱም አቅጣጫ ያለንን ኢትዮጵያውያንን ሁሉ አንገት ያስደፋ የታሪክ ጠባሳችን ነው።

ይህ ልዩነትን የሚያጎላው አስተምህሮ ተቀይሮ ልዩነትም አንድነትም እርስ በርስ ሳይፈራረሱ የሚኖሩበትን የፖለቲካ ምህዋር ማቆም የሚገባን ቢሆንም ዛሬ ድረስ ልዩነቶች እየሰፉ ኢትዮጵያዊ ህብረታችን እየተሸረሸረ እየተሸረሸረ እየተሸረሽረ መጥቷል።

ሃገችንን ለዚህ አደገኛ የህብረት መሰረት መናጋት የጣላት ዋና ችግር አንዱ ይህ ህገ መንግስት ላይ የተጻፈው ህብረታችንን ፈራሽ ያደረገው ክፉ ሃሳብ ሲሆን በሌላ በኩል መንግስት የሚጠቀመው የከፋፍለህ ግዛ የአገዛዝ ስልት ነው። በተለምዶ ከፋፍለህ ግዛ የሚለው ፍልስፍና ከመቼውም ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ ሆኗል። የወቅቱ ጠቃላይ ሚንስትር  ዶክተር አብይ አህመድ ዋና የአገዛዝ ስልት ይሄ ነው። ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ህዝብ ለውጥ ፈልጎ ከፍተኛ ትግል ያደረገ ቢሆንም የቀድሞው የኢንሳ ድሬክተር የነበሩት አብይ አህመድ የኢትዮጵያውያንን ለውጥ በመጥለፍ ወደ ስልጣን በመጡ በወራት የመንግስትን መዋቅር የሚጠልፍ (state capture የሚያደርግ) የደህንነት መዋቅር ፈጥረው ስሙን ኮሬ ነጌኛ ብለው የኢትዮጵያውያንን የዴሞክራሲና የሽግግር ተስፋ አጨናግፈዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን እኚህ ሰው ወደ ስልጣን ከመጡ ማግስት ጀምሮ ችግሮችን በብልሃት ከመፍታት ይልቅ በኮሬ ነጌኛ ኮሚቴው አማካኝነት በሴራና በመጠላልፍ ዘዴ ስልጣን ላይ ለመቆየት በመሞከራቸው ኢትዮጵያውያን እርስ በርስ ተዋግተው በትግራይ ጦርነት ወቅት አያሌ ዜጎች ረገፉ፣ የብዙ ወገኖቻችን ቤት ተዘጋ፣ ረሃብና መፈናቀልን አተረፍን። ህብረት ይበልጥብናል፣ እኔ የመንድሜ ጠባቂ ነኝ የሚሉ ሃይለ ቃሎች በአባቶቻችን ደም የተከተበባቸው የአድዋ ተራሮች ላይ እርስ በርስ ተዋግተን አንገት የሚያስደፋ ታሪክ አስጽፈውናል። የኮሬ ነጌኛው መሪ አብይ አህመድ የትግራዩ ጦርነት ጋብ ባለ በማግስቱ ከአማራ ህዝብ ጋር ሌላ ጦርነት ውስጥ ገብቶ ይታያል። የዚህን ህዝብ ጥያቄ ለመፍታት ፖለቲካዊ መፍትሄ እንደመፈለግ በጦር ሃይል አንበርክኬ እገዛዋለሁ በማለቱ ዛሬ የአማራ ህዝብ በከፍተኛ ሁኔታ ከአብይ አህመድ አገዛዝ ጋር መራራ ትግል ላይ ይገኛል።

ኮሬ ነጌኛ የተሰኘው ህቡዕ ኮሚቴ ዋና ማዕከሉን አድርጎ የነበረው የኦሮሞን ህዝብ በመሆኑ ዛሬ ኦሮምያ ውስጥ ቅጥ ያጣ አስተዳደር፣ ዝርፊያና እንግልት፣ እስራትና ግድያ ቁም ስቅሉን እያሳየው ይገኛል። የኦሮሞ ህዝብ የሚያነሳው የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄ የጠለፉት ኮሬ ነጌኛዎች ይህ ህዝብ የሞተላትን ሃገሩን እያጠቁበት ይገኛሉ። ከሌላው ወገኑ ጋር እንዲጋጭና የስርዓቱ ዘበኛ እንዲሆን በኦሮምኛ ቋንቋ እየተናገሩ ሌት ከቀን ሊከፋፍሉት ይሞክራሉ።

የደቡቡ ወገናችንን ሁናቴ ስናይ አንዴ ጋሞን፣ አንዴ ወላይታን፣ አንዴ ሲዳማን ወዘተ. በየተራ የአብይ አህመድ መንግስት በኮሬ ነጌኛ አሰራሩ ቁም ስቅሉን እያሳየው ነው። ረሃብና መፈናቀል በዙር መከራውን እያሳየው ነው። አብይ አህመድ ስልጣን ላይ በመጣ በጥቂት ጊዚያት የጌዲኦ ወገኖቻችን ተፈናቅሎ መከራና ስቃይ ማየቱ አይዘነጋም። ጋምቤላ ውስጥ አኙዋክን ከኑየር ለማጋጨት የዚያን አካባቢ ህዝብ አንድነትና ሰላም በመንሳት የተባበረ የልማትና የሰላም ጥያቄ እንዳያነሳ ሁል ጊዜም ይጥራል። ይህ ክልል ከፍተኛ የተፈጥሮ ጸጋ ያለው ቢሆንም መንግስት ከልማት ይልቅ ግጭት ጠመቃ ላይ ተጥዶ በመኖሩ ዛሬ በዚህ ክልል ውስጥ ሰላም ወጥቶ መግባት፣ አምርቶ በምርት መደሰት የማይቻልበት ክልል ሆኗል። የሶማሌ ክልል ወገናችን በግጭትና በመገናቀል በረሃብ ይሰቃያል። በተለይ ባለፉት አምስት ዓመታት ግጭት፣ መፈናቀል፣ ረሃብ ያላገኘው የሃገራችን ክፍል ከቶ የትኛው ነው? የግጭትና የመፈናቀል መራራ ጽዋ ያልጠጣ ከቶ የትኛው ብሄር፣ ከቶ የትኛው ክልል ነው?

እውነት ነው ይህ ህዝብ በየፊናው ብዙ ዋጋ እየከፈለ ባለበት በዚህ ሰዓት እንደገና የስርዓት ለውጥ ለማምጣት ትግል ላይ ነው። ይሁን እንጂ ትግላችን በየብሄራችን የታጠረ በመሆኑ በአንድ በኩል የስርዓት ለውጥና የሽግግር ጊዜ ፈጥረን እፎይ ለማለት እንዳንችል፣ በጋራ ታግለን በፍጥነት የተሻለ ስርዓት ለመገንባት እንዳንችል አድርጎናል። በሌላ በኩል ይህ የተበጣጠሰ የትግል መስመራችን ድንገት የመንግስት መውደቅ ቢከሰት እንደገና በተባበር ሁኔታ አዲስ የሽግግር ስርዓት ለመፍጠር እንዳንችል የሚያደርግ ስጋትን ደቅኖብናል። በዚያም አለ በዚህ የኢትዮጵያውያን ትግል መከፋፈሉ የጠቀመው ስልጣን ላይ ላለው ኮሪ ነጌኛ ብቻ ነው። መከፋፈላችንና ትግላችን መበጣጠሱ የኮሬ ነጌኛ ኮሚቴ ህልም እስካሁን እንዲቆይ አድርጎብናል።

ኢትዮጵያውያን ጋሞዎች፣ አኙዋኮች፣ ኮንሶዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ትግራዮች፣ አማሮች ወዘተ እንደ ከበረ  እንቁ ይዘነው የነበረው አብሮነታችን፣ ህብረታችን እነሆ ዛሬ በብሄር ፖለቲካና በኮሬ ነጌኛ መዋቅር ምስጦች እየተበላና እየተሸረሸረ አገራችን አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ወድቃብናለች ። መንግስት ከፋፍለህ ግዛ የሚለውን ስልት ሲጠቀም ኢትዮጵያውያን ሊኖራቸው የሚገባው የትግል ስልት የመንግስትን ስልት የተቃረነ አደረጃጀት በመፍጠርና ተከፋፍሎ ለመገዛት አለመመቸት ነው።  ህብረትን የበለጠ ማጥበቅ ነው የትግሉ መጀመሪያ። ይህ የትግል ስልት ነው ጌም ቸንጀር የትግል ስልት የምንለው። በብሄር እየከፋፈለ ሊገዛን ያሰበውን ስርዓት ለመታገል ከተለያዬ ብሄር የመጣን የኢትዮጵያ ልጆች በአንድነት በህብረት ቆመን ከተነሳን ያን ጊዜ አሸንፈን ተነሳን ማለት ነው። የፖለቲካ አሸናፊ ሆነን ተነሳን ማለት ነው።

እኛ ኢትዮጵያውያን ህብረታችን የተጎዳው በመንግስት ከፋፍለህ ግዛው ስልት ብቻ ሳይሆን ከፍ ሲል እንደተጠቆመው አንዱ ስለራሱ ብቻ ሳይሆን ስለሌላው የሚያኖር ህገ መንግስት ስለሌለን ነው። ሃገር የሚባለው ስብስብ ሲቋቋም ዋና መተሳሰሪያ መርሆ መሆን ያለበት እንደ ብሄር ለራስ ብቻ ሳይሆን ስለሌላው መኖር ትልቅ ዋጋ የሚሰጠውና የህብረታችን መልህቅ ሆኖ መቀረጽ አለበት። አንዱ ስለ ራሱ ብቻ ሳይሆን ስለሌላውም የሚያኖረው ስርዓት ያልገነባ ሃገር ህብረቱ እንደምን አይፈርስም? እንዲህ ዓይነት ደካማ መተሳሰሪያ መርሆ ከጫንቃው ላይ የተጫነበት ህዝብ የገዛ ህብረቱ ሁልጊዜም አንካሳ ይሆናል።  የጋራ ተብሎ የተሰራለት ቤትም በአሸዋ ላይ የተሰራ የሰነፍ ሰው ቤትን የሚመስል ይሆናል። እንዲህ አይነት መተሳሰብ የጎደለው ህገ መንግስት የተጫነበት ህዝብ ጠንካራ የጋራ ተቋማትን ዘርግቶ ወደ ልማትና ወደ ሰላም እንደምን አድርጎ ወደፊት  መራመድ ይችላል? ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ዛሬ ስለ ህብረታችን በጥብቅ የምናስብበት ወሳኝ የታሪክ መታጠፊያ ምዕራፍ ላይ ነን። መዘናጋትና መታለል በቅቶ የህብረታችንን ስጋቶች ለመቅረፍ የምንነቃበት ወሳኝ ወቅት ላይ ነን። የተጫነንን ነገር ሁሉ ፈንቅለን ተነስተን ህብረት! ህብረት! ህብረት! የምንልበት ጊዜ ላይ ነን።  ለስርዓት ለውጥ የሚደረጉ ትግሎችን ሁሉ  እርስ በእርስ ለማያያዝ ደፋ ቀና የምንልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ነን።

ዛሬ በአማራ ክልል አካባቢ የተነሳውን የፋኖ ትግል ሁላችን ልንደግፍና አንድ ላይ ሆነን ይህንን ትግል የጋራ አድርገን ልንቀርጸው ይገባል። አንዱ ወገናች ትግል ሲጀምር ህብረትን ማሳየት፣ አብሮነትን ማሳየት ይገባል እንጂ አንዱ የአንዱን ትግል አይጥለፈው። የኦሮሞው ትግልና የአማራው ትግል፣ የትግራዩ ትግልና የደቡቡ ትግል፣ የጋምቤላው ትግልና የሃረሬው ትግል ሁሉ መደጋገፍና አንድ ትልቅ ጥላ ወደ መፍጠር ማደግ አለበት። ኢትዮጵያዊ ጥላ ፈጥረን ትግሎችንን አሰባስበን ህብረታችንን አጠናክረን እነሆ ከወደቅንበት ልንነሳ ይገባል። ፋኖነት አኙዋክነት፣ ኑየርነት፣ አማራነት፣ ኦሮሞነት፣ ጋሞነት፣ ወላይታነት፣ ቡርጂነት፣ ትግራይነት፣ ወዘተ ነው። ሁላችን ኢትዮጵያውያን ህብረታችንን እንደገና ለማደስ የተበላሸውን ሽግግር እንደገና ቀና ለማድረግ ህብረታችንን እንጠብቅ። ህብረት ይሻላል (better together) የሚለው ስሜት በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሃይለ ቃል ሆኖ ይግነን፣። መለያየትና እርስ በርስ ያለመናበብ የተሻለ ስርዓት እንዳንገነባ አድርጎናል። የዴሞክራሲ ትግላችንን እድሜውን አስረዝሞታል።የተለያዬና የተበጣጠሰ ትግል ውስጥ ገብተን አንድ አሸናፊ ሃይል ስልጣን ቢይዝም የረጋ ሃገረ መንግስት ሳንገነባ ቀርተን እንዲሁ በግጭት ውስጥ እንቆያለን።

ውድ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ይህንን ደብዳቤ የምንጽፈው ኢትዮጵያውያን አንዳንዶቻችን የጋሞ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የአኙዋክ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የኑየር ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የትግራይ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የኦሮሞ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የሲዳማ ልጆች ነን፣ አንዳንዶቻችን የአማራ ልጆች ነን.... ሁላችንም ከአራቱም ማዕዘናት የመጣን የተለያዬ ቋንቋ ተናጋሪ ብሄር የመጣን የኢትዮጵያ ልጆች ነን።  እኛ ከተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ ማህበረሰብ የመጣን ኢትዮጵያውያን ዛሬ እነሆ ህብረት ይሻላል (better together) የሚለውን መሪ ቃል ይዘን የተበጣጠሰውን የኢትዮጵያውያንን ትግል ለማሰባሰብ ቆርጠን ተነስተናል። ከተለያዬ ብሄር የተገኘነው እኛ ኢትዮጵያውያን የአንድ እናት ልጆች ነን። ህብረታችንን ነው እናታችን የምንለው። ህብረታችን ሲጎዳ እናታችንን ጎዳን እንላለን። ስለዚህ እኛ የኢትዮጵያ ልጆች በአንድ በኩል የተበጣጠሰውን ትግል በማቀናጀት ለጋራው በጎነት (common good) ትልቅ ሃይል ሆኖ እንዲወጣ የምንጥረው ጥረት የሚቀጥል ሆኖ በሌላ በኩል ይህ በአብይ አህመድ የሚመራው ስርዓት ሲወገድ ሊመጣ የሚችለውን የመከፋፋል አደጋ ቀልብሶ ህብረትን ለመጠበቅ የሽግግር ፍኖቶች ላይ ለመስራት አበክረን እንሰራለን። ስለዚህ ህብረታችን ለሁለት ታላላቅ ግቦች ያስፈልጋል። አንደኛው ለተባበረ ትግል መሰባሰብ ሲሆን ሌላው ስርዓት ለመገንባት የኢትዮጵያን ትንሳኤና ሽግግር ለማሳለጥ የተሻለ ስርዓት ለመትከል ነው።

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን! ዛሬ ይህንን የህብረት ሀይል ቃል መልዕክት የምናስተላልፈው ኢትዮጵያውያን በአራቱም ማዕዘናት ያላችሁ በተለይም ወጣቶች ህብረት ይሻላል፣ ህብረት ይልቃል (better together) የሚለውን ሃይለ ቃል ከፍ አድርጋችሁ እርስ በእርስ መተሳሰብን እንድታዳብሩ፣ ህብረትን ከፍ እንድታደርጉ ለማበረታታት ነው። በተለያዩ የትግል አውድማ ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ህብረት ይሻላል የሚለውን መሪ ቃል ከፍ አድርጋችሁ በመያዝ የትብብር ጥሪ እንድታደርጉ ነው። ምሁራን፣ ተማሪዎች፣ ገበሬዎች፣ ሁላችን ኢትዮጵያውያን ህብረትን ከፍ እናድርግ። በልቦናችን ውስጥ እንጻፈው። በቤታችን ግድግዳ ላይ፣ በጊቢያችን አጥር ላይ እንጻፈው። ህብረት ይሻላል! Better together! ወቅቱ ክፉ ጊዜ ነውና ሁላችን ተጠጋግተን እንቁም፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን ህብረት፣ ህብረት፣ ህብረት እንበል።

Better together

Teko Hatanu !

እስፔተስ ሎኦ !

ዳቶ ቢር !

ህብረት ይጮኝኖ !

ብሐባር  ይሐይሽ !

ህብረት ይሻላል !

መልዕክት ካለዎ bettertogetherethiopia@gmail.com ያግኙን

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189331

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...