Friday, June 30, 2023

"የሚወዱት እንደ ነበር የሚወዳቸዉም አለ"
ፀኃፊዉ  ስማቸዉን ያልጠቀስኩት በፅህፋቸዉ ባሰፈሩት መጣጥፍ ላይ ስለሚገኝ እና ጊዜም ጉልበትም ላለማጥፋት ነዉ ፡፡

መነሻየ ፀኻፊዉ  "የጥቅምት 2005 ዓ.ም.የአዲስ ራዕይ መፅሄት " ላይ ባካተተችዉ ሀተታ የክ/ዘመኑ ባለራዕይ እና አስደማሚ ስብዕና ባለቤት ባለችዉ ሟች የኢህአዴግ ሊ/መንበር  መለስ ዜናዊ (ለገሰ ዜናዊ) ምን ዓይነት ሠዉ ነበር በሚለዉ ርዕስ በአንደኛ እና ሁለተኛ አንቀት በተጠቀሱት እና በተለይም ሁሉንም የሚወድ ፤ሉም የሚወደዉ በሚሉት አረፍተ ነገሮች ነዉ ፡፡

በዚህም አስተያየታቸዉ ሟች የሚጠሉት እንጂ የሚወዱት ስለነበር አንድም ቀን ስለሚወዱት በአንደበታቸዉ ተናግረዉ ም ተስምተዉም እንደማይተወቁ ይገልፃሉ፡፡

ርግጥ ነዉ ስለ ሟች ልዩ እና አይተኬነት በዚህም የተነሳ በሠዉ ልጂ ታሪክ ሠዉ ያዘነለት ፤ዕንባ የተራጨለት ፍጡር የለም መባሉ ለምን ይዋሻል ማለታቸዉ የሚያስማማ ነዉ ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን የበደለዉን ፤የገደለዉን ቀርቶ  በስሜት እና በደም ፍላት ነፍሱን ያጠፋዉን አንብቶ እና ተፀፅቶ አፈር ሳይመልስ ምግብ ዉኃ አይልም ፡፡ ይህም ከአዳም እና ሄዋን የሚነሳ ሠዉ ለዚያዉም ለዓርያ ስላሴ ወደ ዚህች ዓለም በዕንግድነት መጥቶ ወደ መጣበት ሲመለስ ማክበሩ  "አስከሬን ይከበራል " በሚለዉ ተዉፊቱ ቆሞ ማሳለፍ ፤ አልቀሶ መሰናበት ሠባዊነትም ዕምነትም ይገኝበታል፡፡

ነገር ግን የሚጠሉትን እንጂ የሚወዱትን የመፅሄቱ አዘጋጆች ከየት አመጡት ለሚሉት ፀፊዉ ግር ያላቸዉ  የኢህአዴግ መንፈስ አስካሁን ተፅዕኖዉ በተከታዮች እና በአባሎች ስለመኖሩ ልብ ካለማለት ነዉ ፡፡

ዛሬም በሟች ራዕይ በሚከተሉ ሠዎች ቁም ስቅል በምታይ አገር እና አሳሩን በሚከፍል ህዝብ  የክ.ዘመኑ ሠዉ በሚሉ እና ከ.ዘመን ምን እንደሆነ በማያዉቁ ሰዎች በቁም ያመለኩትን ከሞት በኋላ ቢከተሉት ቢያመልኩት ከነበር ጣኦት አምላኪነት እንዴት ያንጊዜ ቀርቶ ዛሬ ላይ ሊወጡት ይችላሉ ፡፡

መወደዳቸዉን እና መዉደዳቸዉን ሁለንተናዊ አድረገዉ የወዳሉ ይወዳዳሉ ያሉ  የሚወዱት ነገር ነበር ማለታቸዉ ስህተት ሊሆን የሚችለዉ በምን መለኪያ ይሆናል ፡፡

ሟች ከምርጫ ‘ 97 ዋዜማ ፣ ዕለት እና ማግስት የተናገሩትን ለሚሰማ የሚጠሉት ከሚወዱት ቢበዛም የሚወዱት ነበር ፡፡ ከህዝብ ልብ ዉስጥ እንዳልሆኑ ሌላዉ ቢቀር ከዚሁ ምርጫ ማግስት  ከህዝብ ልብ መዉጣታችንን አረጋገጥን ብለዋል ፡፡ የራዕይ አዘጋጆች ግን ሁሉ የሚወዳቸዉ በሁሉ የሚወደዱ ካላሉ ከፊል አምልኮ ወይም ራዕይ የለም ለማለት ይመስላል ፡፡

በጥቅሉ  የመፅሄቱ አዘጋጆች የታዘዙትን እንጂ ዕዉነቱን የማድረግ ያኔ ቀርቶ ዛሬ ስለማይችሉ  ሁሉን ይወዳሉ ማለት ሲችሉ ሁሉ ይዳቸዋል ማለቱ ዕዉነት ሳይሆን ምትሃት ማስመሰል መልዕክት አስተላፊነት ሚና ብቻ ነዉ የነበረዉ ፡፡

ሆኖም የሚጠሉት ብቻ ላሉት ፀሃፊዉ  ሟች ሑሉንም ይጠሉ ነበር ባንል እንኳ የሚጠሉት ነበር ካልን የሚወዱት ነገር አልነበረም ማለት እንዴት ይቻላል ፡፡

ጨለማን የሚረግም ብርኃንን ይፈልጋል፤ ብርኃንን የሚጠላ ጨለማን ይመኛል እና ብዙ ጊዜ ሟች ስለ ኢትዮጵያ ፣ ስለ ዓማራ ህዝብ ፣ ስለ ባንዲራ፣ ስለ ቤ/ክርስቲያን ፣ያለፉትን የኢትዮጵያ ስርዓተ መንግስት ፣ መሪዎችን እና በጎ ስራዎች ማንሳት ፤ማዉሳት አይደለም አንድም ቀን ከማክፋፋት እና ማጥላላት ሳይወጡ  ከዚያ አስከ ዛሬ በማዉገዝ እና በመገዝገዝ የተለየ ነገር ከመናገር ዉጭ ማድረግ ሳይችሉ የነበረዉን ከመናድ ፤ከማካድ  ሳይሻገሩ ለንስኃ የተሰጣቸዉን ጊዜ ሳይጠቀሙ  ማለፋቸዉ የነበራቸዉ ዕይታ ከዚህ በተቃርኖ የሚመኙት /የሚሉት እንደነበር ከሚያመላክቱ ምሳሌዎች አንድ ህዝብ ወዳጂ  ጠላት ፤ ጨርቅ እና ወርቅ ፣ ዓማራ ለማኝ ሆኖ የመናፈቅ  ምኞት እና ፍላጎት፣ ባንዲራ ጨርቅ ነዉ፣ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጦር በትኖ  የፓርቲ ጦር ማቋቋም…..ከዚህ በግልባጭ  የሚወዱት ነገር የነበር ስለመሆኑ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባር አተናል፣ሆነናል  ….ዛሬም ላይ ዕዉን ሆኖ ዓለም ያወቀዉ ፀሃይ የሞቀዉ የገሀዱ ዓለም ዕዉነታ ነዉ ፡፡

አበዉ ክፉ ሞቶም ይገድላል እንዲሉ ዛሬም በሙት መንፈስ  ህዝብ ሲያልቀስ አገር ሲማስ እያየን ነዉ ፡፡

እናም "ይመስላል ካሉ ይወለዳል አይገድም "እና አንድ ሠዉ የሚጠላዉ ካለ የሚወደዉን በግልባጩ ይፈልጋል ፣ይመኛል ፣ ይባዝናል ….እናም የሚወዱት አልነበርም አንልም ካልን እኛም ከሠባዊነት ዉጭ ልዩ ፍጡር እና ዘላለማዊ ማድረግ ነዉ እና የሚወዱትስ ብዙ ብዙ ነበር ፡፡

የሚወዱትም የሚወዳቸዉም ነበር ሁሉንም ይወዱ ፤ሁሉም ይወዳቸዉ ነበር ማስታወቂያ እንጂ መታወቂያ ሆኖ ሠባዊነታቸዉን ይገልፃል ማለት ሠባዊነትን መርሳት ስለሚሆን የዚያን ጊዜ የመፅሄቱ አዘጋጆች መብት ቢሆንም ዉሸት ቢደራረብ ነጠላ ዕዉነት አይሆንም እና ቢችሉስ የሚወዱትም የሚጠሉትም ነበር ብለዉ ቢያስካክሉት አሁንም ዕድሉ አለ ፡፡

በዓለማችን በጎ ሰሪዎች ስራቸዉ ቶሎ ሲረሳ በበጎ ስረቸዉ ለዘላለም ሲነሱ ስለመኖራቸዉ የሚያጠራጥርም አይደለም ፡፡ ክፉም የሰራ እንዲሁ በስራዉ ልክ ለዘላለም በታሪክ እና በትዉልድ ጅረት ሲዘከር እና ሲመረመር ይኖራል  ምክነያቱም ክፉ ሠሪን ይቅር ማለት እንጂ ስራዉን መርሳት ስለማይቻል ፡፡ የሆነዉ ሆኖ ክፉን  ለራሱ በጎዉንም ስራዉ ይከተለዉ ብለን ከትናንት እየተማርን ወደ ፊት መጓዝ ይገባል ፡፡

"አንድነት ኃይል ነዉ "

 

Allen

 

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/184231
 

ሚያዚያ 17/2006 በድንገት ከያሉበት ተይዘው የታሰሩት የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞች በሐምሌ 08/2006 የተፃፈ ክስ ሐምሌ 11/2006 ‹ስለ ፀረ-ሽብርተኝነት የወጣውን አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ 3/2/ እና 4 ተላልፋችኋል› በሚል ክስ ቀርቦባቸው የነበረ መሆኑ አይዘነጋም፡፡ ክስ ከቀረበባቸው አስር ግለሰቦች መካከል አምስቱ ሐምሌ 01/2007 በድንገት ከሳሽ ክሱን አንስቻለሁ በማለቱ ከእስር የወጡ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ አምስት ግለሰቦች ላይ ግን ከሳሽ የመሰረተውን ክስ ቀጥሎበት ያቀረባቸው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ጉዳዩን የያዘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት መርምሮ በጥቅምት 05/2008 በዋለው ችሎት 1ኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ፣ 3ኛ ተከሳሽ ናትናኤል ፈለቀ፣ 5ኛ ተከሳሽ አጥናፉ ብርሃኔ እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ አቤል ዋበላ ‹የቀረበባቸውን ክስ መከላከል ሳይገባቸው በነፃ ይሰናበቱ› በማለት ብይን የሰጠ ሲሆን፤ 2ኛ ተከሳሽ በፍቃዱ ኃይሉ በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁ መሰረት የቀረበበትን ክስ ወደ መደበኛው የወንጀል ሕግ አንቀፅ 256/ሀ/ በመቀየር ክሱን እንዲከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር፡፡

በተሰጠው ውሳኔ መሰረትም ነፃ የተባሉት የዞን ዘጠኝ አባላት ከእስር የተለቀቁ ሲሆን በመደበኛው ወንጀል ሕጉ መሰረት ክሱን እንዲከላከል የተወሰነበት በፍቃዱ ኃይሉ በሃያ ሽህ በር ዋስትና ከእስር ተለቋል፡፡ ነገር ግን ‹በከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔ ቅር ተሰኝቻለሁ› በማለት ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ በታህሳስ 04/2008 የተፃፈ ይግባኝ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት ይግባኝ አቅርቧል፡፡ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤትም ከሳሽ በፅሁፍ አለኝ ያለውን ቅሬታ በቃል ሰምቶና የተከሳሾቹን ምላሽ በማዳመጥ ለነገ መጋቢት 20/2008 ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ምን ሊከሰት ይችላል?

በነገው የፍርድ ቤት ውሎ ችሎቱ መዝገቡን መርምሮ የጨረሰ ከሆነና ‹ተጨማሪ ማስረጃ አያስፈልገኝም› የሚል ከሆነ ሶስት የተለያዩ ነገሮች ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡

የመጀመሪያው ነገር ‹የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔ ተገቢ ነው› በማለት የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማፅናት የተከሳሾቹን ነፃነት ማስጠበቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ሊከሰት የሚችለው ጉዳይ ደግሞ ከመጀመሪያው በተቃራኒ የከሳሽ ቅሬታን ተቀብሎ የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ በመሻር ‹ተከሳሾቹ ክሳቸውን እንዲከላከሉ› የሚል ውሳኔ በመስጠት ተከሳሾቹን ዳግም ወደ እስር ቤት መመለስ ነው፡፡

ሶስተኛው የሚጠበቀው ጉዳይ የስር ፍርድ ቤት 2ኛ ተከሳሽን በፍቃዱ ኃይሉን የሚመለከት ሲሆን፤ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕጉ መሰረት አንድ ሰው በተመሳሳይ ጉዳይ በተመሳሳይ ጊዜ በሁለት የተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክሱን ሊከታተል ስለማይገባ ከሕግ አግባብ ውጭ በፍቃዱ ላይ የቀረበውን ይግባይ ውድቅ ያደርገዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

እኛም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ በማፅናት ይህ በመናገር ነፃነት ላይ የተሰነዘረን ጥቃት ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ይሰጠዋል የሚል ተስፋ አለን፡፡
https://amharic-zehabesha.com/archives/52623
The Horn of Africa States Entrepreneurship Should be Driving the Region
By Dr. Suleiman Walhad

June 30th, 2023

We have just rounded up the half-year 2023 and are moving on towards the second half of 2023. This would, of course, take place incrementally, in days and weeks and months and at the end, we might find ourselves still in the same situation we started with in the beginning of the year, with nothing really tangible having occurred in the Horn of Africa States region. The single state format would still be there, the terror groups in parts of the region would be operating as usual, the foreign parties would be as active as they were always in the region, the leaders of the region would be paying lip service to development and the populations of the region would continue to be suffering from the same old ills.

In a nutshell the economies of the region would still be weak, and uncertainties would continue to cloak development. Development would still be in the minds of people without nothing really happening and foreign assistance would still be one of the main pillars for the financial needs of the region, which would continue to make it the begging bowl, its leadership has made it to be. Many would still be blaming the ruling parties without pointing fingers at the opposition parties who play into the hands of the NGOs and world international organizations that thrive on the plight of weak countries and regions, which the Horn of Africa States presents itself to be.

The region does not pride itself with anything new, no innovations, no inclusiveness and being part of geopolitical tensions that have really nothing to do with it. These only erode away the region’s meagre resources and keep it distraught and disrupted economically and socially and, indeed, politically.  The region’s entrepreneurship, unlike those of other nations, still follows the old infrastructures of sticking to the known. They do not even explore the next village or town or region within the same country, let alone the business possibilities of the neighboring countries. Perhaps, some trade takes place, but where does it occur regional entrepreneurs taking hold of the region and serving the wide 157 million market?

The blame game continues to be on the politicians as if the politicians have magic wands. The do not! Businesspeople and entrepreneurs are equally to blame for the underdevelopment of the region as much as all other segments of the populations. What the region’s people do not realize is that no development would take place in the region unless there is a will on the part of the people of the region, no matter where they are stationed – in one country or another within the Horn of Africa States region.

It is where it becomes increasingly necessary for the entrepreneurs of the region to play better roles than they are currently doing. Why should the chambers of commerce and industries of the region not be meeting? And for that matter, why shouldn’t the bankers of the region and financiers of the region not meeting and why shouldn’t the industrialists of the region not be meeting, and why shouldn’t food producers not be discussing on ways of improving food production in the region? And there are many whys and questions?

What has happened to the entrepreneurial spirit of the region and why is it disappearing into other parts of the world, which has nothing to do with the region? We know that there are Horn African entrepreneurs operating in many other countries of the world. Should they not be putting something back into the region, giving jobs to the many unemployed youth of the region instead of just building residential units for themselves and their families, which do not add one iota to the economies of the region?

The fact that foreign media emphasizes always on the problems of the region and its internal conflicts should not put back the region’s entrepreneurs to investing in the countries of the region. The expectation of an entrepreneur to have smooth runs of business is a false proposition. No business runs without risks and the region, of course, has its own nature of risks in addition to others. But it also offers substantial opportunities for the intrepid investor and especially those from the region. Dealing with the weak legal systems is part of the proposition and being involved would only help improving the legal infrastructures. It is where practice makes perfection or close to perfection. If one does not operate in the region, it would be difficult to know where the weaknesses lie for correction and improvement.

The conflicts of the region and its internal confrontations as propagated by foreign media is not really as bad as they make it to be. The region’s entrepreneurs need to be forwarding the region’s aspirations in their own ways. Why shouldn’t there be a Somali bank operating in Ethiopia and vice versa and why shouldn’t there be leasing companies or Ethiopian’ shoe making industries operating in the region, instead of confining themselves in their own environments? Shouldn’t there be chains of coffee shops or regional malls spreading throughout the region?

The regional entrepreneurs should stop running away from the region and should trust the region. It offers many opportunities in terms of resource exploitation, manufacturing, finance and banking, insurance, services such as tourism and many others. The beautiful beaches and coasts of the region today appear to be empty of any regional maritime activities – no yachting, no commercial shipping, no fishing and, indeed, no chains of hotels attracting, at least, some of the millions of tourists that travel the world. Many of the region’s entrepreneurs, indeed, run like those foreign parties that make the region as untouchable as they can make it to be. The Horn of Africa States region and its entrepreneurs need to recalculate the economic dividends the region offers, which only require an innovative entrepreneurial spirit and, of course, cooperation and working together to develop the region, and take on the risks head on.

The Horn of Africa States region needs to embrace its own regional entrepreneurs. Likewise, the region’s entrepreneurs need to adopt and embrace their own region, despite the badmouthing of others from near and far. There is, indeed, a need for the entrepreneurial spirit of the region to permeate the region. Things cannot be left to chance. It is people who matter and make changes and the old folks of the region worked in that spirit. The new folks of the region should revert to those spirits of long bygone days and adopt themselves to new and modern ways of handling issues. The current fragmentation of the region in the political arena does not pose well for the region and business should be pulling the region together. It is where interests are created that link the region together for mutual and beneficial cooperation.

The more chaotic the region is or becomes, the more it is important and necessary for the region to take advantage of its entrepreneurial spirit to build a better future for the large youthful population of the region. Many work on further fragmenting the region, which plays into the hands of the foreign parties that exploit the region for their own interests. Unity and cooperation is the only way that such foreign interests can be checked on their tracks. The more fragmented the region becomes, the weaker it would be, and it is where it becomes necessary for the entrepreneurs of the region to create business and commerce among themselves to keep the region stronger and united.

 

 

 
https://zehabesha.com/the-horn-of-africa-states-entrepreneurship-should-be-driving-the-region/

Ethiopia has made an official request to join the BRICS bloc of emerging economies

Ethiopia has made an official request to join the BRICS bloc of emerging economies
By TESFA-ALEM TEKLE

Ethiopia has made an official request to join the BRICS bloc of emerging economies, the Ministry of Foreign Affairs said.

The BRICS is a five-member bloc comprising Brazil, Russia, India, China and South Africa.

"We have applied for membership and we expect BRICS to give us a positive response to the request we have made," Foreign ministry's spokesperson Meles Alem said on Thursday.

He added that Ethiopia would continue to work with international institutions that can protect its interests.

"As a country that has been a founding member of global institutions like the AU and the UN, and as we seek to guarantee our national interests, it is important to join blocs like BRICS," he said.

Ethiopia, with the second highest population in Africa, is one of the continent's fastest-growing economies, according to the International Monetary Fund,

In its latest World Economic Outlook, the IMF revised its earlier forecast of Ethiopia’s GDP in 2023 from $126 billion to $156.1 billion. But, its economy is less than half of South Africa - the smallest of the BRICS partner states.

Other countries that have sought to join the bloc include Egypt, Algeria and Bangladesh.

Argentina, Iran, Indonesia, Saudi Arabia and Turkey have also expressed interest in joining the alliance.

Last month, South African officials said over 19 countries had expressed interest in BRICS membership.

The bloc, initially named BRIC as an acronym of the member states, was formed in 2009. A year later, in 2010, the letter S was included when South Africa joined.

Pretoria is set to host the annual BRICS summit in August.
https://zehabesha.com/ethiopia-has-made-an-official-request-to-join-the-brics-bloc-of-emerging-economies/

Thursday, June 29, 2023

የመለስ ሞት የኢትዮጵያን ህዝብ ለምን አስለቀሰው? ‘አዲስ ራዕይ ጥቅምት 2005 ልዩ እትም’ን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ
 ክፍል 1

በደሳለኝ ቢራራ

መግቢያ

አቶ መለስ ዜናዊ በዋና አዘጋጅነት ሲፅፋት የነበረችው በራሪ መፅሔት ዛሬ ስለአዘጋጇ መታሰቢያ ተደርጋ ታትማለች። የዚች እትም ትኩረት የአቶ መለስ አስተምህሮዎችና ስራዎቸ እንዲሁም በግለሰብ ስብእናው ዙሪያ ነው። እናም “አቶ መለስ ማነው?” ሲሞትስ “በዓለም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ሚሊዮኖች ያለቀሱለትና በእንባ እየተራጩ የሸኙት ማን ቢሆን ነው?” ብሎ በማጠየቅ ይጀምራል። የመለስን ለቅሶ “በዓለም ታይቶ የማይታወቅ” የሚለውን ግርድፍ ድምዳሜ መሞገቱን ልዝለለውና አዘጋጆቹ ለጠየቁት ጥያቄ እራሳቸው ወደሰጡት መልስ እና ሀተታ ልቀጥል።

“እኛ የአዲስ ራዕይ ዝግጅት ክፍል አባላት ይህን ጥያቄ በማንሳትና መልሱንም በማፈላለግ መፃፍ የመረጥነው በመለስ ማንነትና ስብእና ላይ ብዥታ ስላለን አይደለም!” በማለት ስለመለስኮ አናውቅም ቢሉ ኖሮ ከሚመጣባቸው ዱላ እራሳቸውን ለመከላከል ይጥራሉ። በተለይ ‘ብዥታ አለብኝ’ ማለት አለማወቅን ብቻ ሳይሆን ጉዳዩን ወደ ፖለቲካ አፈንጋጭነት ሊተነተን የሚችል ችግር ስለሆነ የገባውንም ያልገባውንም ነገር ‘ፍንትው ብሎ ታይቶኛል፤ አብጠርጥሬ አውቀዋለሁ’ ለማለት ያስገድዳል። በህወኃት ወይም ኢህአዴግ ቤት እስካለ ድረስ አንድ ሰው ብዥታ ገጥሞኛል፥ አልገባኝም ማለት አይችልም። በጥርጣሬ ዐይን መታየትን የሚወድ አይኖርምና በግድም ቢሆን የተሞሉትን ትርክት ‘እውነት’ ብለው ተጠምቀውት እንደነበረ የሚያስተባቃ ሰውየው ሙቶም የሚገዛቸው መንፈስ ነበር። በመሆኑም አዘጋጆቹ ስለሚፅፉት ታሪክ እውነትነት ሳይሆን እራሳቸውን ከአደጋ ስለመከላከል አበክረው ማብራራታቸው የአገዛዙን ባህሪ አስረጅ ነው።

“መለስ በዘመን ላይ ተፅዕኖ ያሳረፈ የዘመን ውጤት” ነው በማለት ሀተታ የጀመሩት አዘጋጆች ለጥቀው “በአርአያ ስላሴ ተፈጠርን ከምንል ሰዎች ልቀውና መጥቀው ታሪካዊ ዓለማዊ ስብእና ያላቸው. . .” እያሉ ይገልፁታል። ወደ አምላክነት ያጋሽቡታል። እነዚህ ሰዎች የመለስን ታሪክ ሰውየው በህይወት እያለ አዘጋጁ ተብለው ቢሆን ኖሮ ‘ከስላሴም በላይ ልቀውና መጥቀው’ ሊሉ እንደሚችሉ ጥርጥር የለኝም።

ቀጥሎም ፍሬደሪክ ሄግልን በማጣቀስ እንደ መለስ አይነት ሰው “የዚህ አይነት ታሪካዊ ዓለማዊ ምጡቅ የታሪክ ስብእና ከአፍሪካ አይፈልቅም!” በማለት አጉራ ዘለል ድምዳሜ ይከምራሉ። ለዚህ የስብእና ደረጃ መለኪያ አድርገው ያስቀመጧቸው ጉዳዮችም አሉ። የአቶ መለስን ስብእናና ታሪክ ምን ያህል የገዘፈ እንደሆነ ለመግለፅም እንደተለመደው በሀገራችን ታሪክ ጉልህ ሚና የነበራቸውን ነገስታት በማጠልሸት ከጥቁር ታሪክ ላይ በነጭ ፅፈው ለመጉላት ይሞክራሉ።

“ግለታሪካቸውን በስንክሳርና በዜና መዋዕል ፀሐፊዎች እየታገዙ በመጻፍ ታሪካቸውን የሚያስጠርዙ መሪ አልነበሩም አቶ መለስ” ይላሉ አዘጋጆቹ ምስክርነት ሲሰጡ። በሀገሪቱ ያሉ የግልና የመንግስት መገናኛ ብዙሀን እንዲሁም በሀገራችን ፈቃድ ተሰጥቷቸው የሚዘግቡ የውጭ ሀገራት ሚዲያ አካላት በመለስ ዙሪያ ማይኮቻቸውን አጥረው የሚውሉትን በድሀ አጥር ላይ የተንዠረቀቀ የኮሽም ቅጠል ነው ሊሉን ይዳዳቸዋል። ከስንክሳርና ዜና መዋእል በበለጠ እነዚህ አዘጋጆች በአፍጢም እየተደፉ የሚጽፉበት አዲስ ራእይ አይበልጥሞይ? ከመለስ በላይ ታሪኩን ለማስጻፍ ድርጅቶች የከፈተስ ማነው? የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን በሙሉ የማን ዜና መዋዕል ሆኑና! ከህገመንግስት እስከ ቀበሌ መንግስታዊ ቡድን ቃለጉባኤ ድረስ የማን ስንክሳር ሆነና!

የመለስን ምጡቅነትና ስብእና ለመግለፅ ቃላት ከቁፋሮ ግኝት ተፈልገው የተገጣጠሙበት በሚመስል ደረጃ “ድንበርና ጠፈር ሳይከልላቸው፥ ዘር፥ ብሔር፥ ዕድሜ፥ ፆታ፥ ሐይማኖት፥ እምነት፥ ቦታ እና ጊዜ ሳይገድባቸው ለሁሉም ህዝቦች የሚመቹ፥ የሚጥሙና በልቡናቸውም ውስጥ የሚቀመጡ መሆናቸው ነው” ይላሉ። በእንተ እግዝትነ ማርያም መሀረነ ክርስቶስ!!! ሌላ ምን ይባላል?

ሀቁማ ቢያንስ ቢያንስ መለስ የብሔር ፖለቲከኛ ነው። የአንድ ብሔር ነጻ አውጭ ግንባር ሊቀመንበርም ነው። ስለዚህ ሰውየው ከሌሎች ሰዎች ሁሉ እጅግ በጣም የተለዬ ፍጡር ቢሆን እንኳ በዘር፥ በብሔር፥ በድንበር፥ በቋንቋ፥ ወዘተ የተገደበ አላማና ተልእኮ ነው የነበረው። በተጨማሪም ሰውየው እንደማንኛውም ሰው ደግሞ ሰው በመሆኑ በጊዜ እና በቦታ የተገደበ ተጽዕኖ ነው ያለው። ለዚህም ነው የሞተው፤ ለዛውም በድንጋጤ ነው የሞተው። አልፋና ኦሜጋ የሚመስላቸው ለአዲስ ራእይ አዘጋጆች ነው።  እንደዛ አይነት ሰው የለም። ሁሉም ሰው ዘላለማዊነትና ሁለኑባሬያዊነት የለውም። ሁሉም ሰው በአንድ ጊዜ በአንድ ቦታ ብቻ የሚገኝ ህይወቱም በተወሰነች ጊዜ ገደብ የተወሰ ነው። መለስ አጋንንት ካልሆነ በስተቀር ከሰዎች ተለይቶ በተመሳሳይ ሰአት በሁሉም ቦታ ሊገኝ አይችልም፤ ዘላለማዊም ስላልሆነ ሙቷል። ዘረኛ ስለነበረም በቋንቋ ከፋፋይ ስርአት ተክሏል። ክፉ ስለሆነም ህዝቦችን በብሔር ለያይቶ የሚገደሉበትን የጥላቻ ትርክት ስር እንዲሰድ አድርጓል። ጠባብ ጎጠኛ ስለሆነም ከትግራይ ለመጡት የራሱን ቋንቋ ተናጋሪ ሰዎች እንኳ በእኩል አይመለከትም። ቅድሚያ የሚሰጣቸው የአድዋ ተወላጅ፥ ከዛ በኋላ የእንደርታ ተወላጅ፥ ከዛ ቀጥሎ የአክሱም ተወላጅ እያለ ደረጃ ያወጣ ነበር። በተዘረዘረው የአዘጋጆቹ ቃል ሁሉ መለስ ይሰደብበታል እንጅ አይሞገስበትም። ለአንዱም መገለጫ የሚሆን ማስረጃ ማቅረብ አይችሉም።

ነገር ግን መለስን “ለሁሉም ህዝቦችና ብሔሮች የሚመቹ፥ የሚጥሙና በልባቸው የሚቀመጡ ናቸው” ያሉት ዋናውን ቁም ነገር ያዘለ ሁኖ አግንቸዋለሁ። ከሰውየው የሞት ዜና መነገር በኋላ ከተስተዋለው የህዝብ ለቅሶና ሲወረድ የነበረ ሙሾ ምን እንደሆነ እና ለምን እንደሆነ ለመመርመር አስችሎኛል። እናም ‘የመለስ ሞት ሀገርን በሙሉ ያስለቀሰው ምን አይነት ሰው ቢሆን ነው’ የሚለውን ለመረዳት ሀቁን እይታ አክለንበት ወደ አዘጋጆቹ ዲስኩር እንመለሳለን።

የመለስ ሞት የኢትዮጵያን ህዝብ ለምን አስለቀሰው?

አቶ መለስ በሞተ ጊዜ የተደበላለቀ ስሜት ተፈጥሮ ነበር። መጀመሪያ ላይ መሞቱን ማመን ከባድ ነበር። ምክንያቱም አቶ በረከት በሚሰጠው መግለጫ “ጠሚሩ በጥሩ ደህንነት ላይ ናቸው፤ በቅርቡም ወደ ስራ ይገባሉ” ምናምን እያለ ህዝቡን ያወናብደው ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ የወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ አይንና ጆሮ የነበረው ኢሳት ቴሌቪዥን የአቶ መለስን መሞት ዘግቦታል። በወቅቱ ማንኛውም የኢትዮጵያ ባለስልጣን ከሚሰጠው መግለጫ ይልቅ የኢሳት ዜና ተአማኒነት ነበረው። እውነትና ንጋት መገለጡ አይቀርምና የኢሳት ዜና የአቶ በረከትን መግለጫ ትቢያ ደፍቶበት፡ የአቶ መለስ መሞት እውን ሁኖ እሬሳው ወደ ሀገር ሲገባ ለማየት ቻልን። ነገር ግን የባለስልጣኑን መግለጫ ላለማቃለል ይሁን የኢሳትን ዜና ለማስተባበል ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት እሬሳው ወደ ሀገር የገባው ብዙ ቀናትን ቆይቶ ነበር። ሆኖም በዓለም ዙርያ ያሉ ትግሬዎች ሁሉ በመሪር ሀዘን አልቅሰዋል። አዲስ አበባም በየቀበሌው ድንኳን ጥለው፥ በየመንደሩ ጥሩንባ እየተነፋ እና በመኪና ሞንታርቦ ጭነው እየዞሩ በመልፈፍ ለቅሶ ጠርተዋል። በእየድንኳኖቹም አቴንዳንስ እየተያዘ (ለቅሶ የተገኘ ሰው ለመገኘቱ ማረጋገጫ ፊርማውን እያስቀመጠ) ተለቀሰ።

ይህ በአዲስ አበባ እና በትግራይ የተደረገው የለቅሶ መርሃግብር በሌሎቹም ሁሉም ክልሎችና ከተሞች እንዲከናወን በየቀጠናው የተቀመጡ የህወኃት እንደራሴዎች በአስፈጻሚነት ተሰማሩ። ለበታቾቻቸው የወረዳና ቀበሌ ተላላኪዎችም ህዝቡን ለመቀስቀስና ለማስተባበር አቅጣጫ ተሰጣቸው። እነዚህ ኃይሎች ተጣምረው ህዝብን የፍጥኝ በመያዝ የሚፈልጉትን ነገር ለማስደረግ ባላቸው ልምድ ልቅሶውን በየአደባባዩ እየተዞረና ደረት እየተደቃ ሲለቀስ በቪዲዮ ተቀርጾ ለታሪክ እንዲቀመጥና በቴሌቪዥንም ቀጥታ ስርጭት እንዲተላለፍ አደረጉ።

ብዙ ሰዎች ከልባቸው አለቀሱ። በርካቶች የቀበሌያቸውን፥ የጎረቤታቸውን፥ የቤተሰባቸውን እንኳን ሳይቀር ደህንነትና ጥቅም አሳልፎ በመስጠት በህወኃት ጥላ ስር ተጠልለው ኑረዋል። የመለስ ሞት ደግሞ የዚህ ጥላ መገፈፍ ነውና መድረሻ የሚያጡ ባህር የሚውጣቸው፤ ሲያስገድሉት የኖሩት ህዝብ በአንዴ ቆራርጦ የሚጥላቸው ስለመሰላቸው ሆዳቸው ባብቶ ነበርና አምርረው አለቀሱ።  በ8ኛ ክፍል ትምህርት በተለያዬ መስሪያ ቤት የክፍል ኃላፊዎች ተደርገው፥ በፎርግድ ማስረጃ ተቆልለው እንዳሉ ውስጣቸው ያውቃልና፥ ህወኃት ከወደቀ ባላቸው የትምህርት ዝግጅት በያዙት መደብ የሚያስቀጥላቸው የለምና፥ ከሞቀ ከተደላደለ ኑሮ ወደ ተጠያቂነትና ዘብጥያ ሲወርዱ ይታያቸው ነበርና፥ በእያንዳንዱ ግለሰብ ላይ ስለፈጸሙት ግፍና በደል ለፍርድ መቅረባቸውን ባሰቡት ጊዜ በየመንደሩ ጥቁር ተከናንበው ሙሾ እያወረዱ መሪር ለቅሶ አልቅሰዋል።

ሁለተኛው የአልቃሾች አይነት በሰፊ አውድ በጥልቀት የሚታይ ይሆናል። አቶ መለስ “አከርካሪውን ሰብሬ እንደ ሲጋራ ቁሮ ረግጨ ገድየዋለሁ፤ ቀብሬው ከመቃብሩ ላይ ቁሜአለሁ” ያሉት ህዝብ ገዳዩን ሲሞት አዬና አለቀሰ። ዕብሪተኛ ተመጻዳቂና በቀለኛ ገዳይን ከሁሉም በላይ የሚበቀል፥ የመግደል አቅም ስላለው የእግዚአብሔር ኃይል አለቀሰ። አንገቱን ደፍቶ የኖረ ህዝብ ቀና ብሎ አለቀሰ። ይህም ከልብ የመነጨ ለቅሶ ነበር።

ትግሬዎች እንደሚሉት “እግዚአብሔር ዘፈን ሲያምረው ትግሬን ያጠግባል፡ ለቅሶ ሲያምረው ደግሞ አማራን ይገድላል” እየተባለ የአማራን ሞት መሳለቂያ ከማድረግ አልፎ አማራን መግደል እግዜርን ማዝናናት እንደሆነ በሚያስረዳ ደረጃ ሞታችንን ያረከሱትን ሰዎችም ገድሎም ለቅሶን አሳዬን። በአማራ ሞት ብዙ ተዘብቷል፤ ብዙም ተተርቷል። ከሁሉም በላይ ግን የአማራ ሞት የአምላክ መደሰቻ ነው የሚል ትርጉም በስሪት ደረጃ መለማመዳቸው የህልውናችን ውጋት ነበር። የማን ሞት ከማን ሞት ያንሳል? ለቅሶ ለአማራ የተመደበ ማህበራዊ እውነታ ስለነበር ለቅሶን ለእኛ የመደበልን ሰው ሲሞት የእኛም ነባራዊ ሁኔታ ሊገለበጥ እንደሚችል ባሰብን ጊዜ ብዙዎቻችን የእምነት ተስፋ እንባ አስገንፍሎብናል። በርካቶችን ያስለቀሰው ለማልቀስ የተሰጣቸው ትእዛዝ ሳይሆን የዚህ ስርአት መልክ ሊቀየር ነው የሚል ተስፋ ነበር። የህዝቡን ለቅሶ በዚህ ልክ ካየነው ወደ አዘጋጆቹ ቀጣይ ጥያቄ ደግሞ እናምራ።

“መለስ ምን አይነት ሰው ነበር?”

ከህዝቡ ማልቀስ በመቀጠል አዘጋጆቹ በጥያቄ ማዳበር የፈለጉት የመለስ ማንነት የሚለቀስለትና ድጋሜ ሊገኝ የማይችል ምጡቅነቱን ነው። አዘጋጆቹ “መለስ ሁሉንም ሰው የሚወዱና የሚወዳቸው፡ ለሁሉም የሚመቹ፥ በሁሉም ዘንድ ከልብ የታተሙ ናቸው” ይሉታል።

ወደ እውነታው ሲገባ፡ አቶ መለስ ስለሚጠላው ነገር እንጅ ስለሚወደው ነገር አንዴም ተናግሮ አያውቅም። እራሱ ስለሚወደው ነገር ሳይናገር አዘጋጆች ከየት አምጥተው “የሚወደው ነገር” እንዳሉ፡ ለዛውም ግለሰቡ አምርረው የሚጠሉትን የኢትዮጵያን ህዝብ ይወዱት እንደነበር ለማብራራት መሞከር ‘ከባለቤቱ በላይ ያወቀ ቡዳነት’ ነው።   እነ አቶ መለስ የሚጠሉት ነገር እንጅ የሚወዱት ነገር ትኩረት ስለማይሰጠውም ነበር ከአይዲዮሎጅ እስከ ፖሊሲና ስትራቴጅ ድረስ የጥላቻ ማስፈጸሚያ መዋቅሮች፥ ስሪቶችና እሴቶች የተንሰራፉት።

አቶ መለስ በሚመሩት ህወኃት ድርጅታዊ ሰነድ (የትህነግ ማኒፌስቶ) በስፋት ተብራርቶ የተቀመጠው ስለሚጠሉት ነገር ነው። ስለሚወዱት ነገር የተጻፈ ምን አለ? ይህ ድርጅታዊ ጥላቻ በመለስና በጓዶቹም ልብ ተኮትኩቶ አድጎ፥ ታትሞ እንደኖረ ገሀድ ነው። በእርግጥ አዘጋጆቹ ይህን እውነት እንዲጽፉት አይጠበቅም፤ ቢበዛ እንዲዘሉት እንጅ። በመለስ ልብ ታትሞ ስለኖረው ጥላቻ እና የበቀል ሴራ እንጅ እርሱ በሌሎች ልብ ላይ ስለመታተሙ የሰነድም ሆነ የአካል ማስረጃ አያቀርቡም።

ስለዚህ መለስ ጥላቻን የጻፈ፥ ለበቀለ የዘመተ ገዳይና አስገዳይ አውሬ ከመሆኑ የተለዬ ስለስብእናው መጻፍ ይቸግራል። ሰውየው ለብዙ ሽህ ዘመናት አብሮ ይኖር የነበረን ህዝብ በዘር ከፋፍሎ፡ የሌላ ዘውግ ብሎ ያሰበውን አንጡራ እና መሬት በመዝረፍ የራሱን ዘውግ ለማበልጸግ የተጋ፥ የነጻነቲቱን ምድርና ህዝብ ደፍሮ ያስደፈረ፥ የባንዳ ውላጅ፥ የታሪክ አተላ ነው። የአቶ መለስ እና የነስብሀት ነጋ ቤተሰብ ከቅድመ አያቶቻቸው ጀምሮ ጠላትን እየመሩ ወደ መሀል ሀገር በማስገባት ኢትዮጵያዉያንን ሲያስጠቁ ስለነበር ማህበራዊ መገለል ተደርጎባቸው፤ ከነርሱ የተጋባም "ውሻ ይውለድ" ተብሎ ተገዝቶ መኖሩ የታሪክ እውነት ነው። የልጅ ልጆቻቸው ህወሃትን ከመሠረቱት ጀምሮ የበቀል አላማ የሰነቁ ናቸው። ከፍተኛ ጥላቻ አለባቸው። እራሳቸውንም ዝቅ አድርገው ነው የሚያዩት፥ ሊፍቁት የማይችሉት የባንዳ ልጅነት ነውና ምንነታቸው። እናም መቼም ቢሆን ኢትዮጵያዊነትን አይቀበሉትም።

የአቶ መለስ ባህሪም ከዚህ ታሪካዊ ዳራ ጋር የተሰናሰለና አመክንዮአዊ ግንኙነት ያለው ስለሆነ ነው ስለሚጠላው እንጅ ስለሚወደው ነገር እንዳይናገር ያደረገ፡ እድሜልክ አፍኖ ያኖረው ጥላቻ ቂምና የበቀል መንገድ የተከተለው። የባንዳ ታሪካቸው የሚፋቅ ይመስል ታዲያ ረጅሙን የኢትዮጵያ ታሪክ በአጭሩ ቁርጥ አድርጎ በመጣል ‘ተራራ ከሚያንቀጠቅጥ’ - የውሸት ጀብዳቸው የኢትዮጵያ ታሪክ እንዲጀምር ያስደረገ ደፋር ነው። ልብ ሊባል የሚገባው ነገር፡ እነዚህ የባንዳ ልጆች ኢትዮጵያን ጠላት ያደረጓትና ሁሌም የሚበቀሏት የአባቶቻቼውን መገለል ለመበቀል ነው። ነገር ግን ይህ የሁሉም ትግሬ አላማና ፍላጎት አልነበረም። በኢትዮጵያ ታሪክ ስማቸው በወርቅ የሚጻፍ አርበኛና አይተኬ የነበሩ የትግሬ ተወላጅ ጀግኖች አሉ። አሁን የትግራይ ህዝብ ታዲያ እውነተኛ ጀግኖቹን ትቢያ አልብሶ የባንዳዎቹን ልጆች መገለጫው ካደረገ ወይንም ደግሞ እነዚህ ሰዎች መላውን ትግሬ የእነርሱን ታሪክ ጭነው ሲጋልቡት "እሺ" ብሎ ህዝቡ ከተቀበለ ምን ይደረጋል?! እንደ አንድ ወገን የመምከር እድል ካለኝ፡ እባካችሁ ብዙሀን ትግሬወች በፈቃዳችሁ የባንዳ ልጆች ነን አትበሉ። በህወኀዓት አስተምህሮ ተመርታችሁ የበደላችሁትን አጎራባቻችሁን ህዝብ ክሳችሁና ይቅርታ ጠይቃችሁ ወደራሳችሁ ተመለሱ።

ማሳጠሪያ

በመለስ መታሰቢያ አዲስ ራዕይ መጽሔት ላይ የቀረበው ሀተታ ሲጠቃለል ስለመለስ ግላዊ ባህሪ፥ አስተዳደግና አመራር በተለይ ደግሞ ህዝብን፥ ብሔርን፥ ነጻነትን፥ ሐይማኖትን፥ ድንበርን ወዘተ ጠቅሶ በነዚህ ረገድ የሚጠቀስ አንድም በጎ ገጽታ ሊጠቀስ አይችልም። እራሱ ሰዎየው በሕይወት በነበረበት ወቅት ቢጠየቅ እንኳ አንድም ስለራሱ በጎነት የሚያነሳው ዋቢ የሚኖር አይመስለኝም። አዘጋጆቹ ግን የጎባጣ አሽከሮች ናቸውና የሟች ቤተሰብ ለሙሾ በሚመች መልኩ ግለታሪኩን መንግስታዊ ቅርጽ አስይዘው እንዲያዘጋጁት ባዘዟቸው መሰረት መልአክ አድርገው አቅርበውታል። አዘጋጆቹን ልምጥ ወይም አድርባይ ብዬ በተፈጥሯዊ ባህሪያቸው አልሰድባቸውም፤ ከስነምግባር አንጻር ስንኩልን “ስንኩል” አይባልምና። እነዚህ አዘጋጆች  በዋናነት እነ አቶ አገኘሁ ተሻገርና ተመስገን ጥሩነህ ያሉበት የብአዴን ክበብ፡ የሚገርሙኝ አሁንም መለስን ሲያመልኩ እንደነበረው ሁሉ የአብይ አህመድ ደቂቃን መሆናቸው ነው።

 

ክፍል 2 ይቀጥላል።

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/184206
ወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ ህወሃት በከለለው ግዛት ስር ይሁን ፣ (Status- Quo -Ante) ይከበር የሚለው ቅዥት እና ተረት ተረት
መግቢያ

እንግዲህ ግራ የተጋባ ፣ በሕግ የማይመራና ራሱን በተንኮል የተበተበ መንግስት እና ፓርቲ መዘባረቅ ፣ ሕዝብን ማደናበር እና የማይጨበጥ አካሄድ መከተል እና ተረት ተረት ማብዛት ስራው ነው።

የወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ ወደነበረበት አስተዳደር ይመለስ ሲባል ከመነሻው ማነው ያለአግባብ ፣ በማንአለብኝነት እና በኃይል  እነዚህን ግዛቶች ወደራሱ ግዛት ያጠቃለለው የሚል ጥያቄ ሲነሳ መልሱ በማያሻማ መልኩ “ህወሃት” የሚባል አጉራ ዘለል ፖርቲ መሆኑ የማይታበል ሃቅ ነው።

ይህን መነሻ አድርገን በያዝነው 19ኛው ምዕተ ዓመት የተከሰተን ታሪክ/Contemporary History/ ስናይ የአርጀንቲና መንግስት በእንግሊዝ አስተዳደር ስር የነበረችውን ፎክላንድ (The  Falkland Islands) ደሴት በጉልበት እና በኃይል ያዘ።

ደሴቲቷን የእንግሊዝ መንግስት ከመነሻው በአግባብ ነው ወይ ወሮ  የያዘው ? የሚለው አመክንዮ አጠያያቂ ቢመስልም አርጀቲና ግን ሕጋዊ መዓቀፍ ተከትላ ቦታውን ስላልያዘችው የእንግሊዝ መንግስት “አርጀንቲና ሆይ ግዛቴን ልቀቂ/ (Status Quo Ante ) ይጠበቅልኝ ብላ ጠየቀች።

አርጀንቲናም “ በደንበሬ ጥግ የሚገኝ ግዛቴ ነውና አለቅም” ብላ አሻፈረኝ አለች።

ከዚያ የእንግሊዝ መንግስት በኃይል ሆነ በዲፕሎማሲ አግባብነት ባለው መልኩ ደሴቷን መልሶ በቁጥጥር ስር አዋለ።

ይህን መሰረት አርገን የወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያን ጉዳይ ስናይ ገና ከጅምሩ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በዚህ የትውልድ የታሪክ ዘመን በ1984ዓ.ም. አካባቢ (Contemporary History) በአፍሪካ ታሪክ ታይቶ በማይታውቅ አኳሃን በአንድ አገር ክልል ያለን ግዛት በኃይል ቆርሶ እና (Annexed ) አድርጎ የያዘ አጉራ ዘለል ፓርቲ ቢኖር “ህወሃት” የሚባል ዘረኛ ፓርቲ ነው።

ይህን በመቃወም የወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ አባቶች ተቃወሙ ። ወልቃይት ፣ ጠለምት ፣ ራያ ወደነበረበት ግዛት ይመለስ ( Status Quo Ante) ይጠበቅ  ብለው ጠየቁ ። ህውሃት ግን “ ጀሮ ዳባ ልበስ” ብሎ እንደ አርጀንቲና “እሻፈረኝ “ አለ።

ጊዜው ደረሰ እና የወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ ነፃ አውጭ ጀግኖች ከ 27 ዓመት ቆራጥ ተጋድሎ በኋላ እርስታቸውን እንደ እንግሊዝ ግዛት ፎክላንድ ደሴት (Falkland Islands ) ግዛታቸውን በደም እና በአጥንት መስዋእትነት አስመለሱ።

በአንድ አካባቢ ግዛት ስር የነበረን እርስት ወደነበረበት ህግን ወይም ኃይልን ተጠቅሞ የማስመለስ አካሄድ (Status Quo Ante) ይሉሃል ይሄ ነው። አለቀ ደቀቀ ህግን ተክትሎ ለሃያ ሰባት ዓመት ወልቃይት፣ ጠለምት እና ራያ ወደነበሩበት ቦታ እንዲመለሱ መላው የአማራ ሕዝብ ጠየቀ ፣ ምላሽ ሲታጣ አሻፈረኝ ያለን ኃይል በሚገባው ቋንቋ ተነግሮት ጥያቄው እልባት አግኝቷል እንላለን።

ሌላው መላው ኢትዮጵያዊ ሊረዳው የሚያስፈልገው ጉዳይ ኦነግ /OLF/ እና ህውሃት /TPLF/ ከማን ነፃ እንደሚወጡ ግራ የሚያጋባ ቢሆንም “ነፃነታችን እንሻለን” ብለው መታገል ከጀመሩ ሃምሳ  ዓመታት በላይ ሊሆናቸው በእጣት የሚቆጠሩ ዓመታት ቀርቷቸዋል ። “ምን አይታ ዶሮ ምን አደረገች” እንዲሉ ይህ የነፃነት መሻት ዳርዳርታቸው ያቆጠቆጠው ከኤርትራ ነፃነት ግንባር ጥያቄ ማግስት ከራርሞ እንደሆነ ለማንም ግልፅ ነው።

የኤርትራ የነፃነት ጥያቄ “አግባብ ነው አግባብ አይደለም” የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ እና መሰረታዊ ምክንያቶች ቢኖሩም ዛሬ “ኢትዮጵያ” ብለን የሚንጠራትን ሃገር ኤርትራውያን “አቢሲኒያ” ብለው ለመጥራት የሚቀናቸው ሕዝቦች መሆናቸው ጥርጥር የለውም።

የሚገርመው ደግሞ “ህውህት” እና “ኦነግ ብልፅግና” የመገንጠል እና የነፃነት ጥያቄ አባዚያቸው ይታገስላቸው ይሆናል በሚል ህሳቤ የሃገረ መንግስትነት ሥልጣን ጀባ ቢባሉም አደናገሩን ፣ ግራ አጋቡን እና “ከድጡ ወደ ማጡ” ወሰድን ።

“ነገሩ ወዲህ ነው” እና “ ሲከፋሽ ወደ እኔ ሲመችሽ ወደ እሱ” እንዳለው ዘፋኙ “ከእኛ በላይ ኢትዮጵያዊነት ለአሳር” ፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም ወ.ዘ.ተ. ገለመሌ ፣ ገለመሌ ፣ ያደበሌ “ የሚሉውን ነጠላ ዜማቸውን ደረደሩልን ግራሞትን ፈጠረብን እና “አጃየብ” አልን።

የሚገርመው ስልጣን ከያዙ በኋላም ቢሆን ከህሊናቸው እና ከአቋማቸው ገሸሽ የማይለው ጥዮፍ ባህሪያቸው እና  የቂመኝነት ትርክታቸው እነ “ህወሃት” እና “የኦነግ ብልፅግና” “ከሃገሬ ኢትዮጵያ በፊት እኔን” የሚሉትን የአማራ እና መሰል ብሔር ብሔረሰብ ሕዝቦችን ማሰቃየታቸውን ፣ ማሰራቸውን ፣ መግደላቸውን እና እንደ ጠላት አርገው መፈረጃቸውን ቀጥለውበታል።

ይህን የከረፋ ድርጊታቸውን በ27 ዓመታት የህወሃት እና በአለፉት አምስት ዓመታት የመከራ ፣ የግፍ ፣ የዘረኝነት እና ፅንፍ የረገጠ የኦነግ ብልፅግና አካሄድ ላይ አይተንዋል።

የኤርትራ ፣ የትግራይ ምድር ቀይ ባህርን ይዞ (የሳባ ምድር)፣ ( የከለው ምድር) (ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት ፣ ጎንደር ፣ ጎጃም ፣ አማራ ሳይንት ፣ ቡግና ፣ የሽዋ ምድር ፣ ወሎን ይዞ ወ.ዘ.ተ.) ፣ በለው ( ኩናማ ፣ ኢሮብ) ፣ የአፋር እና ከዚህም ከዚያም የተበታተነው “የአገው” የአኩኖ -ወሳባ” ልጆችን አካቶ የሴሜናዊው የኢትዮጵያ  ምድር ተወላጆች ከፍጥረታቸው ጀምሮ  የኢትዮጵያ አስኳል እና መነሻ መሆናቸው የሚታወቅ ነው።

ነገር ግን ጥቂት በቀኝ ገዥ ባንዳ ጡት ስር ያደጉት ህውሃቶች (የሳባ ነገዶች) “ኢትዮጵያዊ አይደለንም” ብሎ መወክሸታቸው እና መጎረራቸው “ዐይንን በጨው ታጥቦ እውነታን እንደመካድ እና “የማያዛልቅ ፀሎት ለቅፅፈት” እንዳይሆንባችሁ” ብለን እንመክራቸዋለን።

ከአኩኖ -ወሳባ ወንድማቾች እና እህታማቾች ከበለው ፣ ከከለው ፣ ከሳባ ነገዶች ባሻገር ከአማራ ወንድሙ ከከለው ጋር እንደተዋሃደው አገው ሁሉ “ላካንዶን” እና “ኖቫ” የሚባሉ ወንድም ነገዶች በሳባ ፣ በከለው እና በበለው ነገድ ተውጠው የቀሩ ነገዶች እንደነበሩ ሊታወቅ ይገባል። ይህ ማለት ምን ማለት ነው? “አገው” ከአማራ ወንድሙ “ከከለው” እና “ከበለው” ጋር ተዛምዶ ፣ተቀላቅሎ እና ተሰባጥሮ ቢኖር ምንም ማለት እንዳልሆነ አስረግጠን እናስረዳለን።

ታሪክ /History/ ፣ /fable/ ተረት ተረት/ እና ዘመኑን የዋጁ ታሪኮች / Contemporary History/ እና አድምታው :

 

በሃገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ሰላሳ ዓመታት እያየነው ፣ እየሰማነው እና እየኖርንበት ያለው ተጨባጭ ሁኔታ በ “ታሪክ (History)  እና ተረት - ተረት (Fable)” መካከል ያለውን ልዮነት ሆንብለው በማፋለስ ፣ በማጣመም ፣ በማደነገር እና በመተብተብ ጥቅማቸውን ለማስጠብቅ የሚሹ ፣ የመስፋፋት ህሳቤ ያላቸው  እና በሥልጣን ኮረቻ ላይ ለመሰንበት የሚውተረተሩ ግለሰቦች ፣ ፖለቲከኞች ፣ መሰሬ ምሁራን  ፣ ተከፋይ የማህበረሰብ አንቂዎች ፣ አፍረተ ቢስ የበይነ-መረብ ባለሙያዎች  ወ.ዘ.ተ.  መላ ሕዝቡን እያደናበሩ ፣ እያምታቱ እና ግራ እያጋቡ ይገኛሉ።

ታሪክ /History/ :

ማለት ያለፉትን ዘመናት እውነታዊ ክሳቴዎች ጠቅለል አርጎ የሚያቀርብ ፣ የሰው ልጅ ከቅድመ አያቶቹ ተላልፈውለት አስታውሶ የሚዘግብበት ፣ ተመራምሮ ያገኝውን ፣ ያወቀውን ዕምቅ ሃሳብ ፣ በውስጡ አመላካች ወካይ ተቋማዊ ማስረጃዎችን አጠናክሮ እና አካቶ በማቅረብ እንዲሁም የክስተቶችን ሃሳባዊ ትርጓሜ ዘርዝሮ የሚያስቀምጥበት የዕውቀት ዘርፍ ነው። “History" is an umbrella term comprising past reliable events as well as the memory, discovery, collection, organization, presentation and interpretation of these events”

ትርክት -ተረት -ተረት- /Fables -Fictives / : ይህ ከእውነታ አዘል ታሪክ የተቃረነ መነባንብ ፣ ተረት የበዛበት ፣ ተናጋሪው ወይም ፀሃፊው የራሱን የይሆናል የግል ማህደር ፅሁፍ ፣ በጥላቻ ተነሳስቶ የሚዘላብደው እና ሰዎች በጋዜጣ ያሰፈሩትን እንቶ ፈንቶ  የያዘ ህተታ ማለት ነው -“ Fables are any chronicle, journal or diary, – thus almost any authored material – is bound to be unreliable since someone has written it (and he will have prejudices and opinions).”

 

ዘመኑን የዋጁ ታሪኮች / Contemporary History:

 

ይህ አይነቱ ታሪክ ደግሞ እንደ አውሮፓውያን እቆጣጠር ከ1946 መባቻ ጀምሮ ፣ ዓለም በጦርነት ታምሳ በነበረችበት ፣ ከቀዝቃዛው ጦርነት መባቻ እና እስከ አሁኑ ዘመን ያሉትን በተለይ በሕይዎት ያለው የዓለም ሕዝብ የኖረበትን ፣ የሚመሰክረውን እና የሚያረጋግጠውን ክስተታው ኩነቶች የሚያካትት ታሪክ ነው። “Contemporary History:  generally defined as beginning in 1946 and continuing to the present. In that time, the world has been almost continuously at war. The Korean War and the Vietnam War existed alongside the Cold War waged between the United States and the Soviet Union.”

 

ዘመኑን የዋጁ ታሪኮች / Contemporary History / : የወልቃይት ፣ የጠለምት እና የራያን ጥያቄ  ሊፈታ የሚያስችል እንድምታ እንዳለው  ስንመረምር :

ይህን መሰረት አድርገን ቀደመት የዓለም ሃገራትን ጆግራፊያዊ አሰፋፈር እና አሁን ያሉበትን የግዛት ይዞታ ስናይ በጣም የሚያስደምም ነገር እናያለን ። አሜሪካ የምትባለው ሃገር በአይርሾች ፣ በእንግሊዞችና በስኮትሾች እጅ ከመውደቋ በፊት የቀዮቹ ህንዳዊያን /Red Indians/ ሃገር ነበረች።  እነካሊፎርኒያ የአሜሪካ ግዛት አልነበሩም ነገር ግን በጦርነት ፣ በወረራ ይሁን በመልካም ፈቃድ አሜሪካ ስፖኒሽ (Spanish) ተናጋሪውን የካሊፎርኒያ ምድር አሜሪካ የራሷ ግዛት አድርጋቸዋለች።

እንግሊዝ አሁን ቦቲ ጫማ የምታከል ሃገር ከመሆኗ በፊት በቀኝ ግዛት ዓለምን ጠቅልላ ውጣ ስለነበር “ፀሃይ በታላቅዋ ብሪታንያ አትጠልቅም /The sun never set in England /” ተብሎ የተዘመረላት ሃገር ነበረች።

ይህን ያመጣሁት ግራ ነፈሰ ቀኝ ከአሁን በኋላ የዓለምን ከ1946 ማለትም በኢትዮጵያ ቀን አቆጣጠር ከ1938 ወዲህ ያለውን ፣ የምናውቀውን ታሪክ ፣ የእኛ አያቶች እና አባቶች  የነገሩንን ፣ የዘመኑ ትውልድ የሚያውቀውን እና የሚመሰክረውን ታሪክ መሰረት አድርገን መሄዱ እንድም ያስታረቃናል ፣ የጥንት ታሪኮችን እውነታ በጥናት አስረግጠን በማጣቀስ የመፍትሄ ሃሳብ ልናቀርብበት እንችላለን።

ይህን የምንጨብጠውን ፣ የምናውቀውን እና እየኖርንበት ያለውን ዘመኑን የዋጀ ታሪክ /Contemporary History/ መሰረት አድርገን እኛ ኢትዮጵያውያንን እያጋጨን ያለውን የመሬት የይገባኛል ጥያቄዎች የጥንት ታሪኮች /Ancient History/ እንዳለ ሆኖ ፣  በቅንነት ፣ ሃገራችን ትዳን ብለን ፣ በወል የጋራ ህሳቤ ፣ በንፁህ ህሊና ፣ ከስግብግብነት ነፃ በመሆን እና በመተማመን ብነጋገር ወደመፍትሄው እንደርሳለን ብለን እንሟገታለን።

የዘመኑን ትውልድ የታሪክ ጭብጥ እና እውነታ (Contemporary History)  አንፃፅረን ስናይ ወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ በአሁኑ ዘመን ትውልድ እይታ የጎንደር እና የወሎ አማራ ዕርስት መሆናቸው የማይታበል ሃቅ ነው።

 

ቁርጠኝነት የሚጠይቅ ተግባቦታዊ ውሳኔ :

የጋራ ታሪካችን በተመለከተ:

ከ3000 እና ከዚያ በላይ የሆነው የኢትዮጵያዊነት ታሪካችን ሃቅ ስለሆነ፣ በእውነተኛነት ማስረጃ የተደገፈ በመሆኑ እና በጋራ እንደ ሕዝብ  የሚያግባባን ጉዳይ ነውና የህውሃት እና የኦነግ ፅንፈኞችን የሚያደናግር ፣ ያላዋጣንን ፣ ኪሳራ እንጂ ትርፍ ያላስገኘልንን ትርክት /Fable/ አሽቀጥረን በመጣል በጋራ ታሪካችን ላይ ብንግባባ ።

ይህን መሰረት እድርገን ስንሞግት ኢትዮጵያ አለች ፣ ለወደፊቱም ትኖራለች ፣ የጋራ ቤታችን ናትና ተዋደን አንድ ሁነን እንኑርባት ብለን እንመክራለን ።

አዲስ አበባን : በተመለከተ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ከመሆኗ በፊት የተለያየ ስም እየተሰጣት ብትዘልቅም እወነታዊው የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ታሪኳ እየገነነ የመጣው በዚህ ትውልድ ታሪክ (Contemporary History) በምንለው ወቅት ከጎንደር የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ቀጥላ የተፀነሰች ከተማ በመሆኗ እና የከተማነት ገፅታ ያላበሷትም መላ ኢትዮጵያውያን በመሆናቸው አዲስ አበባ “የኢትዮጵያ እና የመላ ህዝቦቿ ዋና ከተማ ናት” የሚለው አካሄድ ያስማማናል።

ነገር ግን ብልጡ እና ዐይነ አውጣው “ህወሃት” ለኦነግ “አዲስ አበባ የኦሮሞ ናት ብየ እንደ ማሞ ቂሎ ብሸነግልው ፣ ወልቃይት እና ራያን የህወሃት ትግራይ ናት” ብሎ ከጎኔ ይቆማል እና ይከራከርልኛ የሚለውን “ የአይጥ ምስክሯ ድንቢጥ” የሚለውን አካሄዱ ገሸሽ አድርጎ በእራሱ ጥፋት የተሰውበትን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሕዝቦችን ወላጆች ቢያፅናና እና አካለ ስንኩል የሆኑትን እንዲያገግሙ ቢረባረብ እና በኢትዮጵያ የጋራ የሃገር ግንባታ ሂደት ላይ ቢያተኩር የሚዋጣ ይሆናል እንላለን።

ወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያን በተመለከተ ፣

ታሪክን ወደ ኋላ ጎተት አድርገን ስናይ ከአኩኖወሳብ ልጆች መካከል አንዱ የሆነው “የሳባ” ልጆች ነገድ ቀይ ባህርን ይዞ ከተከዜ ተሻግሮ ባለው ምድር ያለትን ሕዝቦች ከኩናማው ፣ ከአፋሩ ፣ ከኢሮቡ ወ.ዘ.ተ. ነገዶች ሌላ ያሉትን ሕዝቦች ያጠቃልላል ።

ከተከዜ ወዲህ ያለ ምድር የአኩኖወሳባ” ልጆች “የከለው” የአማራ እና በከፊል “የበለው” ልጆች ምድር መሆኑን ረጅሙ የኢትዮጵያ የታሪክ እውነታ አስረግጦ ይናገራል።

ይህን ጥንታዊ ታሪክ ለጊዜው ተግ እናድርገው እና የአሁኑን ትውልድ ታሪክ (Contemporary History) ማለትም ከ1938 ዓ.ም. ወዲህ ያለውን ሃቅ አዘል የሆነውን ታሪክ ተመርኩዘን ስናይ ወልቃይት ፣ ጠለምት በጎንደር ክፍለ ሃገር ፣ ራያ በወሎ ክፍለ ሃገር ስር ሁኖ ይትዳደር የነበር መሆኑ የማይታበል ሃቅ ነው።

እንግዲህ በጥንት ዘመን የነበሩ ቅድመ አያቶቻቸን እና ምንዥላቶቻችን ከሞት ተነስተው ለመመስከር ስለማይችሉ እና በሕግ እያታም ለምስክርነት ስለማይበቁ ፣ የቁም ምስክሮች ፣ የዚህ ዘመን ያሉ የታሪክ ውጤቶችን እና ጭብጦች በመሆናቸው ወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ አሁን ባሉበት የአማራ ክልል ተካለው መዝለቃቸው የግድ የሚላቸው ይሆናል እንላለን።

ማጠቃለያ :

እንደዚህ አይነት በሆደ ሰፊነት የሚሰጥን ሃሳብ መግዛት “ምከረው ፣ ምከረው ካልሆነ መከራ ይምከረው” እንዲሉ ፣ በዚህ በያዝነው ትውልድ ዘመን የሞትን ፣ የመፈናቀልን ፣ የኢኮኖሚ ድቀት እና ስደትን  የትግራይ ሆነ የኦሮሞ ሕዝብ በሚገባ ይገነዘበዋል ተብሎ ስለሚታሰብ ከወዲሁ የሚበጀውን ያደርጉ ዘንድ ምክራችን እንለግሳለን።

ይህ ሆኖ እያለ ሰሞኑን የህውሃት እና የብልፅግና ተከፋይ ማህበራዊ አንቂዎች ፣ ቲክ ቶከሮች (Tiktokers) እና ዮቲዮበርስ በተፈጥሮ የሌለበትን የአማራ ነገድ “ተስፋፊ” ፣ ወልቃይት ፣ ጠለምት እና ራያ የሌለ ተረት ተረት (Fable) እያነበነቡ  “በታሪክ የትግራይ” ነው ፣ “27 ዓመት በነበረበት ግዛት ስር ይሁን” እና “ (Status Quo Ante )” ይከበር እያሉ እየለፈፉ ማህበረሰቡ ወደ እማያባራ ጦርነት እንዲገባ ተግተው በመስራት ላይ ስለሆኑ ይህን ፅሁፍ በመከተል የሚመለከተው አካል ስራውን ቢሰራ ያዋጣል ፣ ሕዝብ እርስ በርሱ እንዳይፋጅ ይረዳል እንላለን።

በእልህ ፣ በስሜት በእውሸት ትርክት ተነሳስቶ እና በሌላው ስር ተወትፎ “  ከወሬ ያልዘለል ትርክት እየተረኩ ከእውነታ ውጭ የሆነ አጃንዳን አሳካለሁ ብሎ መወላገድ ትርፉ እልቂት ይጋብዛል እንላለን።

 

ተዘራ አሰጉ

ከምድረ እንግሊዝ።

 

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/184215
የመለስ ሞት የኢትዮጵያን ህዝብ ለምን አስለቀሰው? ‘አዲስ ራዕይ ጥቅምት 2005 ልዩ እትም’ን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ
 ክፍል 1

በደሳለኝ ቢራራ

መግቢያ

አቶ መለስ ዜናዊ በዋና አዘጋጅነት ሲፅፋት የነበረችው በራሪ መፅሔት ዛሬ ስለአዘጋጇ መታሰቢያ ተደርጋ ታትማለች። የዚች እትም ትኩረት የአቶ መለስ አስተምህሮዎችና ስራዎቸ እንዲሁም በግለሰብ ስብእናው ዙሪያ ነው። እናም “አቶ መለስ ማነው?” ሲሞትስ “በዓለም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ሚሊዮኖች ያለቀሱለትና በእንባ እየተራጩ የሸኙት ማን ቢሆን ነው?” ብሎ በማጠየቅ ይጀምራል። የመለስን ለቅሶ “በዓለም ታይቶ የማይታወቅ” የሚለውን ግርድፍ ድምዳሜ መሞገቱን ልዝለለውና አዘጋጆቹ ለጠየቁት ጥያቄ እራሳቸው ወደሰጡት መልስ እና ሀተታ ልቀጥል።

“እኛ የአዲስ ራዕይ ዝግጅት ክፍል አባላት ይህን ጥያቄ በማንሳትና መልሱንም በማፈላለግ መፃፍ የመረጥነው በመለስ ማንነትና ስብእና ላይ ብዥታ ስላለን አይደለም!” በማለት ስለመለስኮ አናውቅም ቢሉ ኖሮ ከሚመጣባቸው ዱላ እራሳቸውን ለመከላከል ይጥራሉ። በተለይ ‘ብዥታ አለብኝ’ ማለት አለማወቅን ብቻ ሳይሆን ጉዳዩን ወደ ፖለቲካ አፈንጋጭነት ሊተነተን የሚችል ችግር ስለሆነ የገባውንም ያልገባውንም ነገር ‘ፍንትው ብሎ ታይቶኛል፤ አብጠርጥሬ አውቀዋለሁ’ ለማለት ያስገድዳል። በህወኃት ወይም ኢህአዴግ ቤት እስካለ ድረስ አንድ ሰው ብዥታ ገጥሞኛል፥ አልገባኝም ማለት አይችልም። በጥርጣሬ ዐይን መታየትን የሚወድ አይኖርምና በግድም ቢሆን የተሞሉትን ትርክት ‘እውነት’ ብለው ተጠምቀውት እንደነበረ የሚያስተባቃ ሰውየው ሙቶም የሚገዛቸው መንፈስ ነበር። በመሆኑም አዘጋጆቹ ስለሚፅፉት ታሪክ እውነትነት ሳይሆን እራሳቸውን ከአደጋ ስለመከላከል አበክረው ማብራራታቸው የአገዛዙን ባህሪ አስረጅ ነው።

“መለስ በዘመን ላይ ተፅዕኖ ያሳረፈ የዘመን ውጤት” ነው በማለት ሀተታ የጀመሩት አዘጋጆች ለጥቀው “በአርአያ ስላሴ ተፈጠርን ከምንል ሰዎች ልቀውና መጥቀው ታሪካዊ ዓለማዊ ስብእና ያላቸው. . .” እያሉ ይገልፁታል። ወደ አምላክነት ያጋሽቡታል። እነዚህ ሰዎች የመለስን ታሪክ ሰውየው በህይወት እያለ አዘጋጁ ተብለው ቢሆን ኖሮ ‘ከስላሴም በላይ ልቀውና መጥቀው’ ሊሉ እንደሚችሉ ጥርጥር የለኝም።

ቀጥሎም ፍሬደሪክ ሄግልን በማጣቀስ እንደ መለስ አይነት ሰው “የዚህ አይነት ታሪካዊ ዓለማዊ ምጡቅ የታሪክ ስብእና ከአፍሪካ አይፈልቅም!” በማለት አጉራ ዘለል ድምዳሜ ይከምራሉ። ለዚህ የስብእና ደረጃ መለኪያ አድርገው ያስቀመጧቸው ጉዳዮችም አሉ። የአቶ መለስን ስብእናና ታሪክ ምን ያህል የገዘፈ እንደሆነ ለመግለፅም እንደተለመደው በሀገራችን ታሪክ ጉልህ ሚና የነበራቸውን ነገስታት በማጠልሸት ከጥቁር ታሪክ ላይ በነጭ ፅፈው ለመጉላት ይሞክራሉ።

“ግለታሪካቸውን በስንክሳርና በዜና መዋዕል ፀሐፊዎች እየታገዙ በመጻፍ ታሪካቸውን የሚያስጠርዙ መሪ አልነበሩም አቶ መለስ” ይላሉ አዘጋጆቹ ምስክርነት ሲሰጡ። በሀገሪቱ ያሉ የግልና የመንግስት መገናኛ ብዙሀን እንዲሁም በሀገራችን ፈቃድ ተሰጥቷቸው የሚዘግቡ የውጭ ሀገራት ሚዲያ አካላት በመለስ ዙሪያ ማይኮቻቸውን አጥረው የሚውሉትን በድሀ አጥር ላይ የተንዠረቀቀ የኮሽም ቅጠል ነው ሊሉን ይዳዳቸዋል። ከስንክሳርና ዜና መዋእል በበለጠ እነዚህ አዘጋጆች በአፍጢም እየተደፉ የሚጽፉበት አዲስ ራእይ አይበልጥሞይ? ከመለስ በላይ ታሪኩን ለማስጻፍ ድርጅቶች የከፈተስ ማነው? የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን በሙሉ የማን ዜና መዋዕል ሆኑና! ከህገመንግስት እስከ ቀበሌ መንግስታዊ ቡድን ቃለጉባኤ ድረስ የማን ስንክሳር ሆነና!

የመለስን ምጡቅነትና ስብእና ለመግለፅ ቃላት ከቁፋሮ ግኝት ተፈልገው የተገጣጠሙበት በሚመስል ደረጃ “ድንበርና ጠፈር ሳይከልላቸው፥ ዘር፥ ብሔር፥ ዕድሜ፥ ፆታ፥ ሐይማኖት፥ እምነት፥ ቦታ እና ጊዜ ሳይገድባቸው ለሁሉም ህዝቦች የሚመቹ፥ የሚጥሙና በልቡናቸውም ውስጥ የሚቀመጡ መሆናቸው ነው” ይላሉ። በእንተ እግዝትነ ማርያም መሀረነ ክርስቶስ!!! ሌላ ምን ይባላል?

ሀቁማ ቢያንስ ቢያንስ መለስ የብሔር ፖለቲከኛ ነው። የአንድ ብሔር ነጻ አውጭ ግንባር ሊቀመንበርም ነው። ስለዚህ ሰውየው ከሌሎች ሰዎች ሁሉ እጅግ በጣም የተለዬ ፍጡር ቢሆን እንኳ በዘር፥ በብሔር፥ በድንበር፥ በቋንቋ፥ ወዘተ የተገደበ አላማና ተልእኮ ነው የነበረው። በተጨማሪም ሰውየው እንደማንኛውም ሰው ደግሞ ሰው በመሆኑ በጊዜ እና በቦታ የተገደበ ተጽዕኖ ነው ያለው። ለዚህም ነው የሞተው፤ ለዛውም በድንጋጤ ነው የሞተው። አልፋና ኦሜጋ የሚመስላቸው ለአዲስ ራእይ አዘጋጆች ነው።  እንደዛ አይነት ሰው የለም። ሁሉም ሰው ዘላለማዊነትና ሁለኑባሬያዊነት የለውም። ሁሉም ሰው በአንድ ጊዜ በአንድ ቦታ ብቻ የሚገኝ ህይወቱም በተወሰነች ጊዜ ገደብ የተወሰ ነው። መለስ አጋንንት ካልሆነ በስተቀር ከሰዎች ተለይቶ በተመሳሳይ ሰአት በሁሉም ቦታ ሊገኝ አይችልም፤ ዘላለማዊም ስላልሆነ ሙቷል። ዘረኛ ስለነበረም በቋንቋ ከፋፋይ ስርአት ተክሏል። ክፉ ስለሆነም ህዝቦችን በብሔር ለያይቶ የሚገደሉበትን የጥላቻ ትርክት ስር እንዲሰድ አድርጓል። ጠባብ ጎጠኛ ስለሆነም ከትግራይ ለመጡት የራሱን ቋንቋ ተናጋሪ ሰዎች እንኳ በእኩል አይመለከትም። ቅድሚያ የሚሰጣቸው የአድዋ ተወላጅ፥ ከዛ በኋላ የእንደርታ ተወላጅ፥ ከዛ ቀጥሎ የአክሱም ተወላጅ እያለ ደረጃ ያወጣ ነበር። በተዘረዘረው የአዘጋጆቹ ቃል ሁሉ መለስ ይሰደብበታል እንጅ አይሞገስበትም። ለአንዱም መገለጫ የሚሆን ማስረጃ ማቅረብ አይችሉም።

ነገር ግን መለስን “ለሁሉም ህዝቦችና ብሔሮች የሚመቹ፥ የሚጥሙና በልባቸው የሚቀመጡ ናቸው” ያሉት ዋናውን ቁም ነገር ያዘለ ሁኖ አግንቸዋለሁ። ከሰውየው የሞት ዜና መነገር በኋላ ከተስተዋለው የህዝብ ለቅሶና ሲወረድ የነበረ ሙሾ ምን እንደሆነ እና ለምን እንደሆነ ለመመርመር አስችሎኛል። እናም ‘የመለስ ሞት ሀገርን በሙሉ ያስለቀሰው ምን አይነት ሰው ቢሆን ነው’ የሚለውን ለመረዳት ሀቁን እይታ አክለንበት ወደ አዘጋጆቹ ዲስኩር እንመለሳለን።

የመለስ ሞት የኢትዮጵያን ህዝብ ለምን አስለቀሰው?

አቶ መለስ በሞተ ጊዜ የተደበላለቀ ስሜት ተፈጥሮ ነበር። መጀመሪያ ላይ መሞቱን ማመን ከባድ ነበር። ምክንያቱም አቶ በረከት በሚሰጠው መግለጫ “ጠሚሩ በጥሩ ደህንነት ላይ ናቸው፤ በቅርቡም ወደ ስራ ይገባሉ” ምናምን እያለ ህዝቡን ያወናብደው ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ የወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ አይንና ጆሮ የነበረው ኢሳት ቴሌቪዥን የአቶ መለስን መሞት ዘግቦታል። በወቅቱ ማንኛውም የኢትዮጵያ ባለስልጣን ከሚሰጠው መግለጫ ይልቅ የኢሳት ዜና ተአማኒነት ነበረው። እውነትና ንጋት መገለጡ አይቀርምና የኢሳት ዜና የአቶ በረከትን መግለጫ ትቢያ ደፍቶበት፡ የአቶ መለስ መሞት እውን ሁኖ እሬሳው ወደ ሀገር ሲገባ ለማየት ቻልን። ነገር ግን የባለስልጣኑን መግለጫ ላለማቃለል ይሁን የኢሳትን ዜና ለማስተባበል ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት እሬሳው ወደ ሀገር የገባው ብዙ ቀናትን ቆይቶ ነበር። ሆኖም በዓለም ዙርያ ያሉ ትግሬዎች ሁሉ በመሪር ሀዘን አልቅሰዋል። አዲስ አበባም በየቀበሌው ድንኳን ጥለው፥ በየመንደሩ ጥሩንባ እየተነፋ እና በመኪና ሞንታርቦ ጭነው እየዞሩ በመልፈፍ ለቅሶ ጠርተዋል። በእየድንኳኖቹም አቴንዳንስ እየተያዘ (ለቅሶ የተገኘ ሰው ለመገኘቱ ማረጋገጫ ፊርማውን እያስቀመጠ) ተለቀሰ።

ይህ በአዲስ አበባ እና በትግራይ የተደረገው የለቅሶ መርሃግብር በሌሎቹም ሁሉም ክልሎችና ከተሞች እንዲከናወን በየቀጠናው የተቀመጡ የህወኃት እንደራሴዎች በአስፈጻሚነት ተሰማሩ። ለበታቾቻቸው የወረዳና ቀበሌ ተላላኪዎችም ህዝቡን ለመቀስቀስና ለማስተባበር አቅጣጫ ተሰጣቸው። እነዚህ ኃይሎች ተጣምረው ህዝብን የፍጥኝ በመያዝ የሚፈልጉትን ነገር ለማስደረግ ባላቸው ልምድ ልቅሶውን በየአደባባዩ እየተዞረና ደረት እየተደቃ ሲለቀስ በቪዲዮ ተቀርጾ ለታሪክ እንዲቀመጥና በቴሌቪዥንም ቀጥታ ስርጭት እንዲተላለፍ አደረጉ።

ብዙ ሰዎች ከልባቸው አለቀሱ። በርካቶች የቀበሌያቸውን፥ የጎረቤታቸውን፥ የቤተሰባቸውን እንኳን ሳይቀር ደህንነትና ጥቅም አሳልፎ በመስጠት በህወኃት ጥላ ስር ተጠልለው ኑረዋል። የመለስ ሞት ደግሞ የዚህ ጥላ መገፈፍ ነውና መድረሻ የሚያጡ ባህር የሚውጣቸው፤ ሲያስገድሉት የኖሩት ህዝብ በአንዴ ቆራርጦ የሚጥላቸው ስለመሰላቸው ሆዳቸው ባብቶ ነበርና አምርረው አለቀሱ።  በ8ኛ ክፍል ትምህርት በተለያዬ መስሪያ ቤት የክፍል ኃላፊዎች ተደርገው፥ በፎርግድ ማስረጃ ተቆልለው እንዳሉ ውስጣቸው ያውቃልና፥ ህወኃት ከወደቀ ባላቸው የትምህርት ዝግጅት በያዙት መደብ የሚያስቀጥላቸው የለምና፥ ከሞቀ ከተደላደለ ኑሮ ወደ ተጠያቂነትና ዘብጥያ ሲወርዱ ይታያቸው ነበርና፥ በእያንዳንዱ ግለሰብ ላይ ስለፈጸሙት ግፍና በደል ለፍርድ መቅረባቸውን ባሰቡት ጊዜ በየመንደሩ ጥቁር ተከናንበው ሙሾ እያወረዱ መሪር ለቅሶ አልቅሰዋል።

ሁለተኛው የአልቃሾች አይነት በሰፊ አውድ በጥልቀት የሚታይ ይሆናል። አቶ መለስ “አከርካሪውን ሰብሬ እንደ ሲጋራ ቁሮ ረግጨ ገድየዋለሁ፤ ቀብሬው ከመቃብሩ ላይ ቁሜአለሁ” ያሉት ህዝብ ገዳዩን ሲሞት አዬና አለቀሰ። ዕብሪተኛ ተመጻዳቂና በቀለኛ ገዳይን ከሁሉም በላይ የሚበቀል፥ የመግደል አቅም ስላለው የእግዚአብሔር ኃይል አለቀሰ። አንገቱን ደፍቶ የኖረ ህዝብ ቀና ብሎ አለቀሰ። ይህም ከልብ የመነጨ ለቅሶ ነበር።

ትግሬዎች እንደሚሉት “እግዚአብሔር ዘፈን ሲያምረው ትግሬን ያጠግባል፡ ለቅሶ ሲያምረው ደግሞ አማራን ይገድላል” እየተባለ የአማራን ሞት መሳለቂያ ከማድረግ አልፎ አማራን መግደል እግዜርን ማዝናናት እንደሆነ በሚያስረዳ ደረጃ ሞታችንን ያረከሱትን ሰዎችም ገድሎም ለቅሶን አሳዬን። በአማራ ሞት ብዙ ተዘብቷል፤ ብዙም ተተርቷል። ከሁሉም በላይ ግን የአማራ ሞት የአምላክ መደሰቻ ነው የሚል ትርጉም በስሪት ደረጃ መለማመዳቸው የህልውናችን ውጋት ነበር። የማን ሞት ከማን ሞት ያንሳል? ለቅሶ ለአማራ የተመደበ ማህበራዊ እውነታ ስለነበር ለቅሶን ለእኛ የመደበልን ሰው ሲሞት የእኛም ነባራዊ ሁኔታ ሊገለበጥ እንደሚችል ባሰብን ጊዜ ብዙዎቻችን የእምነት ተስፋ እንባ አስገንፍሎብናል። በርካቶችን ያስለቀሰው ለማልቀስ የተሰጣቸው ትእዛዝ ሳይሆን የዚህ ስርአት መልክ ሊቀየር ነው የሚል ተስፋ ነበር። የህዝቡን ለቅሶ በዚህ ልክ ካየነው ወደ አዘጋጆቹ ቀጣይ ጥያቄ ደግሞ እናምራ።

“መለስ ምን አይነት ሰው ነበር?”

ከህዝቡ ማልቀስ በመቀጠል አዘጋጆቹ በጥያቄ ማዳበር የፈለጉት የመለስ ማንነት የሚለቀስለትና ድጋሜ ሊገኝ የማይችል ምጡቅነቱን ነው። አዘጋጆቹ “መለስ ሁሉንም ሰው የሚወዱና የሚወዳቸው፡ ለሁሉም የሚመቹ፥ በሁሉም ዘንድ ከልብ የታተሙ ናቸው” ይሉታል።

ወደ እውነታው ሲገባ፡ አቶ መለስ ስለሚጠላው ነገር እንጅ ስለሚወደው ነገር አንዴም ተናግሮ አያውቅም። እራሱ ስለሚወደው ነገር ሳይናገር አዘጋጆች ከየት አምጥተው “የሚወደው ነገር” እንዳሉ፡ ለዛውም ግለሰቡ አምርረው የሚጠሉትን የኢትዮጵያን ህዝብ ይወዱት እንደነበር ለማብራራት መሞከር ‘ከባለቤቱ በላይ ያወቀ ቡዳነት’ ነው።   እነ አቶ መለስ የሚጠሉት ነገር እንጅ የሚወዱት ነገር ትኩረት ስለማይሰጠውም ነበር ከአይዲዮሎጅ እስከ ፖሊሲና ስትራቴጅ ድረስ የጥላቻ ማስፈጸሚያ መዋቅሮች፥ ስሪቶችና እሴቶች የተንሰራፉት።

አቶ መለስ በሚመሩት ህወኃት ድርጅታዊ ሰነድ (የትህነግ ማኒፌስቶ) በስፋት ተብራርቶ የተቀመጠው ስለሚጠሉት ነገር ነው። ስለሚወዱት ነገር የተጻፈ ምን አለ? ይህ ድርጅታዊ ጥላቻ በመለስና በጓዶቹም ልብ ተኮትኩቶ አድጎ፥ ታትሞ እንደኖረ ገሀድ ነው። በእርግጥ አዘጋጆቹ ይህን እውነት እንዲጽፉት አይጠበቅም፤ ቢበዛ እንዲዘሉት እንጅ። በመለስ ልብ ታትሞ ስለኖረው ጥላቻ እና የበቀል ሴራ እንጅ እርሱ በሌሎች ልብ ላይ ስለመታተሙ የሰነድም ሆነ የአካል ማስረጃ አያቀርቡም።

ስለዚህ መለስ ጥላቻን የጻፈ፥ ለበቀለ የዘመተ ገዳይና አስገዳይ አውሬ ከመሆኑ የተለዬ ስለስብእናው መጻፍ ይቸግራል። ሰውየው ለብዙ ሽህ ዘመናት አብሮ ይኖር የነበረን ህዝብ በዘር ከፋፍሎ፡ የሌላ ዘውግ ብሎ ያሰበውን አንጡራ እና መሬት በመዝረፍ የራሱን ዘውግ ለማበልጸግ የተጋ፥ የነጻነቲቱን ምድርና ህዝብ ደፍሮ ያስደፈረ፥ የባንዳ ውላጅ፥ የታሪክ አተላ ነው። የአቶ መለስ እና የነስብሀት ነጋ ቤተሰብ ከቅድመ አያቶቻቸው ጀምሮ ጠላትን እየመሩ ወደ መሀል ሀገር በማስገባት ኢትዮጵያዉያንን ሲያስጠቁ ስለነበር ማህበራዊ መገለል ተደርጎባቸው፤ ከነርሱ የተጋባም "ውሻ ይውለድ" ተብሎ ተገዝቶ መኖሩ የታሪክ እውነት ነው። የልጅ ልጆቻቸው ህወሃትን ከመሠረቱት ጀምሮ የበቀል አላማ የሰነቁ ናቸው። ከፍተኛ ጥላቻ አለባቸው። እራሳቸውንም ዝቅ አድርገው ነው የሚያዩት፥ ሊፍቁት የማይችሉት የባንዳ ልጅነት ነውና ምንነታቸው። እናም መቼም ቢሆን ኢትዮጵያዊነትን አይቀበሉትም።

የአቶ መለስ ባህሪም ከዚህ ታሪካዊ ዳራ ጋር የተሰናሰለና አመክንዮአዊ ግንኙነት ያለው ስለሆነ ነው ስለሚጠላው እንጅ ስለሚወደው ነገር እንዳይናገር ያደረገ፡ እድሜልክ አፍኖ ያኖረው ጥላቻ ቂምና የበቀል መንገድ የተከተለው። የባንዳ ታሪካቸው የሚፋቅ ይመስል ታዲያ ረጅሙን የኢትዮጵያ ታሪክ በአጭሩ ቁርጥ አድርጎ በመጣል ‘ተራራ ከሚያንቀጠቅጥ’ - የውሸት ጀብዳቸው የኢትዮጵያ ታሪክ እንዲጀምር ያስደረገ ደፋር ነው። ልብ ሊባል የሚገባው ነገር፡ እነዚህ የባንዳ ልጆች ኢትዮጵያን ጠላት ያደረጓትና ሁሌም የሚበቀሏት የአባቶቻቼውን መገለል ለመበቀል ነው። ነገር ግን ይህ የሁሉም ትግሬ አላማና ፍላጎት አልነበረም። በኢትዮጵያ ታሪክ ስማቸው በወርቅ የሚጻፍ አርበኛና አይተኬ የነበሩ የትግሬ ተወላጅ ጀግኖች አሉ። አሁን የትግራይ ህዝብ ታዲያ እውነተኛ ጀግኖቹን ትቢያ አልብሶ የባንዳዎቹን ልጆች መገለጫው ካደረገ ወይንም ደግሞ እነዚህ ሰዎች መላውን ትግሬ የእነርሱን ታሪክ ጭነው ሲጋልቡት "እሺ" ብሎ ህዝቡ ከተቀበለ ምን ይደረጋል?! እንደ አንድ ወገን የመምከር እድል ካለኝ፡ እባካችሁ ብዙሀን ትግሬወች በፈቃዳችሁ የባንዳ ልጆች ነን አትበሉ። በህወኀዓት አስተምህሮ ተመርታችሁ የበደላችሁትን አጎራባቻችሁን ህዝብ ክሳችሁና ይቅርታ ጠይቃችሁ ወደራሳችሁ ተመለሱ።

ማሳጠሪያ

በመለስ መታሰቢያ አዲስ ራዕይ መጽሔት ላይ የቀረበው ሀተታ ሲጠቃለል ስለመለስ ግላዊ ባህሪ፥ አስተዳደግና አመራር በተለይ ደግሞ ህዝብን፥ ብሔርን፥ ነጻነትን፥ ሐይማኖትን፥ ድንበርን ወዘተ ጠቅሶ በነዚህ ረገድ የሚጠቀስ አንድም በጎ ገጽታ ሊጠቀስ አይችልም። እራሱ ሰዎየው በሕይወት በነበረበት ወቅት ቢጠየቅ እንኳ አንድም ስለራሱ በጎነት የሚያነሳው ዋቢ የሚኖር አይመስለኝም። አዘጋጆቹ ግን የጎባጣ አሽከሮች ናቸውና የሟች ቤተሰብ ለሙሾ በሚመች መልኩ ግለታሪኩን መንግስታዊ ቅርጽ አስይዘው እንዲያዘጋጁት ባዘዟቸው መሰረት መልአክ አድርገው አቅርበውታል። አዘጋጆቹን ልምጥ ወይም አድርባይ ብዬ በተፈጥሯዊ ባህሪያቸው አልሰድባቸውም፤ ከስነምግባር አንጻር ስንኩልን “ስንኩል” አይባልምና። እነዚህ አዘጋጆች  በዋናነት እነ አቶ አገኘሁ ተሻገርና ተመስገን ጥሩነህ ያሉበት የብአዴን ክበብ፡ የሚገርሙኝ አሁንም መለስን ሲያመልኩ እንደነበረው ሁሉ የአብይ አህመድ ደቂቃን መሆናቸው ነው።

 

ክፍል 2 ይቀጥላል።

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/184206

Wednesday, June 28, 2023

የዲያስቦራን ዶላር ለመግፈፍ የአብይና ጓዶቹ አዲሱ ዘዴ | Hiber Radio
https://youtu.be/FZqFn6_7Ai4

የዲያስቦራን ዶላር ለመግፈፍ የአብይና ጓዶቹ አዲሱ ዘዴ | Hiber Radio
https://amharic-zehabesha.com/archives/184187
መርዶ በሞንታርቦ፡ የህወኃት ትሩፋት - በደሳለኝ ቢራራ
የህወኃትን የጭካኔ ልክ ቃላት ከሚገልጹት በላይ የአካል ማስረጃዎችና ሰለባ የተደረጉ ሰዎች ምስክርነት ተደርጓል። በታሳሪ አፍንጫ እስክርቢቶ በመኮርኮር መረጃ አውጣ ከማለት እስከ ጥፍር መንቀልና ብልት ላይ ማንጠልጠል በበርካታ አማራ ተወላጆች ላይ ተፈጽሟል። ህወኃት ጸረ-አማራ አይዲዮሎጅ ይዞ እንደተነሳ ድርጅት አማራን ማሰር፥ መግደልና ማሳደድ በስውርም ሆነ በይፋ ሲፈጽመው እንደ መደበኛ ስራ ተቆጥሮ የኖረ ስቃይ ነበር። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስተዋለ እንደመጣው ግን የትግራይ ህዝብንም ቢሆን በዲሞክራሲ መንገድ ስልጣን ይዘናል ለማለት ያህል “የምንወክለው ትግራይን ነው” ለማለት ያህል ይጠቀሙበታል እንጅ በመሰረታዊነት ህወኃት ለትግሬም ቢሆን ደንታ እንደሌለው በገሀድ መታየት ጀምሯል።

እስከዛሬ የሚታወቀው የህወኃትና የትግራይ ህዝብ ትስስር ‘ወያነ’ በሚል የጋራ እሴት ‘ህወኃት ትግራይ ነው፡ ትግራይም ህወኃት ነች’ በሚል ፍጹም አንድ መሆንን በሚያስረዳ መስተጋብር ይገለጽ ነበር። በህወኃት ተደጋጋሚ ስልጠናዎች የሰረጸ “ትግራይ ከሌለች ህወኃት የለም፤ ህወኃትም ከሌለች ትግራይ የለችም!” የሚል ጥልቅና አስፈሪ ትስስር ተሰርቷል። በመሆኑም የትግራይ ህዝብ ህወኃትን የሚያምንና በህወኃት የሚተማመን፥ ህወኃት አድርግ ያለውን ሁሉ ለማድረግ የማያቅማማ እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች ተረድተነዋል። ለምሳሌ፡ በሚሊየን የሚቆጠር የትግራይ ህዝብ የህወኃትን ጥሪ ተቀብሎ ሰሜን ወሎን፥ ዋግኸምራን፥ ደቡብ ወሎንና ደቡብ ጎንደርን ወረራ ሲፈጽም በከፍተኛ የጥላቻ በቀል የህዝብ ተቋማትን በማውደምና የግል ንብረቶችን በመዝረፍ ነው። የትግራይ ህዝብ የፈጸመውን ይህንን ወንጀል ለፖለቲካ ትክክልነት ብዬ በህወኃት ስም ብቻ አልሸበልለውም። ህወኃት የነበረው አጠቃላይ ምሊሻ፥ ልዩ ኃይልና ፖሊስ ተደምሮ 250 000 ገደማ ነው። አማራን የወረረው ግን እስከ ሁለት ሚሊዮን የሚደርስ (ምናልባትም አቅም የፈቀደለት የትግራይ ተወላጅ በሙሉ) በመዝመት ነው። የፓርቲ አባል ያልነበረ፥ ወታደር ያልሆነ፥ ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎና ፍላጎት የሌለው የህብረተሰብ ክፍል በጅምላ ተነስቶ አጎራባች ህዝብን ለመውረር ከዘመተ የማስተባበር ስራ የሰራው ድርጅት ብቻውን ተወቃሽና ተከሳሽ የሚደረግበት ምክንያት የለም።

ህዝቡ የተጋተውን የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ሰምቶ ከነባር ባህልና አስተሳሰቡ ውጭ የሆኑ ዘግናኝ ነውሮችን ፈጽሟል። መነኮሳትን ማስነወር፥ ዱዳ እንስሳትን መጨፍጨፍና የእንጀራ መሶብ ላይ መጸዳዳት የትግሬ ማህበራዊ አኗኗር እና ባህል መገለጫ አልነበረም። ባሳለፍነው ጦርነት የትግራይ ህዝብ ይህንን ነውር ነው የፈጸመው። ወንድማማችነትና ሰላም የሚናፍቃቸው ወገኖች እንደዚህ አይነቱን ሀቅ በዝርዝር እንዲነሳ አይፈልጉትም፤ ተድበስብሶና ወደ አንድ በጋራ የምናጥላላው አካል ተላኮ ህዝቡን ብጹዕ ማድረግ ነው የሚፈልጉት። ዳሩ ግን በውሸት ከሚመጣ ሰላምና ወንድማማችነት ይልቅ በቂም ተይዞ የሚዘገይ ፍትህ ይሻላል። አንድ ህዝብ በሌላ ህዝብ ላይ ላደረሰው በደል ህዝባዊ ፍትህ እና እርቅ ሳይደረግ የግል ጥቅምባሰገራቸውና የስልጣን ጥማት ባንገበገባቸው ፖለቲከኞች ተምታትቶ እንዲቀር ቢደረግ ጊዜውን ጠብቆ የሚነሳ የፍትህ ታጋይ ኃይልን ቀብሮ ማሳደር ነው የሚሆነው። እውነተኛ ፍትህና እርቅ ግን ዘላቂ ሰላምና አስተማማኝ ወገንነት እንዲኖር ያደርጋል። ያሳለፍነው ጦርነት በምንም ሁኔታ ቢቋጭ ከህዝቡ የሚቀረውን እዳ ሳልጠቁም ማለፍ ስለማልፈልግ ነው ይህን ያነሳሁት። በዋናነት ግን በዚህ አጭር ጽሑፍ ለማውሳት የምወደው ‘ህወኃት ስለትግራይ ህዝብ ምን ያስባል?’ ስለሚል ጥያቄ ነው።

የትግራይ ህዝብ “ሀዘኑ ሀዘኔ፤ ደስታውም ደስታዬ፤ ጥቅሙን ማስከበር አላማዬ፤ ክብሩ እሴቴ . . . ነው” ይላል? መሬት ላይ ከምናየው እውነታ እንደምንረዳው ህወኃት ለትግራይ፡ ብአዴን ለአማራ ህዝብ ከሆነው የተለየ ሁኖ አይታየኝም። ልዩነቱ ህወኃት በትግራይ ይወደዳል ፤ ብአዴን ግን በአማራው ዘንድ ይጠላል ብቻ ሳይሆን ‘የአማራ ህዝብ ብአዴንን ይጠየፈዋል’። ምክንያቱም ብአዴን ምንም ከአማራ ህዝብ ጋር የሚነካካ ነገር የሌለው ፍጹም ቆሻሻ የሆነ ስብስብ ነው። ብአዴን የሚያደርጋቸውን ማናቸውንም እንቅስቃሴዎች የአማራ ህዝብ በዐይነቁራኛ ነው የሚያያቸው፤ ምክንያቱም ባንዳ ከሀዲ፥ አድርባይና ተላላኪ የደናቁርት ስብስብ መሆናቸውን ህዝቡ ያውቃል።

ህወኃት ግን በግልጽ በመንግስታዊ አቋም ደረጃ “ሁለት ሚሊዮን ትግራዋይ ሰውተን ወደ ስልጣናችን መመለስ ከቻልን ጥሩ ነው” የሚል መግለጫ ሲሰጥ ህዝቡ “እንበር ተጋዳላይ!” እያለ በዘፈን ተቀብሎታል። የትግራይ ህዝብ ህወኃትን በስልጣን ለማቆየት ለመሰዋት ፈቃዱን የሰጠው እራሱ ነው። አስቀድሞ ህወኃት አቋሙን ሲገልጽ ህዝቡ መልስ መስጠት ይችል ነበር። ቢያንስ ቢያንስ “እናንተን በስልጣን ለማቆየት አይደለም የምንሰዋው፤ ትግራይን ነጻ ለማውጣት አላማ አድርጋችሁ ከታገላችሁ በኋላ በስልጣን ሰላሳ ዓመት ኖራችኋል፤ አላማችሁን የት አደረሳችሁ?” ብሎ መጠየቅ ይጠበቅበት ነበር። ህዝቡ ግን ከመጠየቅ ይልቅ ማገዶ ለመሆን ነበር የተዘጋጀው። ተማገደ አለቀ። በዚህም ብቻ በበቃ።

ህወኃትን በነበረው ማንነት በጣሳቸው ህጎችና ባሉበት በርካታ ተጠያቂነቶች ምክንያት ከፓርቲነት የሰረዘችውን የምርጫ ቦርድ ኃላፊ ወ/ር ብርቱካን ሚደቅሳ ስልጣን እንድትለቅ መደረጉን ሪፖርተር ጋዜጣ ሰኔ 18 ቀን 2015 በወጣው እትሙ አትቷል። ተሰርዞ የነበረው “የህወኃት ህጋዊ ሰውነት እንደገና እንዲመለስ መጀመሩ. . . “ ይላል ርዕሱ። ህወኃት ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ የትግራይን ህዝብ ጨፍጭፎ በመጨረሻም የኦነግ ተለጣፊ ሁኗል። አሁን ህወኃት ከኦነግ ጋር የጫጉላ ሽርሽር ላይ ነች። በትልልቅ ሞንታርቦ አዲስ አበባ ላይ “በሎም!” እየተባለ በውስኪ እጅ እየታጠቡ ነው።

ታዲያ ስልሳ አመት በነጻ አውጭነት ብራንድ፥ ሰላሳ አመት በስልጣን የኖረውን ህወኃት “ወያናይ መስመርና፡ አፈር ልሰን ተነሳና” ማለት የትግራይን ህዝብ ንቃተ ህሊና አያስጠይቅም? አሁንስ የትግራይ ህዝብ የተገለጸለት ነገር ይኖር ይሆን? ህዝባዊ አንድምታውስ በምን ምልክት ወይም ድርጊት ሊገለጽ ይችላል? ከሁሉም ነገር በበለጠ የሚገርመው ደግሞ ህወኃት በዚህ ጦርነት ሰለባ ያስደረጋቸውን የህዝቡ አካላት ለቤተሰባቸው መርዶ ያደረገበት መንገድ ነው። የሟቾችን መርዶ እንደ ህዝባዊ በኣላት ወይም እንደ ሰርግ ትልልቅ ሞንታርቦዎችን ሰቅሎ እንደ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሟቹን ስም እየጠራ፡ የሟች ቤተሰብ በድንጋጤና በለቅሶ ሲንፈራፈር ገመናውን ቪዲዮ ቀረጻ እያደረገ ነው። በአማራ ልማዳዊ አገላለጽ እጅግ የከፋ ነገር ሲያጋጥመን “አረ ለጠላቴም አይስጠው” እንላለን። እንደዚህ አይነቱን ለማለት ነው።

 

ፎቶ፡ https://twitter.com/KeyAstra/status/1673400818806956047/video/1
https://amharic-zehabesha.com/archives/184184
The Horn of Africa States Beyond the Last Century Histories
By Dr. Suleiman Walhad

June 27th, 2023

The Horn of Africa States region consisted of three countries in 1960, namely Somalia, Ethiopia and Djibouti, although Djibouti was then French Somaliland. Currently it also includes Eritrea which broke away from Ethiopia in 1993 to make the region four countries. All, in essence, have been shaped and erected through European colonialism, which to a large extent determined the legacies of the region todate. Those memories of the past and European colonialism are fading, albeit slowly and the region’s people need to move away from those thought processes and blame games. The region currently is managed by its own people, who should be laying down the groundwork for the future of the region in terms of thought processes, education and social issues and economic development. The times of blaming the Europeans for the past and present dilemmas of the region, are surely being relegated to old memories which are being forgotten. The youthful population of the region do not even remember much of the military regimes of the region some thirty years ago let alone the actions and activities of Europeans earlier.

The region’s fate, thus, becomes more and more, a responsibility of its people and leadership, no matter what was inherited from its colonial past. No doubt the old colonising countries still need the region and whatever it offers in terms of resources or other geopolitical considerations and they, indeed, have missions and have strategies for implementing these missions.

What does the region have in place for dealing with those countries and, indeed, the new powers that have replaced the old ones? There are now the United States of America and China and Russia and even small regional powers such as the GCC countries and Turkey, and, indeed, old historical relations which seems to have soured lately such as Egypt.

To know the evolving situation of the region is not only the preview of the leadership but also those of academia, opposition parties and civic societies, educational institutions, and media of the region. It is the collective approach of the societies of the region to address the new realities, for they affect not only the economies of the region but its stability and security and hence peace and life. It is where it becomes necessary for the region to devise its own survival strategies, in this uncertain future, which appears to be even more clouded than the past.

The HAS region is strategically located and has always attracted non-regional parties. It will continue to do so tomorrow and the future behind it. Such non-regional parties included traders and those who wanted to exchange commerce with it. Others were military and naval related projects of others, particularly in the last century. This continues under the new powers that be in the world. The Indo-Pacific agendas of major powers seem to be now affecting the region. It is, indeed, being drawn into that wider competition among major powers and also regional powers through their growing military and naval presence in the region. It is where there is a necessity for the region to come together and work out strategies together to address these oncoming challenges.

The new external security frameworks of the Horn of Africa States constitute major challenges for the region. If the Horn is not able to manage the growing presence and regional interests of foreign military actors, it risks increased fragmentation and/or becoming a part of wider international security competition, over which it is likely to have little influence. The region could even become the venue for the sort of destabilizing external competition last seen during the cold war. The international political and economic shifts that are driving the new external security dynamics of the Horn region are, at the same time, also a major opportunity, bringing new investments, infrastructure and connections to world markets. Taking advantage of the opportunities and managing the challenges will, however, require a significant shift in the approach of the Horn countries to their relations with external security actors. Currently the region acts on an individual and single-state format. A collective approach would be better.

Collectively, the region can create together an instrument or institution that represents the region in new partnerships with those foreign parties that do not compromise the future of the populations and socio-political development of the region. The region need not dug deep its heels but must work to understand the needs of others and work with the flow of events such that it takes advantage of whatever direction it takes.

What can the region offer collectively? The region has access to a large maritime resource where ports of differing kinds can be built and where hence food production in terms of maritime food sources can be developed. It can also provide accessibility to cargo, commercial and naval and military movements of the world in the geostrategic location of the region. It offers a significantly large market of a youthful population that can either be consumers and producers at the same time at reasonable costs. It is a region which dips to a deep historical background which would assist its youth work on strategic technologies given the right opportunity. The region can also produce food for its growing population and for others, noting that it identified grains and seeds for food and tamed animals such as camels and donkeys and its own brands of cattle both for food and burden. The region can also develop as a beautiful tourist attraction, offering its beautiful weather, which is reasonable year-round and its blue pristine blue seas, again year-round.

The region has gone through tumultuous periods in the past eighty years and is, therefore, ready for settling down, leaving behind the miseries and disasters of wars and civil struggles. Those who take advantage of the opportunity at hand and create partnerships with the region would gain better footholds than those who would come later. Is the region ready for such strategic partnerships?

There are still forces of evil and forces of goodwill at play in the region and the forces of goodwill seem to be gaining the upper hand at present. There is a shift in gaze and attitudes, although still many who keep putting down their own folk still abound in the region. The region does not need further splintering, as it was already divided by the Europeans of the nineteenth century into its currently four countries although it could have been more, had it not been for the foresight of some of its people to bring together parts of the region. The old colonial legacies are dying away and fading into obscurity, and the people of the region should be working on forging new paths for development and economic growth.

 
https://zehabesha.com/the-horn-of-africa-states-beyond-the-last-century-histories/

Tuesday, June 27, 2023

https://youtu.be/_fZxl5aWbSA

የወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ስንብት፥ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ''እኔ የለሁበትም '' አለ
https://amharic-zehabesha.com/archives/184107
ኢዜማና የመግለጫ ፖለቲካ ጨዋታው 
June 25, 2023

ጠገናው ጎሹ

ነገረ አስተሳሰባችንና ነገረ ሥራችን ሁሉ ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች እየተፈራረቁ የሚያወርዱብንን መከራና ውርደት ማስቆም በሚያስችል ፅዕኑ ራዕይ ፣ መርህ፧ ዓላማ ፣ ስትራቴጅ፣ ግብ ፣ እቅድ፣ አደረጃጀት እና የተግባር ውሎ ላይ የተመሠረተ ባለመሆኑ ቀንና ሌሊት የሚፈራረቁበትን ስዓታት እንኳ ሳይጠብቅ ከሚንጠን የሃዘን ማእበል ፣ በደም እንባ ጎርፍ ከሚያጥለቀልቀን አስፈሪ ሁኔታ፣ አሰቃቂው የእኩያን ገዥዎች ሥርዓት ከሚተፋብን የእሳት እቶን ፣  ለዘመናት ከዘለቀውና አሁንም ለማመን በሚያስቸግር ሁኔታ እያሸማቀቀን ካለው የድህነትና የተመፅዋችነት ሃፍረት ፣ ገዳይዮችንና  አስገዳዮችን እየተማፀን  ከቀጠልንበት ከፉ አዙሪት ፣ የገዛ ራስ ስንፍና እና ውድቀት የሚያስከትለውን ጉስቁልና የሚፀየፈውን ፈጣሪን ሳይቀር  ካልወረድክ እያልን ከቀጠልንበት አሳፋሪና አስከፊ አባዜ  ሰብረን ለመውጣት በሚያስችል አቋምና ቁመና ላይ አይደለንምና ከምር ቆም ብለን ማሰብን የግድ ይለናል።

ቀዳሚው ተጠያቂ እና የነፃነትና የፍትህ ትግል ዒላማ የባለጌና ጨካኝ የጎሳ/የመንደር አጥንት ስሌት ፖለቲካ ገዥ ቡድኖች ሥርዓት የመሆኑ እውነትነት እንደ ተጠበቀ ሆኖ የዚሁ ሥርዓት "የተሃድሶ ለውጥ ገድል" ፍቅር ሰለባ ለመሆን ፈቃደኛ ሆኑት እንደ ኢዜማ አይነት ተቀዋሚ (ተፎካካሪ) ተብየ ቡድኖችም (አካላትም) ከሃላፊነትና ከተጠያቂነት የሚያመልጡበት መውጫ መንገድ ፈፅሞ የለም። አይኖርምም። የገዳይ፣ የአስገዳይና የአገዳዳይ ገዥ ቡድኖች አጋሮች ብቻ ሳይሆኑ ቀጥተኛ ግብረ በላዎች ናቸውና። አዎ! በንፁሃን ደም የጨቀየ ግብረ በላነት!!!

ይህንን ግልፅና ግልፅ የሆነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ድህነት፣ የሞራል ዝቅጠት እና የቁም ሙትነት በአስመሳይ የመግለጫ ጋጋትና የዲስኩር ድሪቶ ለመሸፋፈን መሞከር ከደመ ነፍስ እንስሳት በታች የሚያደርግን ፍላጎት ለጊዜው ያረካ እንደሆን እንጅ ፈፅሞ አያዛልቅም!

የሚያዛልቀው ከዘመን ጠገቡና በአሁኑ ጊዜ ደግሞ እንኳን ለማመን ለማሰብም በሚከብድ ሁኔታ በተረኞች ከቀጠለው ሥርዓት ጋር የፈፀሙትን እኩይ (ያልተቀደሰ) አጋርነት (ጋብቻ) አፍርሶ በእውነተኛ ፀፀትና ይቅርታ በእጅጉ የበደሉትን መከረኛ ህዝብ መካስ ብቻ ነው።

ለሩብ ምእተ ዓመት ህሊናቸውን ሸጠው ሲያገለግሉት የቆዩትን ህወት መራሽ የባለጌዎችና የጨካኞች ሥርዓት በተረኝነት ተቆጣጥረው ለማመን የሚያስቸግር የጭካኔ ሰይፋቸውን በመከረኛው ህዝብ ላይ ካሳረፉት ኦህዴዳዊያን/ኦነጋዊያን/ኦሮሙማዊያን/ብልፅግናዊያን ጋር በእርካሽ የፖለቲካ አመንዝራነት እየተሻሹ (ጭራን እየቆሉ) የያሳስበናልና የይታሰብበት መግለጫ በማዥጎድጎድና የዲስኩር ድሪቶ በመደረት እመኑንና እንተማመን ማለት በመከረኛው ህዝብ መከራና ውርደት ላይ መሳለቅ ነው የሚሆነው።

ከቀናት በፊት ተዘጋጅቶ የተሰራጨውን የኢዜማ መግለጫ በስሜት ከመጋለብ ክፉ የፖለቲካ ልክፍት ወጥቶ በቅጡ (ሂሳዊ በሆነ አስተሳሰብ ወይም ምልከታ) ላነበበና ለታዘበ የአገሬ ሰው በአብይ አህመድና በካምፓኒው ማለትም ኦህዴድ/ኦነግ/ብልፅግና “መቶ በመቶ እተማመናለሁ” በሚል የመከራውና የውርደቱ ዘመን እንደሚራዘም  ካደረጉ የኢዜማ ፖለቲከኞች ለርካሽ ህዝባዊነት (ተወዳጅነት) ሲባል የሚሰራጨውን የመግለጫ ጋጋት ከምር ወስዶ “ጠንካራ ፣የበሰለ፣ የተሻለ፣ ወዘተ” እያሉ ማራገብ ከመሬት ላይ ካለው እጅግ መሪር እውነታ ይልቅ በወረቀት ላይ ነብር እየደነዘዙ  የሰቆቃውን ዘመን ማራዘም ነው የሚሆነው።

እንዲህ አይነቱ የልክ ልኩን ነገሩት ወይም የልክ ልኳን ነገሯት ወይም የልክ ልካቸውን ነገሯቸው የልጆች ጨዋታ አይነት ፖለቲካ የባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች መሳለቂያዎችና ሰለባዎች አድርጎናልና ይበቃናል።

እጅግ ልክ የሌለው አድርባይነት ከተጠናወተው የፖለቲካ አስተሳሰብና ከዘቀጠ ሞራል የመነጨው "የመቶ በመቶ የመተማመን" ትርክት ለተፈፀመውና እየተፈፀመ ላለው ምድራዊ ሰቆቃ የራሱን አስተዋፅኦ የማድረጉን መሪር ሃቅ ፈፅሞ ማስተባበል አይቻልም።

ከልብ የሆነ ይቅርታ ለመጠየቅና ከገባበት የፖለቲካ የወንጀለኛ ገዥዎች ክለብ ራሱን ለማግለል  ወኔው የጎደለው  ኢዜማ  እየሞነጫጨረ  የሚያነብልንና የሚያስነብበን መግለጫ ፈፅሞ ስሜት አይሰጥም! ከባለጌና ጨካኝ ፍቅረኞቹ (ኦህዴዳዊያን/ኦነጋዊያን/ብልፅግናዊያን) በምንና እንዴት የተሻለ እንደሆነ ለመረዳትም ሆነ ለማስረዳት ፈፅሞ አይቻልም።

አዎ! አገር ለንፁሃን ዜጎቿ (ልጀቿ) ምድረ ሲኦል ስትሆን ምን አደርጋችሁ ተብለው ሲጠየቁ "የጥናት፣ የምክር እና የማስጠንቀቂያ ሰነድ እያዘጋጀን (እየሰነድን) አቅርበናል" በሚል ምላሽ ራሳቸውን እንደ የነፃነትና የፍትህ ተሟጋቾች (ታጋዮች)  አድርገው ሊያሳምኑን ሲሞክሩ ህሊናቸውን ጨርሶ የማይጎረብጣቸው ፖለቲከኞች የተሰባሰቡበት ኢዜማ በፖለቲካ ወለድ ወንጀል ለበሰበሰውና ለከረፋው ሥርዓት እድሜ መራዘም  ጉልህ ድርሻ ማበርከቱን ለማስረዳት ማስረጃና መረጃ ፍለጋ መድከም አያስፈልገንም።

በእውነት ስለእውነት ከተነጋገርን እጅግ አደገኛ በሆነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ካንሰርና መግለፅ በሚያስቸግር የሞራል ዝቅጠት የተበከለውን ሥርዓተ ኦህዴድ/ኦነግ/ብልፅግና “በሰላማዊ ህዝባዊ አልገዛም ባይነት መታግልና ኮርነር ማድረግ ፈፅሞ የመፍትሄ አካል ስላልሆነ ( ዮሃንስ የሚባል የኢዜማ አመራር አባል ከኢሳት ሞጋቾች ኘሮግራም አዘጋጅ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ ልብ ይሏል) ትክክለኛው አካሄድ በጥናት ላይ የተመሠረተ ሰነድ (የይፈፀምልን አቤቱታ) እየሰነዱ ማቅረብና መግለጫዎቸን ማውጣት ነው” በሚል ሊያሳምኑን (ሊያቂሉን) ሲሞክሩ ህሊናቸውን ጨርሶ የማይኮሰኩሳቸው የፖለቲካ "ሊቆች" የተሰባሰቡበት ኢዜማ ከመልካም ዜግነትና ከማህበራዊ ፍትህ ጋር ምን አይነት ዝምድና (ግንኙነት) እንዳለው ለመረዳት ፈፅሞ አይቻልም።

እናም በፅዕኑ የታመመ የፖለቲካ ክለብ (ሥርዓት) ሽፋን ሰጭ ሆነው እያለ የፈዋሽነት ወይም የመፍትሄ አካልነት መግለጫ የማዥጎድጎድ ፖለቲካ ጨዋታ ተጫዋቾችን (ተዋንያንን) በግልፅና በቀጥታ በቃችሁ ለማለት እስካልቻልን ድረስ የመከራውና የውርደቱ ዘመን አያጥርምና ልብ ያለው ልብ ይበል!!!
https://amharic-zehabesha.com/archives/184094
South Africa President Shouts to the World Africans aren't Beggars Respect us Now
https://youtu.be/OOGSJY44meo

South Africa President Shouts to the World Africans aren't Beggars Respect us Now
https://zehabesha.com/south-africa-president-shouts-to-the-world-africans-arent-beggars-respect-us-now/
The chairwoman of Ethiopia's National Election Commission (NEBE), Birtukan Mideksan resigns
The chairwoman of Ethiopia's National Election Commission (NEBE), Birtukan Mideksan, an imprisoned former opposition politician who had held the post since December 2018, announced on Monday that she had tendered her resignation for health reasons.

"Needing a long rest to take care of my health, I submitted my letter of resignation on June 12 to the office of the Speaker of the House of People's Representatives (lower house of parliament, ed. note) to inform him that I will, of my own free will, be stepping down as NEBE chair on August 7, 2023," 49-year-old Birtukan wrote in a Facebook post.

"The remaining time will be devoted to completing unfinished business and ensuring the administrative transition," she continued, without giving any further details.

Among the "unfinished business" should be the proclamation of the official results of the referendum on the creation in southern Ethiopia of a 12th regional state within the federal state.

The vote took place on 6 February in several administrative zones of the Southern Nations, Nationalities and Peoples Regional State (SNNPR), which had called for them to be grouped together in a new region. However, the vote was cancelled in the Wolayta zone due to irregularities, and was re-run there on 19 June.

According to the results published by NEBE on 24 June, voters in this area voted overwhelmingly in favour of a new region, as did those in the other areas concerned.

Two similar referendums, in 2019 and 2021, have already resulted in the creation of two additional regions, Sidama and Sud-Ouest, which were split off from the SNNPR.

A former judge and then opposition leader, imprisoned in the 2000s under the coalition regime dominated between 1991 and 2018 by the Tigray People's Liberation Front (TPLF), then exiled to the United States, Ms Birtukan was chosen by the new Prime Minister Abiy Ahmed, shortly after he came to power in 2018, to chair the NEBE.

"Over the past four years and six months, I have tried honestly and in accordance with the law to fulfil my duty: to manage the political parties and organise three referendums and one national election", she said.

According to the Constitution, NEBE is responsible for "organising elections impartially, freely and fairly", in a country where the sincerity of the ballots has long been contested.

In 2018, Mr Abiy promised that the 2020 legislative elections would be "free, fair and democratic", but they were postponed twice, first because of the Covid pandemic and then because of logistical difficulties.

The elections were finally held in 2021, but it was not possible to hold them in all the constituencies due to the multiple outbreaks of violence, in particular the armed conflict opposing

AFP
https://zehabesha.com/the-chairwoman-of-ethiopias-national-election-commission-nebe-birtukan-mideksan-resigns/

Monday, June 26, 2023

https://youtu.be/jCb91uyamNI

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፓሪስ ቆይታ ........'' ከዶ/ር ዮናስ ብሩ ጋር
https://amharic-zehabesha.com/archives/183960
https://youtu.be/jCb91uyamNI

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፓሪስ ቆይታ ........'' ከዶ/ር ዮናስ ብሩ ጋር
https://amharic-zehabesha.com/archives/183960
The Horn of Africa States The Politics and Economics of Water Issues
By Dr. Suleiman Walhad

June 25th, 2023

Whenever water issues are raised, the Horn of Africa States region is one of the few places that come to mind. But this is a phenomenon that is no longer unique to the region. It is becoming a feature in other parts of the world such as the United States, and Europe where water issues are becoming acute and problematic. Some predict that water wars may occur in the future, which would make this world less safe and less secure as Kamala Harris, the United States Vice President recently noted. She further said that “water security is now one of the focal points in America's strategy”.

Water security and water availability is being delineated by many countries as an important strategic issue and the Horn of Africa with the current shortages of rains, generally reported to be the worst in over forty years, should not be taken lightly by the region’s leadership. The story of the GERD and Egypt is, perhaps, one of the well-known issues related to water in the region. However, the growing population of the region itself and their need for water, for themselves and for their large livestock populations, would not only affect lives in the region but also other parts of the world as people would move through migration processes, legal or illegal, as thirst and hunger drive people out of their normal abodes and ways of life.

A UNICEF ADVOCACY BRIEF on investing in water security for children in the Horn of Africa generally noted that more and more people are exposed to water insecurities in the region, which they wrongly define as inclusive of some East Africa Community countries such as Kenya, Uganda and South Sudan. The statistics for the region from the UNICEF thus remain tainted as they are not specific to the Horn of Africa States region which consists only of the SEED countries (Somalia, Ethiopia, Eritrea and Djibouti).

Although climate change in the region is blamed for most of the food insecurities, the issue of terrorism which prevents people from working on their small farms and herding of livestock, appears to be more dangerous than the climate induced shortages. In some parts of the region deluges have affected more than rain shortages, while in others, governments struggling fighting terror groups both tribal/ethnic and religious, play significant roles. In effect most of the problems appear to be man-made, than really natural. NGOs living off the backs of poor people keep calling for assistance for the region, and collect people in camps scattered throughout the region, which assistance never reaches the region. Perhaps only some 5 to 10 percent of the funds collected, on behalf of the region only, reach the intended populations.  The balance is consumed by the fat administrations of the NGOs and even the United Nations organs and other international institutions, who enjoy bosh hotels and residences in Nairobi and other cities of the region.

The onus remains to be on the leadership of the region, which includes not only the ruling parties but also the opposition groups which play into the hands of the interfering foreign parties. They would need to devise and come forth with solutions and strategies that address the issues of water security in the region. A region such as the Horn of Africa States would always attract foreigners because of its geostrategic location and, therefore, its leadership should take advantage of such opportunities to develop and improve the lives and loves of the region’s population and especially when it comes to water availability and water security.

The Guardian in a report on April 27th, 2023, warned of devastating droughts in the region, including members of the EAC countries. The report was not HAS-specific, indeed, but a warning anyway for the region. The report noted that the droughts in the region could not have happened without human actions. Human actions come from near and far. Those that are coming from afar include the usage of fossil fuels in other parts of the world, while the local actions of humans pertain to the continuing civil strives in the region, which does not allow people to grow their own foods, resulting in fallow fields and hence less greeneries and less vegetation. This leads to poor soils and inabilities of people to retain rainwater which comes as flashes and runs away.

The region created in the past a specific organization to deal with and manage droughts and desertification in the region. The institution was called the Inter-governmental Authority for Droughts and Desertification (“IGADD”) but the leaders of chaos that came after the collapse of the socialist leaning military regimes of Ethiopia and Somalia, changed the mandate of the institution to one that is more political and security-oriented than actually dealing with the original purpose for which it was created. Whence the leaders decide to stay only in politics and social issues, nothing really happens in any other front, be it economic or dealing with the plights of the populations related to droughts and water shortages and, indeed, food shortages.

Water shortages is no doubt a major issue in the region, and it needs to return to its traditional food production processes, even at the subsistence level as most families used to produce their own foods, whether this was tilling the lands or herding of animals. Perhaps, they would need to revisit the issue of herding which need not continue in the traditional model of nomadism or moving from place to place in search of water and fodder. They could settle and herd the animals in fixed locations drilling wells and growing fodder for the animals. Some projects in this regard have been started in various locations and so far, they appear to have been successful. It is where governments can help in providing resources which the ordinary citizen cannot afford.

A collective approach of the governments of the region with respect to water issues remains necessary as it was in the past. Perhaps there is a need to reform the IGAD organization to its original IGADD and hence mandate. While politics would always determine the way people of the region react to issues, there is a need for the region’s leadership to put their heads together and sketch together ways of handling the issue of water shortages of the region and its consequences. The region, which remains to be the roof of Africa would have to deal with the waters of the Nile and the GERD and other rivers that descend from the plateaus of the region. Water management thus remains to be one important area where the regional leaders need to be working together instead of working against each other.

Regional ownership of the issue is important, and this should aim at restoring some of the forests and trees the region lost out of negligence and out of focus in the past. The world is changing, and its climate is warming, and the region needs to work out processes of dealing with the oncoming disasters of water shortages and climate change. The region, while welcoming assistance from beyond, should be working more and together on its own solutions as well.

The issue of water and water security remains challenging with respect to the economies of the region which remain small and underdeveloped. A lot of damage to the environment has already been done by others from beyond the region. The individual states of the region alone, therefore, stand little chance of confronting these challenges but working together would, no doubt, allow them, at least, to have a bigger bargaining chip when it comes to seeking respite and assistance from the industrialized world, which have caused most of the damage to the environment.

Yet this does not negate the drive of the regional leadership to raise awareness of the issue of water security and water shortages and its effects on the environment within the societies of the region. This can be done through introduction of the matter through educational systems. This remains a focal issue which the populations of the region need to be all working on. It is where even the governments of the region need help from an aware citizenry.

Tackling water issues and generally environmental issues remain no ordinary challenges and would require not only governmental interference but also population involvement using all the possible means at their disposal, be it economic, political, social and scientific.  It is maintaining, at least, something for the future generations of the lands, rivers, lakes, seas, and lives thereon, of the region.

 

 
https://zehabesha.com/the-horn-of-africa-states-the-politics-and-economics-of-water-issues/

Sunday, June 25, 2023

ኢትዮጽያን ና የአፍሪካን ቀንድ ለማዳን የአለማቀፍ ማህበረሰብ ጫና ወሳኝ ሚና (ዶ/ር ዮናስ ብሩ)

ኢትዮጽያን ና የአፍሪካን ቀንድ ለማዳን የአለማቀፍ ማህበረሰብ ጫና ወሳኝ ሚና   (ዶ/ር ዮናስ ብሩ)


በኢትዮጽያ ሁለት መንግስታት አሉ ። አንደኛ የአድናቆት ስስት በተጠናወተው ለራሱ ከፍተኛ ግምት የሚሰጥ ጠቅላይ ሚኒስትር የምትመራ ኢትዮጽያ አለች ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሚመራው ህዝብ ደህንነት ግድየለሽ በመሆኑና የህዝቡን ስቃይ ለመገንዘብ ባለመቻሉ የሀገሪቱን ሀብት ድህነት ተኮር ከሆኑ ጠቃሚ መንግስታዊ የልማት ስራዎች ጭምር በማውጣት በጣት ለሚቆጠሩ እርባናቢስ ፕሮጀክቶች ማስፈፅሚያ እንዲውል አድርጓል።

ለራሱ የተጋነነ ከፍተኛ ግምት የሚሰጥ ሰው ስብእና የሚገነባው ራሱ በስቀለው ማማ ላይ ወጥቶ በመሆኑ ተጨባጭ እውነቶችን እንደ ረብሻ በመቁጠር ከእውነት ተጣልቶ ይኖራል። ይህም የማስተካከያ እርምጃዎች ለመውስድ የሚያስችሉ አጋጣሚዎች ሲፈጠሩ እድሉን እንዳይጠቀምበት አድርጎታል።

ሁለተኛው የኦሮሙማ መንግስት ነው ። ኦሮሙማ ፀረ ኢትዮጽያ ፤ ፀረ ክርስትናና ፀረ እስልምና የሆነ ራሱን የኦሮሞ ብሄራዊ ንቅናቄ ዋና ርእዮተ አለም አድርጎ የሚወስድ የኦሮሞ አሸባሪ አምልኮ ነው ። የንቅናቄው ዶግማ በቅስቀሳ ዘመቻው ፣ በንቅናቄውና ኢሰብአዊ በሆነ ጭካኔው ናዚዎች የተደራጁበትን ስርአት ይከተላል። ከቀን ወደ ቀን የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግስት በመገዝገዝ ላይ ይገኛል። መሪዎቹ ፕሮፌሰር አሰፋ ጃለታና ሺመልስ አብዲሳ ናቸው። እ.ኢ,አ ከ2007 ወዲህ የቲኒሲ ኖክስቬል ዩኒቨርሲቲ የመረጃ መረብ ድህረ ገፅ ለንቅናቄው የጥላቻ ንግግርና የዘር ፍጅት ቀስቃሽ ጽሁፎች ማከማቻ በመሆን እያገለገለ ይገኛል ።

ምንም እንኳ ሁለቱ መንግስታት መሳ ለመሳ እየሰሩ ቢሆንም የጋራ ፍላጎቶችና የማይታረቁ ቅራኔዎች አሏቸው ሁለቱም የፖለቲካ ስልጣን መሰረት የሚሆን የኦሮሞ ጎሳን ድጋፍ ለማስባሰብ ባላቸው ፍላጎት ይመሳሰላሉ። ልዩነታቸው የሚመነጨው ከዘላቂ አላማዎቻቸው ነው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ታላቅ ጉጉት የኢትዮጽያ ንጉስና የአፍሪካ ምርጥ መሆን ነው ። በአንፃሩ ኦሮሙማ በሀገር ውስጥ የተወሰነና ወደ ኋላ የሚያልም በከፊል አምልኮና በከፊል የፖለቲካ ዶግማ የሆነ ሀገሪቱን ወደ 16 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ለመመለስ የሚመኝ ነው።

ምንም እንኳ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማን አህሎኝነት እየፎከሩ ቢሆኑም የስልጣን መሰረት የሆናቸው ህዝባዊ ድጋፍና ህጋዊ ተቀባይነታቸው በፍጥነት በመሸርሸር ላይ ይገኛል። የኦሮሙማን አራማጆት ትእዛዝ በመፈፀም ድጋፍ ለማግኘት አብያተክርስትያናትን ና መስጊዶችን እስከ ማፍረስ ደርሷል። ያም ሆኖ እንደ ተአማኒ አጋር እንደማይወስዱት ለመረዳት አያዳግትም። እሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን ያበቃውን ለማ መገርሳን ፤ ከትህነግ ወረራ ያተረፈውን ፕሬዝዳንት ኢሳያስን ከድቷል። እንዲሁም ጠመንጃውን ሊገድሉት ወይም ሊይዙት እየዛቱ ወደ አዲስ አበባ ሲገሰገሱ የነበሩትን የትህነግ ታጣቂዎችን ያቆሙለት የአማራ ህዝብና ፋኖ ላይ አዙሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለራሳቸው በሚሰጡት ጤናማ ያልሆነ የተጋነነ ግምት፣ በኦሮሙማ የዘርማጥፋት የህሊና ውቅርና ኢስብአዊ ጭካኔ ሰበብ ኢትዮጽያ በመፈራረስ ላይ ትገኛለች ። አስፈሪ የዘርማጥፋት ዝግጅት ውስጥ ውስጡን እየተብላላ ነው። የዘር ማጥፋቱን የሚያቀጣጥለው የኦሮሙማ ጥላቻ የሩዋንዳን ዘር ማጥፋት ካመጣው ሃይል የማይተናነስ ክፋት አለው። ከሩዋንዳ ዘር ማጥፋት በኋላ ‘ሁለተኛ አይደገምም ‘ የሚል ቃል የገባው አለም አቀፉ ማህበረስብ በ120 ሚሊዮን ኢትዮጽያውያን ላይ የተደቀነውን የህልውና አደጋ የመቀልበስ የሞራል ግዴታ አለበት ። በተጨማሪም አለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጽያን መረጋጋት የሚፈልግበት አካባቢያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞች አሉት ምክንያቱም ኢትዮጽያ በአለም ዋና የነዳጅ መተላለፊያ ከሆኑት አንዱ በሆነውና ለአለም አቀፍ የነዳጅ ሃይል አቅርቦት ዋስትና ወሳኝ በሆነው የአፍሪካ ቀንድ የምትገኝ ታላቅ ሀገር በመሆኗ ነው።

 


የአእምሮና የስነምግባር ብቃት የጎድለው ጠቅላይ ሚኒስትር


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉን አድራጊ ፤ሁሉን አዋቂ፤ በሁሉ ቦታ መገኝት የሚችል መሆኑን ማመኑ የስነልቦና ቀውሱን ማሳያዎች ናቸው ። በሰባት አመት የልጅነት እድሜው እናቱ የኢትዮጽያ ንጉስ እንደሚሆን ና ሀገሪቱን ከድህነት ወደታላቅነት እንደሚመራ እንደነገረችው በአደባባይ ለመናገር ምንም ሀፍረት አልተሰማውም። በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርቦ በእኔ አመራር በ2050 ኢትዮጽያ በአለም ሁለተኛ ልእለ ሃያል ሀገር ትሆናለች ሲል እንዲሁ ሀፍረት አይሰማውም። እናት ለልጆቿ ያላትን በጎ ህልም እንደ የመፅሃፍ ትንቢት ያምናል።

ለአድናቆትና ዝና የማይረካ ጥም አለው። የእሱን የቅዥት ስኬት በመሬት ላይ ካለው ውድቀቱ ለማስታረቅ ሲያቅተው እውነታውን መሸሽ እንደአማራጭ ይጠቀማል። በምሳሌ ላስረዳ

በዴሴምበር 2022 እ.ኢ.አ አለም አቀፉ ሚዲያ ዮክሬን ስንዴ የተጫነች መርከብ የተራቡ ኢትዮጽያውያንን ለመመገብ እንደሰደደች ሲዘግብ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውዝግብ አስነስቷል። በቴሌቪዥን ቀርቦ ‘’መንግስቴ ፈጽሞ ስንዴ አልለመነም አለም አቀፉ ማህበረሰብ ስንዴ የሚልከውና በአለም አቀፍ ሚዲያ የሚያራግበው በምግብ እህል ራስን በመቻል ያስመዘገብኩትን ስኬት ለማንኳሰስ ነው። ‘’ ሲል ንዴቱን ገልጿል። ‘’ኢትዮጽያ የምግብ እርዳታ ከመጠበቅ አልፋ ምግብ ለውጭ ንግድ ለማቅረብ ተዘጋጅታለች ‘’ ብሏል።

እ.ኢ.አ በ2023 አሜሪካ ና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለተራቡ ድሆች ሊቀርብ የሚገባው ስንዴ ላይ ከፍተኛ መንግስታዊ ስርቆት ተከስቷል በሚል ለኢትዮጽያ የሚያቀርቡትን ስብአዊ ድጋፍ አቁመዋል። በእርዳታ የተገኘው ስንዴ ወደ ዱቄት ተቀይሮ ኬንያና ሱማሊያ ተልኮ ተሽጧል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ በአደባባይ ወጥተው አሜሪካንና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስብአዊ ድጋፍ ለማቆም መወሰናቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጽያውያንን ለርሃብ አደጋ ያጋልጣል ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ይህ የተገለፀው ከስድስት ወራት በፊት ኢትዮጽያ የተትረፈረፈ ምርት አምርታ ስንዴ ለውጭ ገበያ ታቀርባለች ባለው የጠቅላይ ሚንስትር ቢሮ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥላውን የማያምን ሰው በመሆኑ ሰላማዊ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ለርሱ ፍፁም ስልጣን አደጋ እንደሆኑ አድርጎ ይወስዳል ። እ.ኢ.አ በ2021 በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ስልጣኔን ሊቀሙ እያሴሩ ነው በማለት ከሶ በአንድ ጀንበር በመቶ ሺዎች ሲገደሉ ያያሉ ሲል ዝቷል።

እ.ኢ.አ በ 2023 እርሱን ከስልጣን ለማውረድ ብጥብጥ የሚያስነሱ ጽንፈኞች በ1970 ከነበረው የቀይ ሽብር እልቂት የበለጠ መዘዝ እንደሚያስከትል ሊያውቁ ይገባል ሲል ዛቻውን ከፍ አድርጎታል ። እንደ አፍሪካ ህብረት መረጃ በቀይ ሽብር ከ700,000 የሚበልጡ ኢትዮጽያውያን ተገድለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ደህንነት ግድየለሽነትና ችግሩን ለመረዳት ፍላጎት ማጣት ለህዝቡ ስቃይ ማዘን እንዳይችል አድርጎታል። ወደ ስልጣን ከመጣ ጀምሮ ከሚሊዮን የሚበልጡ ሰዎች በጦርነት፣ ርሃብና የጅምላ ፍጅት አልቀዋል እንዲሁም ከ 5 ሚሊዮን የሚበልጡ ሰዎች በግድ ተፈናቅለዋል ። ይህ ሁሉ ሆኖ እሱ ቅድሚያና ትኩረት የሚሰጠው ለታይታ መናፈሻዎችና ቤተመንግስት ግንባታዎች ነው ። የሚገነባው ፈርኦናዊ ቤተ መንግስት ሶስት ሰው ሰራሽ ሃይቆች ፤ የአራዊት ፓርክ ፤ ፏፏቴና በዱባይ ደረጃ ያሉ ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን ጨምሮ ሊሎች ቅንጡ ግንባታዎችን ያካተተ ነው ። ይህ የርሱ ፕሮጀክት በኢትዮጽያ ታሪክ እጅግ ውድ ሲሆን እስከ 15.3 ቢሊዮን ዶላር ያስወጣል።

ስለፕሮጀክቶች የሚቀርቡ ሰፊ ወቀሳዎች ሲመልስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጽያ ድህነት ፕሮጀክቶቹን ከማስፈፀም እንደማያግዱት በጥብቅ በመቃወም ተናግሯል። በአሜሪካ በምግብ እርዳታ የሚኖሩና ቤት አልባ የሆኑ ዜጎች የኢትዮጽያን ህዝብ 50 በመቶ (ከ 60 ሚሊዮን በላይ) የሚሆኑ ናቸው ሲል ሞግቷል። መልእክቱ ይህ አሜሪካንን ወደ ማርስ መጓዝን ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ከማስፈፀም አላገዳትም ነው።

ይህ ሆነተብሎ የተደረገ ግልፅ ማጭበርበር ነው። በመጀመሪያ በአሜሪካ ቤት አልባ ዜጎች ቁጥር 582,000 ነው በምግብ እርዳታ የሚኖሩ አሜሪካውያን 42 ሚሊዮን ናቸው ይህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጠቀሰው 60 ሚሊዮን ያነስ ነው። ዋናው ነገር በምግብ እርዳታ የሚኖሩ አሜሪካውያን ያጡ የነጡ አይደሉም።

ምንም እንኳን የመንግስት የተለያዩ ድጎማዎች ተጠቃሚ ቢሆኑም አብዛኛዎቹ መኪና ፤ የራሳቸው ቤት ፤70 ኢንች ቲቪ ፣ ዘመናዊ አይ ፎን፤ የመሳሰሉት አላቸው። ለምሳሌ 4 አባላት ያሉት (ባል ፤ ሚስት ና ሁለት ልጆች) አመታዊ ገቢው ከ36,084 እስከ 55,512 ዶላር የሆነ አንድ ቤተሰብ ለምግብ ርዳታ ብቁ ይሆናል ። 8 አባላት ያሉት (ባል፤ሚስት ና ስድስት ልጆች) አመታዊ ገቢው 60,624 እስከ 93,264 ዶላር የሆነ ቤተሰብ ለምግብ እርዳታ ብቁ ይሆናል ምክንያቱም በአሜሪካ ደረጃ እነዚህ ከድሃ ስለሚመደቡ ነው ።

 


የኢኮኖሚው ቀስ በቀስ መፈራረስ


የእርስ በርስ ጦርነቱ፤ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ቅድሚያ አለመስጠትና የተሳሳቱ የኢኮኖሚ መመሪያዎች ድምር ውጤት የሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ጂዲፒ 25.9 በመቶ መቀነስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዱባይ ያዩትን ብልጭልጭ የሚደንሱ ውሃዎችና የታላቁ ፒተርን የመሰሉ መናፈሻዎች በመገንባት ለመዝናናት በሚያስቡበት በአሁኑ ወቅት 22 ሚሊዮን ኢትዮጽያውያን አለም አቀፍ የምግብ እርዳታ ጥገኛ ናቸው። እንዲሁም ከ 2.3 ሚሊዮን በላይ ህፃናት በጦርነቱ የወደሙት ትምህርት ቤቶች እስኪሰሩ ከትምህርት ገበታ ውጭ ናቸው። ከዚህም አልፎ 3 ሚሊዮን ሰዎች ከድህነት ወለል በታች የሚኖሩ ኢትዮጽያውያንን ተቀላቅለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገንዘብ በማተም በሚያሰራቸው የማይረቡ ፕሮጀክቶች (15.3 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣውን ቤተ መንግስት ጨምሮ) የሃገሪቱን ኢኮኖሚ እያወደመ ነው ። እ.ኢ.አ በ2018 የኢትዮጽያ የዋጋ ግሽበት 13.8 በመቶ ነበር። በዚሁ ወቅት ከሳሃራ በታች የሚገኙ ሀገሮች አማካይ የግሽበት መጠን 4.1 በመቶ ነበር። እ.ኢ.አ

በጃንዋሪ 2022 ኢትዮጽያ በአለም የከፋ የዋጋ ግሽበት ከስመዘገቡ 10 ሀገራት መካከል አንዷ ነበረች። የአለም የገንዘብ ድርጅት የ2023 የኢትዮጽያ ግሽበት ትንበያ 31.4 በመቶ ነው። በ2024 የግሽበት ትንበያው 23.5 በመቶ ነው ። የአፍሪካ 2024 አማካይ የግሽበት ትንበያ 5 በመቶ ነው።

ዋናው አሳሳቢ ጉዳይ የ2023/24 የመንግስት የ281.05 ቢሊዮን ብር (5.2 ቢሊዮን ዶላር) የበጀት ጉድለት ነው። የተለያዩ ምክንያቶች ለችግሩ አስተዋፅኦ አድርገዋል። አንዱ ከቀረፅ የሚገኝው ገቢ ለሀገር ውስጥ አጠቃላይ ምርት ሲካፈል ውጤቱ እየቀነስ መምጣቱ ነው ። ከአምስት አመት በፊት 0.11 ነበር በ2022/2023 በጀት አመት 0.07 ነበር ። ከስሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት አማካይ 0.17 ነው። ወደር የሌለው ሙስና ሌላኛው ነው። ወደ መንግስት ካዝና ሊገባ የሚገባው ገንዘብ ወደ ግለሰቦች የግል ባንክ ሂሳብ ይገባል። ከወርቅ የውጭ ንግድ ይገኝ የነበረው ገቢ 59 በመቶ መቀነሱ ለዚህ ምሳሌ ነው። ሶስተኛው ምክንያት አለም አቀፉ ማህበረሰብ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የአስተዳደር ብቃት ላይ እምነት በማጣቱ እርዳታ በከፍተኛ መጠን መቀነሱ ነው።

ሁለተኛው አሳሳቢ ጉዳይ መንግስት ለዘላቂ ልማት ስራዎች (ለመንገዶች ፤ ድልድዮች ና ለመሳሰሉት) የሚመድበው ገንዘብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱ ነው ። በመንግስት በሚጠቀስ አንድ የ’ሴፈስ ካፒታል’ ሪፖርት በ2018/19 በጀት አመት የመንግስት የዘላቂ ልማቶች ወጪ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 6.5 በመቶ ብቻ ነበር። በ2022/23 ወደ 2.9 በመቶ አሽቆልቁሏል። የኢትዮጽያ የስታስቲክስ አገልግሎት መረጃ ተመሳሳይ ነው። ለ2023/24 ምንም መረጃ አልወጣም ሆኖም በዋጋ ግሽበት ምክንያት በተፈጠረው የመንግስት በጀት መቀነስ ቁጥሩ በ2022/23 ከነበርው በጣም እንደሚቀንስ ይገመታል።

“ከፍተኛ ማሽቆልቆል” የሚለው አጠቃላይ የኢኮኖሚውን ሁኔታ የሚገልፅ ይመስላል ። ቱሪዝም አንዱ ማሳያ ነው። ሀገሪቱ በጦርነቱ ና በኮቪድ 19 ምክንያት 2 ቢሊዮን ዶላር አጥታለች ። ። ጦርነቱ ከስድስት ወራት በፊት

አቁሟል።ወረርሽኙ ካለፈ በኋላ አለም አቀፍ ቱሪዝም ሲያንሰራራ የኢትዮጽያ ግን ወደ ቀድሞው ሊመለስ አልቻለም። ይህ በዋናነት በሀገሪቱ ህግ ና ስርአት ባለመኖሩ ምክንያት የመጣ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእውነት እንደተጣላ ዋነኛው ማሳያ ቱሪዝም ነው ። ህግ ና ስርዐት ወደ ሌለበት ዜጎች ህግን በመዳፋቸው ወዳስገቡበት ሀገር ቱሪስት እንዳማይሄድ እየታወቀ ለቱሪስት መስህብ በሚል መናፈሻ መገንባቱን ቀጥሏል። በአንፃሩ ኬንያ በ2022 ቱሪዝምን ወደ ቀደመ ደረጃው መመለስ ችላለች። በ 2022 የቱሪዝም ገቢዋን 83 በመቶ በማሳደግ ወደ 2.13 ቢሊዮን ዶላር ማድረስ ችላለች ። በ2023 መጨረሻ ገቢዋ ወደ 3.37 ቢሊዮን እንደሚያድግ ይጠበቃል።

በከፍተኛ ማሽቆልቆል ላይ ከሚገኙት መካካል ኢንዱስትሪው ይጠቀሳል ። እንደ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በ2022 446 የማምረቻ ኢንደስትሪዎች ምርት አቁመዋል። የገንዘብ እጥረት፤ የመሰረተ ልማት አለመሟላት፤ የተቀናጀ መንግስታዊ ድጋፍ አለመኖር ና የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት እንደምክንያት ተጠቅሰዋል። የውጭ ምንዛሬ ችግር እንዲሁ አሳሳቢ ጉዳይ ነው ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጓዳ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ በማግኝታቸው የሀገሪቱ የማምረቻ ና ሌሎች ህዝባዊ ፕሮጀክቶች ከህጋዊው ተመን እስከ እጥፍ በመክፈል ወደ ጥቁር ገበያ ለመሄድ ተገደዋል ።የሃርቫርድ ጥናት እንዳመላከተው አሳሳቢ ደረጃ የደረስው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚፈልጉ አምራች ድርጅቶችን እየጎዳ ነው። በቅርቡ የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ከቻይና 200 አውቶብሶችን ለመግዛት የጥቁር ገበያ ተመን እንደተጠቀመ ለማመን ተገዷል። ይህ የከተማ መስተዳድሩ ለእያንዳንዱ አውቶብስ ከመደበኛው እጥፍ ዋጋ እንዲከፍል አድርጎታል።

ምናልባት እጅግ የሚያሳዝነው ማሽቆልቆል ከድህነት ቅነሳ ጋር የተያያዙ የመንግስት ወጪዎች ላይ የታየው ነው። እንደ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት የሩብ አመት የኢኮኖሚ ትንተና ድህነት ተኮር ወጪዎች

በ2022 የሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት 2.9 በመቶ ነበር ይህ ከ2017 ወዲህ ዝቅተኛው ነው። የኢትዮጽያ ስታስቲክስ አገልግሎት መረጃ ከ2017/18 እስከ 2020/21 ተመሳሳይ ማሽቆልቆል ያሳያል።

ብቸኛው ውጤታማ ድርጅት የኢትዮጽያ አየር መንገድ ነው 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢው ሀገሪቱ ከውጭ ምንዛሬ ንግድ ካገኘችው 3.9 ቢሊዮን ዶላር እጅግ ይበልጣል ። የሚያሳዝነው ይህ ፅሁፍ በሚፃፍበት ወቅት ከኢትዮጽያ የሚሰማው ሰበር ዜና የአየር መንገዱ ቦርድ ሊቀመንበር ግርማ ዋቄ በግዳጅ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ነው ታይምስ ኤሮስፔስ የአፍሪካ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አባት ተብለው የሚታወቁትን ሰው አስደንጋጭ የስራ መልቀቅ ‘’ ግርማ የኢትዮጽያን አየር መንገድ የአህጉሩ ታላቁ አየር መንገድ ና ከታላላቅ አለም አቀፍ አየር መንገዶች ተፎካካሪ እንዲሆን ያስቻሉ ናቸው’’ ሲል ዘግቧል ። አክሎም ‘’ምንም እንኳ በአየር መንገድ ስራ ውስጥ የመንግስትን ድጋፍ የሚያደንቁ ቢሆንም የመንግስትን በአየር መንገዱ አስተዳደር ጣልቃ መግባት ይቃወሙ ነበር ‘’ብሏል

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኝህን የአቪዬሽን እንቁ በኢትዮጽያ ፤ በቀጠናውም ሆነ በአለም አቀፍ አቪዬሽን ምንም እውቅና በሌላቸው ወጣት የአየር ሃይል ጄኔራል ቀይረዋቸዋል ። መላምቶች ቢኖሩም በግዳጅ ስልጣናቸውን የለቀቁበት እርግጠኝ ማብራሪያ አልተገኘም ። እንደኔ እምነት ውሳኔው የተደረገው የአየር መንገዱን የአሜሪካ ዶላር ና ዩሮ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቤተ መንግስት ፕሮጀክት ለማዞር ባለ ፍላጎት ነው። እንዲሁም አለም አቀፍ የምግብ እርዳታ ተሰርቆ ለውጭ ንግድ የቀረበበት ምክንያት በከፊል መንግስት እንዲሁ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የማይረቡ ፕሮጀክቶች የውጭ ምንዛሬ ለማቅረብ ካለው ሰቀቀን ጋር የተገናኘ ነው የሚለውን ከግምት ውጭ ለማድረግ አስቸጋሪ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገሪቱን ሀብት ምርታማ ና ድህነት ቀናሽ ከሆኑ ተግባራት ወደ ራሱ የማይረቡ ፕሮጀክቶች በማዞሩ የኢትዮጽያ ኢኮኖሚ እየሰጠመ ነው። ከዚህም የከፋው እነዚህን የማይረቡ ፕሮጅክቶች የሚያከናውነው ከ ሀገሪቱ ህግ ማእቀፍ ውጭ ነው።

መልስ የሚያሻቸው ጥያቄዎች አሉ ። አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ና የአለም ባንክ ይህንን እያዩ እንዳላዩ እይሰሙ እንዳልሰሙ መሆን ጆሮ ዳባ ልበስ ሊሉ ይችላሉ? ይህ የድርጅቶቻቸውን የአባል ሀገራትን ኢኮኖሚና የገንዘብ ፖሊሲ ጤንነት በየጊዜው የመመርመር ሃላፊነታቸውን አለመወጣት አይሆንም ወይ?

የምንሰማው የውጭ ምንዛሬ ተመንን በጣም ለመጨመር ያላቸውን ጉጉት ብቻ ነው ። መሰረታዊ የኢኮኖሚ ችግሮቹ ያሉት ሌላ አካባቢ ነው ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህግ ከተፈቀደለት ውጭ የማይረቡ ፕሮጀክቶችን ሲያቅድ ና ሲያስተገብር ለምን ዝም አሉት? ለምን ከፈተኛ ድጎማ የሚደረግለት ብድር ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለሚያደርስ አምባገነን ይሰጣሉ ? ይህ የአለም አቀፍ እርዳታ ገንዘብ ለሚያዋጡት አለም አቀፍ ግብር ከፋዮች ያለባቸውን የመተማመን ግዴታ መጣስ አይሆንም ወይ?

 


የኦሮሙማ መንግስት


ቃል በቃል ኦሮሙማ ማለት ኦሮሞነት ወይም ኦሮሞ መሆን ማለት ነው። በተለምዶ የኦሮሞን ባህል የማቀፍ ና መንከባከብ ጽንሰ ሃሳብ ነው። ክፋቱ ቃሉ የስን ምግባር ና ስነልቦና ድርቀት ባጋጠማቸው የኦሮሞ ጎሳ ምሁራን ተወርሶ ፤ ተጠልፎ ና ተበርዞ እንደ ዋና የኦሮም ብሄራዊ እንቅስቃሴ ርእዮት ሆኖ ቀርቧል ።

የኦሮሙማ የጡት አባት የሆኑት ፕሮፌሰር አሰፋ ጃላታ እንቅስቃሴው ሁለት መልክ እንዳሉት አረጋግጠዋል። ከታሪክ ፤ ባህል ና ልማድ የወጣው የተለመደው ኦሮሙማ ና የፖለቲካ ና ርእዮተ አለም ፕሮጀክት የሆነው ብሄራዊና አለም አቀፍ ኦሮሙማ ። ኦ ፕራይድ የተባለው ታዋቂ ጋዜጣ ቃሉን ‘’ የኦሮሞ ፖለቲካዊ ማንነት ‘’ በማለት ገልጾታል ።

የእንቅስቃሴው ደጋፊዎች የኦሮሙማ ኢስብአዊ ጭካኔዎች እንደ የፖለቲካ ርእዮት ሲጠቀሱ በጣም ይበሳጫሉ። ፍላጎታቸው የፖለቲካ ግቦቻቸውን በኦሮሞ ባህልና ልማድ መጋረጃ መደበቅ ነው። እውነታው በኦሮሙማ መዝገበ ቃላት የቃሉ ፍቺ ‘’ ብሄራዊ ና አለም አቀፍ የፖለቲክ ፕሮጀክት ‘’ የሚል ነው ።

ኦሮሙማን አደገኛ የሚያደርገው ለዋናው ፖለቲካዊ ፍላጎቱ ማህበራዊ ና ሃይማኖታዊ መልክ መጨመሩ ነው ። በዚህም የተነሳ ፖለቲካዊ ና ሃይማኖታዊ አመራሩን መቆጣጠር ለኦሮሙማ እንቅስቃሴ እጅግ ጠቃሚ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ክርስቲያኖች ና ሙስሊሞች በኦሮሞ መሬት ሃይማኖታቸውን የመከተል መብት እንዳላቸው እስከ መጠየቅ አድርሷቸዋል ። ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ በተደረገ ጥናት እንደተመላከተው ፕሮፌሰር ጃለታ ‘’ ኢስላም በኦሮሞ ማንነት ውስጥ ትክክለኛ ቦታ እንዳለው ለመቀበል አመንትተዋል ‘’ እንዲሁም ‘’ኦሮሞዎችን ክርስቲያን የማድረግ ሂደት ዘረኝነት ነው ‘’ ሲሉ ይከሳሉ።

እንደ የፖለቲካ ና ሃይማኖት እንቅስቃሴ ፣ ኦሮሙማ አመጽን ይጠቀማል እንዲሁም ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር በቅርበት ይሰራል ። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በጅምላ ግድያ ና ኢትዮጽያውያን ና የውጭ ሀገር ዜጎችን በማፈን ገንዘብ በመጠየቅ ይታወቃል ። የኦሮሙማ ምሁራን ለኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ገንዘብ ይሰበሰባሉ ፤እንዲሁም መንግስት ና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በታንዛኒያ ድርድር ሲቀመጡ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ልኡክ አባል ነበሩ።

የኦሮሙማ እንቅስቃሴ ዋና ኢላማ ‘’ የኢትዮጽያ ቅኝ አገዛዝ ‘’ ና እንደ ቅኝ ገዢ ተቋማት ና ግዛት አስፋፊ የሚታዩት ቤተክርስትያኖች ና መስጊዶች ናቸው ።ምንም እንኳ ኦሮሙማ የኢኮኖሚ ፤ፖለቲካ ና ባህል እንቅስቃሴ ነኝ ቢልም አትኩሮቱ ሃይማኖት ላይ ነው። ከሚያቀርቧቸው ክሶች መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ

•የሃበሻ ገዢዎችን ሃሳቦች ና ሃይማኖት አስተዋውቀዋል

•ኦሮሞዎች የበታችነት ስሜት እንዲሰማቸው ና ራሳቸውን እንዲጠሉ አድርገዋል

•የኦሮሞን ጥንታዊ ሃይማኖት በመቀየር ና የሃበሻ ና አረብ ስሞችን ፣ ሃይማኖትን ፤ ወግ ና ስርዐት መውረስ

•ኦሮሞዎች የተውሶ ሃይማኖት ማንነትና ንዑስ ማንነት መጠቀም መጀመራቸው

የኦሮሞ ህዝብ ክርስትና እና እስልምናን እንዳይከተል ጫና ማድረግ

የኦሮሙማ እንቅስቃሴ ባህላዊ ገፅ ሲፋቅ ና በጥልቀት ሲፈተሽ አላማው ዋቄ ፈና የተባለውን የኦሮሞ ሀገር በቀል ሃይማኖት እንደ መንግስታዊ ሃይማኖት እውቅና መስጠት ነው። እንደ 2007 ህዝብ ቆጠራ 3.3 በመቶ ኦሮሞ ብቻ ዋቄ ፈናን ይከተላል። በተቃራኒው 96 በመቶ የኦሮሞ ህዝብ ክርስትናን ና እስልምና ይከተላል ክርስትና ና እስልምና የሚከተሉና የሚያመልኩ ኦሮሞዎች የጥቃት ሰለባዎች ናቸው። በቴኔስ ዩኒቨርሲቲ የመረጃ መረብ ድህረ ገፅ የታተሙ ሁለት ጽሁፎች ኦሮሞ ክርስቲያኖችን ና ኦሮሞዎችን የገለፁት እንደሚከተለው ነው

‘’እንደ ሀበሻ ጌቶቻቸው የሃበሻ ባህልን ሃይማኖትን ና የአማረኛ ቋንቋን የሚያስጠብቁ ና የኦሮሞን ታሪክ ፣ ባህል ና ተቋማት የሚጠሉ ኦሮሞዎች ናቸው እንዲሁም ሙሉ በሙሉ ከኦሮሞ ልማድ የተገለሉ ና የበታችነታቸውን ባሳመኗቸው ገራፊዎቻቸው ሃሳቦች ና እውቀት የሚደመሙ ናቸው።’’ ሃበሻ በሰሜን ኢትዮጽያ የሚኖሩ ህዝቦችን ለመግለፅ ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። የኦሮሞ ክልል ፕሬዝዳንት አማራዎችን ‘’ጠላት ‘’ በማለት በተደጋጋሚ ሲገልፁ ተሰምተዋል።

የኦሮሙማ እንቅስቃሴ ምሁራዊ ሙከራ አይደለም ። የሃይማኖት ማፅዳት ቅድመ ዝግጅት ነው። ለዘር ማጥፋት ዘመቻ ፅንስ ነው ። በ ጃንወሪ 2023 የአሜሪካ ድምፅ እንደዘገበው ከኦሮሞ ጎሳ መሬት የተፈናቀሉ አማሮች ወደ አንድ ሚሊዮን ይደርሳሉ። ሰዎቹ ክርስቲያኖች ና እስላም ናቸው። በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰውን በደል በመዘከር ፖፕ ፍራንሲስ ተከታዮቻቸውን ‘’በኢትዮጽያ ለተገደሉ ክርስቲያኖች እንዲፀልዩ’’ ጠይቀዋል

ዘጋርድያን ‘’ ከሁለት መቶ የሚበልጡ አማራዎች በ ኦሮሞ ፅንፈኞች ተገድለዋል ‘’ ሲል ዘግቧል አብዛኛዎቹ ሙስሊም ነበሩ ። የ ሰብአዊ መብት ተሟጋች ‘’ ከፍተኛ ትጥቅ ያነገቡ ገዳዮች ሴቶችን ና ህፃናትን ጨምሮ

400 ሰላማዊ አማሮችን ገድለዋል ‘’ ሲል እንዲሁ ስለ ሌላ ዙር ጅምላ ጭፍጨፋ ዘግበዋል ። በሪፖርቱ የሚያለቅሱ ሙስሊም አባት ተጠቅሰዋል ።

‘’ የ 8 ወር ልጄ ማልቀስ ጀመረች ። ወደኛ ከመተኮሳቸው በፊት አንድ ታጣቂ ‘ ወደ እዚህ ተመልከት ‘ወደ እዚህ ተመልከት ‘ ሲል ሰማሁት ... ህፃን ልጄን ተኩሰው ገደሉት ። ሬሳውን በለበስኩት ልብስ ሸፈንኩት ። ሌላዋ ልጄ ከጀርባ ተመታች ጥይቱ በአንገቷ አካባቢ ወጣ ። የቆሰለች ልጄን ወደ ደረቴ አስጠግቼ አላህ ህይወቷን እንዲያተርፍልኝ ፀለይኩ “

ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ የኦሮሞ መንግስት ከ200 በላይ ቤተክርስትያኖች ና መስጊዶች አፍርሷል ፕሬዝዳንት ሺመልስ ለክርስቲያን ና ሙስሊም ሃይማኖት መሪዎች በቴሌቪዥን የተቀርፀ ሁለት ገለፃ ሰጥቷል አንደኛው የፈረሱት የአምልኮ ቦታዎች ህገወጥ ግንባታዎች ነበሩ የሚል ነው። የኢትዮጽያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ይህንን ክስ ተቃውሞታል ።

ሁለተኛው የአምልኮ ቦታዎቹ በፈርሱበት መሬት ሰማይ ጠቀስ ህንጻዎች ያሉት የኦሮሞ ታላቅ ከተማ ይገነባል የሚል ነው። ገለፃው ተቃውሞ ሲገጥመው ፕሬዝዳንት ሺመልስ ያስከተለው የሚረብሽ መልስ ነው ‘’ ጠላቶቻችን አላማችን ገብቷቸዋል ‘’ አላማው መስጊዶች ን ና ቤተክርስቲያኖችን ለማፍረስ እንደ ምክንያት አዲስ ታላቅ ልብወለድ ከተማ መጠቀም ነው ። ‘’ ሸገር ከተማ ና ገዳ የኦሮሙማ የሰማይ ቤተመንግስት ቅዠት ናቸው”

በስብሰባው የታደሙ የሃይማኖት መሪዎች ላይ ማሾፍ በሚመስል አይነት ፕሬዝዳንቱ ወደፊት ለመስራት የሚፈቀድላቸው ደረጃቸውን የጠበቁ የውጭ ጎብኝዎችን መሳብ የሚችሉ ህንፃዎችን ብቻ ነው ብለዋቸዋል። ‘’ ትንንሽ ቤተክርስቲያኖች ና መስጊዶች መስራት አይፈቀድም ‘’ሲሉ አስረገጥዉ ተናግረዋል ። የውጭ ጎብኝዎችን የሚስቡ እንደ ቅዱስ ጼጥሮስ ካቴድራል ወይም በዱባይ ክሬክ ሃርቦር ያለው ታላቅ መስጊድ አይነት ካልገነቡ ምንም የማምለኪያ ስፍራ አይኖራቸውም ።

ጉዳዩ የግንባታ ደረጃን መጠበቅ አይደለም ።ድሃ ክርስቲያን ና ሙስሊሞችን በኦሮሞ መሬት የአምልኮ ስፍራ የመከልከል ስልት ነው። በወሎ አንድ አባባል አለ ‘’ ቤተክርስቲያኑ ወይም መስጊዱ ሲያንስ ፈጣሪ ይቀርበናል’’ ቁምነገሩ በቤቱ ያለው መንፈስ ነው እንጂ የህንፃው ማሸብረቅ አይደለም የሚል ነው። ‘

የፕሬዝዳንት ሺመልስ ና የሃይማኖት መሪዎቹ በቴሌቪዥን የተቀርፀ ስብሰባ የሕዝብ ግንኙነት ድራማ ነበር ። በመሬት ላይ ያለው እውነታ በኦሮሞ የሚኖሩ ከርስቲያኖች ና ሙስሊሞች ኢሰብአዊ ለሆነ አሰቃቂ ጭካኔ የተጋለጡ መሆናቸው ነው። አለም ከስብአዊ መብቶች ጥሰት ሪፖርቶች የኦርቶዶክስ ክርስቲያን መሪዎችን ከህግ አግባብ ውጭ ግድያ የቀሳውስትና ኢማሞች መደበደብ አንብቧል ። አረጋዊ ሙስሊም እናት እያለቀሱ በዚህ ከቀጠለ ለመቀበሪያ ቦታ እንኳን አናገኝም በማለት ምህረት ሲለምኑ አለም ሰምቷል ።

አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በምክርቤት መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው ኦሮሞ ያልሆኑ የምክርቤት አባላት ‘’ የአማሮ ህዝብ በሶስት አቅጣጫ በኦሮሞ የተከበበ ነው። ከሌሎች ክልሎች እንዳንገናኝ ተከልክለናል። ሆስፒታሎቻችን ቤተክርስቲያኖቻችን ተቃጥለዋል ። የደረሰብንን መከራ በቃላት ለመግለፅ ያስቸግራል። ተወረናል ፤ ተጨፍጭፈናል ና ጎሳችን የህልውና ስጋት ተጋርጦበታል። ‘’ በማለት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ፍትህ ሲማፀኑ ሰምቷል

ከዚህም የከፋው ምእመናን በፀሎት ና ዝማሬ ላይ እያሉ የመንግስት የፀጥታ ሃይሎች በኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ውስጥ አስለቃሽ ጭስ ሲወረውሩ አለም በድንጋጤ ታዝቧል። እነዚህ ኦሮሙማን ና ዋቄ ፈናን በኢትዮጽያ መንግስታዊ መመሪያዎችና ሃይማኖት ለማድረግ የሚወስዱ ጥቃቅን እርምጃዎች ናቸው።

ፕሬዝዳንት ሺመልስ የኦሮሞ ብልጽግና ለወደፊቷ ኢትዮጽያ ያቀደላት የገዳ ስርዐት ነው ብለው ሲናገሩ ቃላት ለመምረጥ አልተቸገሩም ። ገዳ ሃይማኖታዊ (ዋቄ ፈና) ና ሃይማኖታዊ ያልሆኑ ተግባራትን የያዝ የኦሮሙማ ፍልስፍና መሰረት ና ዋና መመሪያ ነው ። ችግሩ ገዳ በቁራን ና ነቢዩ መሃመድ ትምህርት ከተመሰረተው ከእስልምና ህግ ከሽሪያ ይቃረናል። የፕሮፌሰር ጃለታ አቋም ክርስትና ና እስልምና ከብሄራዊው ኦሮሙማ መስማማት አለባቸው የሚል ነው

ፕሬዝዳንት ሺመልስ በኦሮሞ ጎሳ መሬት የሚኖሩ ክርስቲያኖች ና እስላሞች ኦሮሙማ ከሃይማኖታቸው እንደሚበልጥ መገንዘብ አለባቸው በማለት ይሄንኑ ደግሞታል። ፕሬዝዳንት ሺመልስ በብሄራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው መንግስታቸው በአዲስ አበባ የኦሮሙማን ምልክቶች ለማኖር በቢሊዮኖች እያወጣ ነው ሲሉ አክለዋል። ከአዲስ አበባ ነዋሪ ኦሮም 19 በመቶ ብቻ ነው ።

እ.ኢ.አ በ2007 የሕዝብ ቆጠራ ውጤት ክርስቲያኖች ና እስላሞች በጋራ የአዲስ አበባን ሕዝብ 99 በመቶ ይሆናሉ ። በአንፃሩ የዋቄ ፈና ተከታዮች 0.05 በመቶ ብቻ ናቸው ። ዋቄ ፈና በአዲስ አበባ ድሃጣን ነው። በህዝብ ብዛትም አናሳ ነው። ነገር ግን ክርስቲያኖች ና ሙስሊሞች ወደ ኦሮሙማ ና የኦሮሙማ ሃይማኖት ወደ ሆነው ዋቄ ፈና እንዲዞሩ ተነግሯቸዋል። ይህ የተነገረው ከዋነኞቹ የአሜሪካ ዮኒቨርስቲዎች በአንዱ ድህረ ገፅ ነው።

መጽሃፍ ቅዱስን ክኦሮሞ ማንነት ለማስማማት በሚያደርጉት ጥረት የኦሮሙማ ምሁራን ኢትዮጽያ የሚለውን

በኩሽ በመቀየር አዲስ የመፅሀፍ ቅዱስ ትርጉም አሳትመዋል። ኦሮሙማው መፅሀፍ ቅዱስ ምሳሌ 68፡31 እንዲህ ይነበባል ‘’ኩሽ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች “



 


የኦሮሙማ ኢሰብ አዊነት ሰእላዊ ማሳያ


የኦሮሞ መንግስት ና የኦሮሙማ ወሮበሎች የሚፈፅሙት ወንጀል ጉዳት ለማድረስ ታቅዶ የሚደረግ ነው። (1) በፎቶው የሚታየው የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ የሆነች እናት ና የልጇ ሬሳ ነው። (2) የአምኒስቲ ኢንተርናሺናል ሪፖርት (3) የኢራን ጋዜጣ (ታስኒም) ባለስልጣናት በመቶ የሚቆጠሩ ቤቶች በማፍረሳቸው የተነሳው ቁጣ በሚል ርእስ ያወጣው ዜና ። (4) የክርስቲያኖችን ና ሙስሊሞችን በብዛት መፈናቀል የሚያሳይ (5) በፈረሰ መስጊዳቸው የሚፀልዩ ሙስሊሞች (6)ቤታቸው ከፈረሰና ንብረታቸው ከተጣለ በኋላ ከትንሽ ወንድሟ ጋር በጎዳና የተቀመጠች ህፃን


የኦሮሙማ ወንጀሎች ጭካኔ ምንጭ ና የዘርማጥፋት ምልክቶች


የኦሮሙማ ወንጀሎች ና ኢሰብአዊ ድርጊቶች የሚፈፀሙት በኦሮሞ ወጣት ካድሬዎች ፤ የአካባቢ ታጣቂዎች ና የፖሊስ አባላት ነው ። እነዚህ ቁጣን ና ብቀላን ለማነሳሳት ታስቦ በተደርጉ የዘመናት የኦሮሙማ የውሸት ቅስቀሳ አእምሮቸው የተበረዙ ወጣቶች ናቸው። በጥላቻ የተሞሉ ወጣት ኦሮሞዎች ቤተክርስቲያን ና መስጊድ ሲያዩ የሚታያቸው ‘የኢትዮጽያ ግዛት አስፋፊዎች ና በሃይል የተጫነባቸው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ማንነት ነው ‘’

አብያተ ክርስትያናትን ና መስጊዶችን ሲያዩ የሚያስቡት የኦሮሞ ጠላቶች ክርስትናን ና እስልምናን ለማስተዋወቅ የተጠቀሙት ሶስት ደረጃዎች ያሉት ሂደት የሚለውን የኦሮሙማ ትርክት ነው ።. የመጀመሪያው የኦሮሞን መሬት መውሰድ ነው ‘ መሬቱን መውረር ‘ ። ሁለተኛው በሃይል ወይም ማግባባት የሃገሬውን ሰው አእምሮ ክርስትናን ወይም እስልምናን በመጠቀም መለወጥ ነው ። ወቀሳው ሃይማኖት ኦሮሞን ለማንጻት ና መቀደስ ጥቅም ላይ ውሏል ምክንያቱም የኦሮሞ ህዝቦች እንደ እርኩስ ይቆጠሩ ስለነበር ነው የሚል ነው። ሶስተኛው ና የመጨረሻው ደረጃ ለተወረሩት ህዝቦች አዲስ ታሪክ መፍጠር ነው።

በጥላቻ የተመረዙ ወጣት ኦሮሞዎች ከሰሜን ኢትዮጽያ አካባቢ የመጡ ሰዎችን የሚያዩቸው ኦሮሞን በስነልቦና ለመቆጣጠር ና ለመጨቆን የኦሮሞን ሃይማኖት አጥፍተው እስልምናን ና ክርስትናን የጫኑባቸው የ ቱርክ፣ ሀበሻ፤ አና አውሮፓ ወኪሎች አድርገው ነው

ወጣቶቹ ጠላቶቻቸውን የሚጠሉት አምርረው ነው። ንዴታቸውን ና የበቀል ስሜታቸውን የሚያነሳሱት ‘’ በ 19ኛው ምዕተ አመት መባቻ የጀመረው የኢትዮጽያ የቀኝ አገዛዝ ሽብር ና የዘር ማጥፋት ዛሬም በ 21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቀጥሏል ‘’ የሚለውን የሃሰት ትርክት በማመን ነው ።

በሚኒስትር ማእረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ በ አፕሪል 3,2023 የዛሬይቱ ኢትዮጽያ ሩዋንዳ በዘር

ማጥፋት ዋዜማ በነበረችበት መስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛለች ሲሉ አለምን ያስጠነቀቁት ትክክል ነበር።


ከሚኒስትሩ መግለጫ ጥቂት ጊዜ በኋላ ለምኪን ኢንስቲትዩት ፎር ጄኖሳይድ ፕረቨንሽን ‘’ አማራዎች


(ኦሮሙማ ቀንደኛ ጠላት የሚሏቸው ህዝቦች) በቀላሉ ወደ ዘር ፍጅት ሊቀየር የሚችል አደገኛ መስመር ላይ


ይገኛሉ’’ በማለት አፅንኦት ሰጥቶ ለዘር ማጥፋት ወንጀል የቀይ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል ።

ኦሮሙማ ጉዳት ያደረሰው በክርስትያን ና እስላም ላይ ብቻ አይደለም የመረዛቸው ና ወደ ዞምቤ ገዳይ የቀየራቸው የኦሮሞ ወጣቶች እንዲሁ ተጠቂ ናቸው።


አለም አቀፍ ጫና ብቸኛው አማራጭ ነው


ከሩዋንዳ የዘር ፍጅት በኋላ አለም አቀፉ ማህበረስብ ‘’አይደገምም ‘’ ሲል ቃል ገብቶ ነበር። የሩዋንዳ የዘር ፍጅት በፍጥነት የተፈፀመ ነው ። የኦሮሙማ የዘር ፍጅት ቀስ በቀስ እየተብላላ ነው። አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጣልቃ የመግባት የሞራል ሃላፊነት አለበት ። ቀደም ብለው በተጠቀሱት ምክንያቶች አለም አቀፍ ማህበረሰቡ የአፍሪካን ቀንድ መረጋጋት የሚፈልግበት ፖለቲካዊ ና ከባቢያዊ ፍላጎቶች አሉት ።

እየተባባሰ የመጣውን የኢኮኖሚ ቀውስ ና የኦሮሙማ የሃይማኖት የዘር ፍጅት የሚያስከትል ጦርነት ለማስቆም የሚያስችሉ አዋጭ እርምጃዎችን ከማየታችን በፊት ሁለት ወሳኝ ነጥቦችን መረዳት ይኖርብናል ። የመጀመሪያው መሰረታዊ ነጥብ ጠቅላይ ሚኒስትሩና የኦሮሙማ አስተሳሰብ መሪዎች ፍላጎታቸውን ለማሳካት ያላቸውን ኃይል ሁሉ እየተጠቀሙ መሆኑ ነው። ለኢኮኖሚው መውደቅ ና እየቀረበ ለመጣው የኦሮሙማ ዘር ፍጅት ምልክቶች በፍጥነት እየታዩ ነው።

ሁለተኛው ኢትዮጽያውያን በሁለት ግንባር በኢኮኖሚው ና ሃይማኖት ንቅናቄ ማድረግ ይገባቸዋል የሃይማኖቱ ያለፖለቲካ አክቲቪስቶች ጣልቃ ገብነት በሃይማኖት ተቋማት ብቻ መመራት አለበት የኢኮኖሚው ንቅናቄ ከሃይማኖቱ ተለይቶ መደረግ አለበት አለም አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ና ሃይማኖታዊ ንቅናቄዎች አትኩሮት እንደሚስቡ ማስታወስ ያሻል።


ኢኮኖሚው


ኢኮኖሚው ቀስ በቀስ ከውስጥ ወደ ውጭ እየፈረሰ ነው ። የኢኮኖሚው እያንዳንዱ ክፍል የሞት ጣር ላይ ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት ቀውሱ በከፍተኛ መጠን በፍጥነት ሲባባስ እየታዘብን ነው። መንግስቱ የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በጥይት ና በጅምላ እስር ለማፈን ይሞክራል ።

እንደ የኢትዮጽያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መንግስቱ የውሃ አቅርቦት ለወራት ከተቋረጠ በኋላ የውሃ እጥረት በማጋጠሙ ሰልፍ የወጡ ስዎችን ተኩሶ ገድሏል። የኮሚሽኑ ረፖርት እንዳመለከተው ‘’ሶስት ሰዎች በጭንቅላታቸው ና በደረታቸው ላይ በጥይት ተመተው ሞተዋል። እንዲሁም ከ30 በላይ ሰዎች በተለያየ ደረጃ ቆስለዋል ‘’

በተመሳሳይ የአዲስ ስታንደርድ ሪፖርት ፖሊስ በደቡብ ህዝቦች ክልል ሃድያ ዞን መንግስት የሶስት ወር ደመዎዝ ባለመክፈሉ ሰልፍ በወጡ የመንግስት ሰራተኞች ላይ ድብደባ ፈጽሟል ። ሪፖርቱ አንድ የአይን እማኝ መረጃ ይዞ ወጥቷል ‘’ ሰልፉን ለመበተን በፖሊስ ክፉኛ የተደበደቡ ሶስት ሰዎች ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል ‘’ በተቃውሞው ሳቢይ ከ 40 በላይ ሰዎች ታስረዋል ።

በተጨማሪም በኑሮ ውድነት የተነሳ የሚጠየቁ የደመወዝ ጭማሪ ተቃውሞዎች በድንብ ና ማስፈራሪያ ይከለከላሉ። የኢኮኖሚ ቀውሱ ሀገሪቱን ና የቀንዱን አካባቢ ወደ ኢኮኖሚ ውድመት ሊያስገባቸው ጫፍ ደርሷል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእርምት እርምጃ እንዲወስዱ ለማስገደድ የገንዘብ አቅም ያለው ብቸኛው ሃይል አለም አቀፉ ማህበረስብ ነው ።

የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ዋና መሳሪያ ማእቀብ ነው ። ሰብአዊ እርዳታ ሲቀር ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ መዋል አለበት ። አንዳንድ ሰዎች ማእቀብ ከገደል አፋፍ ያለውን ኢኮኖሚ ክፉኛ ይጎዳዋል ይላሉ ‘ ያልተረዱት ጉዳይ ጣልቃገብነቱ ከቀረ ኢኮኖሚው እንደሚጠፋ ነው። እኔ የማምነው ‘’ የተመርጡ ማእቀቦችን መጣል የሚያመጣው ጉዳት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጀመሩት መንገድ ሄደው ከሚመጣው የኢኮኖሚ አጠቃላይ ውድቀት ያነሰ ነው።’’

ማእቀብ በጣም አስፈላጊ የሆነውን የውጭ ምንዛሪ በማሳጣት የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጉራ ና ቅዥት ፕሮጀክቶች ለማሰናከል ብቸኛው አዋጪ አማራጭ ነው ። የሀገሪቱን ሀብት ወደ ምርታማ የኢኮኖሚ ክፍሎች በማዞር ኢኮኖሚውን ከአጠቃላይ ውድቀት ወደ ማገገም ማምጣት ያስችለናል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከትህነግ ጋር የሰላም ስምምነት ሲፈራረም ። ከኦሮሙማ ሸኔ ጋር ለድርድር ሲቀመጥ አይተናል ማእቀብ አይሰራም ና እንደ አማራጭ መወሰድ የለበትም የሚለው ጅላ ጅል ሃሳብ ነው ። ማስተካከያ

፤ከ ደነዞቹ ‘’
https://amharic-zehabesha.com/archives/183850
https://youtu.be/e0geyhPOpOw

በአማራ ክልል ለሶስት ቀናት የሚቆይ አድማ ተጠራ
https://amharic-zehabesha.com/archives/183847
https://youtu.be/e0geyhPOpOw

በአማራ ክልል ለሶስት ቀናት የሚቆይ አድማ ተጠራ
https://amharic-zehabesha.com/archives/183847
Ethiopia: More turbulence ahead for Ethiopian Airlines
The imminent ousting of Mesfin Tasew Bekele, who has been CEO of Ethiopian Airlines since March 2022, prompted the chairman of the board Girma Wake to step down unexpectedly last week.

Published on 22/06/2023 at 04:40 GMT Reading time 2 minutes

The resignation earlier this month of Girma Wake as chairman of Ethiopian Airlines (EAL) was as sudden as it was unexpected, even if it came on the heels of weeks of behind-the-scenes wrangling between him and the company's sole shareholder, the Ethiopian state. Girma disapproved of the decision to replace CEO Mesfin Tasew Bekele with commercial director Lemma Yadecha, whom Girma considered too inexperienced. The departure of Mesfin, who was made CEO in March 2022 (AI, 20/05/22), is said to be imminent.

Ethiopian Airlines' 11 June statement announcing Girma's resignation - three days after it took place - offered no explanation for his departure and Girma himself has not given a reason. The company did not reply to our request for comment. A key player in Africa's leading airline, Girma was recalled to its board in 2018 and appointed chairman a year ago by Prime Minister Abiy Ahmed.

Serial departures

After last year's resignation of long-standing CEO Tewolde Gebremariam, Girma's return was meant to steady the airline's course, and many expected him to stay on for a while. The octogenarian has a 30-year history with EAL, including as CEO between 2004 and 2011. He was immediately replaced as chairman by Lieutenant General Yilma Merdasa, who had been on the board since January 2021 after commanding Ethiopia's air force since 2018.

Tewolde's departure plunged EAL into a period of turbulence from which the company is struggling to emerge. Several people close to Girma took advantage of the instability to climb the EAL ladder. Chief operating officer (COO) Mesfin Biru replaced Nigusu Worku as the head of the airline's international services, and Retta Melaku, a middle manager, became COO. Lemma Yadecha himself seized the opportunity to replace Esayas Woldemariam, who was dismissed in April 2022, as commercial director. However, this regional executive, who has held EAL positions in Malaysia, Burkina Faso and France, still has little experience in the upper echelons of the airline.

Africa Intelligence.

 
https://zehabesha.com/ethiopia-more-turbulence-ahead-for-ethiopian-airlines/
The International Community Must Express Ourtrage Now: Torture of Amhara must stop
The below video from Anchor Media shows the level of atrocities and savagery inflicted on Amhara Political prisoners in Ethiopia. These atrocities under the watch of Prime Minister Abiy Ahmed are reminiscent of  the  torture chambers under the TPLF, this time inficted on Amhara prisoners including women by the Oromo Prospetiy Party comandeered Special Task force consisting solely Afaan Oromo speakers.

Torture includes electric shocks, clubbing, pulling finger nails, psychological torture forcing political prsioners to disclose connections and agencies.as well as other forms of incpacitation in the wee hours of night at a special prison camp called Gelan. Victims include Amhara female journalists, writers and opinion makers, civil society leaders.

Anchor media confirms these atrocities based on hand written letters of appeal from prisoners. It is hard to describe the level of brutality and savagery. One female prisoner continues to bleed.

No one really knows the number of Amhara potical prisoners in Ethiopia's torture cambers. It is in the thousands.

I urge you to send letters to Senators,Congressmen and women, academics, government officials, the UN, human rights agencies, the African Union and others urging them to express outrage.

The international community must be made to understand that in today's Ethiopia, it is virtually impossible to defend rights peacefully.Do your part please.

 

Aklog Birara DR.

 
https://zehabesha.com/the-international-community-must-express-ourtrage-now-torture-of-amhara-must-stop/

Saturday, June 24, 2023

https://youtu.be/dGSCHmjmOj0

በእስር ላይ የሚገኙ የአማራ ተወላጆች ላይ ከፍተኛ ቶርቸር እየተፈጸመ ነው። ከማጎሪያ እስር ቤት ከእስረኞች የተላከ መልዕክት
https://amharic-zehabesha.com/archives/183836
600 የሚሆኑት ማስጠንቀቂይ ተሰጣቸው! መከላከያ በአማኑኤል መወጫ አጥተዋል!|የአማራ ድምጽ ዜና
https://youtu.be/qmbGg-2L3Oo

 

600 የሚሆኑት ማስጠንቀቂይ ተሰጣቸው! መከላከያ በአማኑኤል መወጫ አጥተዋል!|የአማራ ድምጽ ዜና

https://youtu.be/cz4U58fUfho

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/183829
600 የሚሆኑት ማስጠንቀቂይ ተሰጣቸው! መከላከያ በአማኑኤል መወጫ አጥተዋል!|የአማራ ድምጽ ዜና
https://youtu.be/qmbGg-2L3Oo

 

600 የሚሆኑት ማስጠንቀቂይ ተሰጣቸው! መከላከያ በአማኑኤል መወጫ አጥተዋል!|የአማራ ድምጽ ዜና

https://youtu.be/cz4U58fUfho

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/183829
The Horn of Africa States A Regional Perspective
By Dr. Suleiman Walhad

June 20th, 2023

The collapse of the old ruling elites in the Horn of Africa States region, gave rise to the present elite. They rose out of the chaos that followed the collapse of the old military regimes, which themselves, replaced the older either kingly or republican parties, and who adopted socialism as the hallmark of their administrations. Tribal and ethnic based opposition parties generally led the oppositions to the ruling socialist military parties, which collapsed with the Ex-Soviet Republics and in general the left parties of those bygone days. They took advantage of the political chaos that followed the collapse of the military regimes to come to power and further weakened governmental institutions of the two main countries of the region, namely Ethiopia and Somalia.

Ethiopia gave independence to Eritrea, while Somalia splintered into a multitude of clan fiefdoms owned by some of the main clans of the Somali population. Ethiopia further adopted a federal infrastructure based on ethnic tribes and languages, while Somalia broke down into its large array of clans and sub-clans. The elites of the new tribal/clan regimes of Ethiopia and Somalia created an ecosystem of inequalities and where citizens have become divided into first-class and second-class citizens. They, indeed, have become predatory and leaders of chaos, which makes the Horn of Africa States region become prey to other forces from beyond. The remaining two countries of the region and namely Eritrea and Djibouti both remain under the control of single parties.

There appears to be in the region, despite its wishes otherwise, a lack of knowledge of general governance and the workings of politics, which is currently abused through tribal/clan prisms. There also seem to be no clear vision for any of the countries other than to keeping the existing tribal/clan regimes on even keels.  There, indeed, is no vision for the region let alone the constituent SEED countries. These two factors contribute to dispersal and/or distancing from circles of governance, of experts and knowledgeable people in all fields in the states of the region. This, therefore, allows reliance by the regimes on consultancies from others from beyond the region, mostly NGOs, who have their own agendas for the region. This culminates in keeping the region as chaotic as it can be, which allows the unscrupulous to exploit its resources and/or prevents exploitation of the resources such as a potentially thriving tourism the region could have enjoyed, let alone its natural resources.

Perhaps the region’s experts and knowledgeable people of the region, individually and/or collectively did not offer their help to the regimes and fled the scene, and the regimes could not, therefore, be blamed for all that is going on, in the countries, and for the interferences of others. This could have been out of fear or simply a search for greener pastures. In either case, the regimes lost most of those who could have had institutional memories and the workings of efficient administrative systems.

Sadly cronyism, incompetence, corruption and indeed, tribal/clan dominances which have replaced the old regimes seem not to be much different from the systems they intended to replace. The region, indeed, needs to revisit itself and rework the scaffold of management. All could participate if, in all honesty, people started thinking and acting in terms of individuals and not in terms of the collective tribe and/or clan, where the most competent could be given the reigns and helped in executing the good ideas they may come up with.

A series of regional conferences and meetings at many levels, be they governmental, academia or business or simply civil societies could be encouraged to take place, instead of letting things take their own course. But then, it is always up to the leadership of each country to allow such events without taking offense. They would probably leave their names in the pages of history for the good they did in their times instead of the bad they did. The politics of tribalism/clannism and their accompanying corruption-cum-cronyism could be reviewed and replaced by a more nationalistic regional aura. One must, however, note that the region does not have the luxury of time to experiment with new thought processes. What the region needs today is to have the current leadership of the region take the bull by the horns and reform their own regimes from within and thence create a regional collective together.

The regimes of the Horn of Africa States, face an increasingly polarised world where the West is fighting to maintain its traditional hegemony and the Chinese, Russia and other emerging powers like India seem to be on the rise. For the Horn of Africa States and for Africa, in this respect, neither holds the best interest of the region at heart. In the case of the West, one notes that they, indeed, offer political alliances-cum-support but do not offer any economic dividends. They would not like the Horn of Africa States or for that matter the African continent rise. This still remains anthemic to the West. In a sum total, a political alliance minus economic support amounts to nil at the end of that simple arithmetic.

The Chinese and the other major rising powers, on the other hand, offer economic support, in terms of infrastructures such as rail, roads and bridges, airports and seaports but political alienation from the rest of the world and would not come to defend the region or Africa. The story of Sudan should not be forgotten. China will choose where its interests lie. This amounts to an economic support minus political support which amounts, at the end of the day to zero, in the same simple arithmetic.

It is where the necessity for a Horn of Africa States regional block becomes necessary to harness, not only its geopolitical situation but also its geoeconomic advantages. Indeed, the region is situated in a geostrategic location coveted by all and there is no need why the region cannot collectively work together to take advantage of this opportunity without unduly stressing anyone. The current single-state format of the region and hence approach to handling global issues of which the Horn of Africa States as a region would always be a part because of its location, does not represent a workable and successful structure. It is where the necessity for creating a collective Horn of Africa States institution is not only required but a necessity. What we see missing is leadership taking initiatives in this regard and/or mistrust created by none other than those who milk the region in its current format.

There is no reason why there should not winning solutions for all the countries of the region. The region enjoys a large and growing young population which represents a large market. It has resources in terms of agricultural lands and marine foods which if properly exploited could feed not only the growing population of the region but also millions more into the distant future. The region also enjoys a large mineral base including oil and gas, lithium, diamonds, platinum, iron ore, potassium, uranium, rare earths and many more, and above all, a year-round good weather, where one does not really need to drastically change clothing apparel for hot and cold weathers. It is, indeed, a tourist paradise with its blue seas and towering mountains and savannah country. Of course, it also has desertic and semi-desert environments which add to its beauty, in their own ways.

At literally the centre of east/west air travel, it could also become a world-renowned stopover for people travelling from east to west and vice versa and stopovers for yachting people and cruisers. The region is centrally located and could become a reasonably tourist destination for many who want to escape the cold weathers or even the hot weathers. And for producing, the region provides a large cheap labor which can be easily trained into any industrial production.

A regional infrastructure would create many opportunities for the populations of the region but most of all peace and stability, which have been missing from the region for a long time. The leadership of the region owes the populations this dividend and they should be working towards this goal without rest and without respite. It is what they can offer the region’s population, at least.

 

 
https://zehabesha.com/the-horn-of-africa-states-a-regional-perspective/

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...