Thursday, November 30, 2023

https://youtu.be/54yzd9QlzC8?si=Auv3iS16oYkNK02z

 

ደረጀ እሸቱ እየመጣን ነው-
https://amharic-zehabesha.com/archives/187457
https://youtu.be/54yzd9QlzC8?si=Auv3iS16oYkNK02z

 

ደረጀ እሸቱ እየመጣን ነው-
https://amharic-zehabesha.com/archives/187457

Wednesday, November 29, 2023

ያማራ የሕልውና ችግር ሁለቱ ምንጮችና ዘላቂ መፍትሔው
ያማራን ሕልውና እጅጉን እየተፈታተኑ ያሉት ጭራቅ አሕመድና መሰሎቹ የበሽታ ምልክቶች እንጅ በሽቶች አይደሉም።   በሽታወቹ ደግሞ ጭራቅ አሕመድንና መሰሎቹን በላዔ አማራወች ያፈለቁት ሁለቱ ፀራማራ ምንጮች ናቸው።  ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለዘለቄታው ማረጋገጥ የሚችለው እነዚህን ሁለት ፀራማራ ምንጮች ለዘላለም ካደረቀና ካደረቀ ብቻ ነው።  ያማራ ሕዝብ ለዘላለም ሊያደርቃቸው የሚገባ ጭራቅ አሕመድንና መሰሉቹን ያፈለቁት ሁለቱ ፀራማራ ምንጮች ደግሞ የሰውና የቦታ ስያሜወችን የተመለከቱ ናቸው።

ሰብዓዊነት የሚባል ምናምኒትም ስላልፈጠረበት ከእንስሳ ሊቆጠር የሚችለው አረመኔው የገዳ ጨፍጫፊ ሠራዊት በግራኝ አሕመድ ጦርነት የተዳከመውን ያማራን ሕዝብ እየጨፈጨፈ ባማራ ግዛት ላይ ሲስፋፋ፣ ከጭፍጨፋው የተረፉትን አማሮች በሞጋሳና በጉዲፈቻ ዘዴ የኦሮሞ ስም እየለጠፈ ኦሮሞ ናቸሁ አላቸው።  የተስፋፋባቸውን ያማራ ግዛቶች ደግሞ በነገዱና በጎሳው እየሰየመ የኦሮሞ ናቸው አላቸው።  ያማራ የሕልውና ችግር የሚመነጨው ከነዚህ ሁለት ምንጮች ነው።

አያቶቻችን ከለማበት የተጋባበት እንዲሉ፣ የኦሮሞ ነጻነት ታጋዮች ነን በማለት ዛሬ ላይ ያማራን ሕዝብ ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱት እውነተኞቹ የቦረና ኦሮሞወች ሳይሆኑ፣ ኦሮሞነት በስም እንጅ በደም የሌለባቸው ጭራቅ አሕመድ፣ ለማ መገርሳ፣ ሽመልስ አብዲሳ፣ ዳውድ ኢብሳ፣ መራራ ጉዲና፣ በቀለ ገርባ፣ ጃዋር ሙሐመድና መሰሎቻቸው ናቸው።  እነዚህ የቁጩ ኦሮሞወች ያማራን ሕዝብ ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱት ደግሞ የኦሮሞ ያልሆኑትን ቦታወች በኦሮሞኛ ስለተሰየሙ ብቻ የኦሮሞና የኦሮሞ ብቻ ናቸው በማለት ነው።

የቦታወችን ስያሜወች በተመለከተ መፍትሔው ላማራ የሕልውና ትግል ያጭር ጊዜ ሥራ ነው።  ያማራ ሕዝብ በመራራ ትግሉ የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግስት አስወግዶ ጭራቅ አሕመድንና ግብራበሮቹን (በተለይም ደግሞ የአብን፣ የኢዜማና እና የብአዴን ግብራበሮቹን) ማስተማሪያ በሚሆን መንገድ አይቀጡ ቅጣት ከቀጣ በኋላ የጦቢያን ሐገረ መንግሥት እንደገና ሲያቋቁም፣ ተስፋፊው የገዳ ሠራዊት ያወጣቸውን የመስፋፋት ስሞች (ውሎ፣ ወራኢሉ፣ ጉለሌ፣ ሰላሌ ወዘተ ) አንዳችውም ሳይቀሩ ሁሉንም በሕጋዊ መንገድ ላንዴና ለመጨራሻ ጊዜ ማጥፋትና ሁሉንም ቦታወች በቀድሞ ስማቸው መሰየም አለበት።  ለምሳሌ ያህል ጨፍጫፊው የገዳ ሠራዊት ባወጣለት የጭፍጨፋ ስሙ ወሎ የሚባለውን ቤታማራን ወሎ ብሎ በኦፊሴል (officially) መጥራት በጭፍጨፋ መስፋፋትን ከመደገፍ የሚያስቆጥር ከባድ ወንጀል መሆንና ከባድ ቀጣት ማስከትል አለበት።  አልኦፌሴል (non-officially ማለትም ባዘቦት ንግግር ላይ) ቤታማራን ወሎ ብሎ መጥራት ደግሞ ተናጋሪውን ማሳፈርና ማሽማቅቅ አለበት።

የሰወችን ስያሜወች በተመለከተ ግን መፍትሔው ላማራ የሕልውና ትግል የመቶ ዓመት ሥራ ነው።  ያማራ ሕዝብ የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግሥት ካስወገደ በኋላ ሕልውናውን በተመለከት ትልቁ ሥራው መሆን ያለበት የሚከተለው ነው። እሱም ኦሮሞ ነው ከሚባለው ሰፊ ሕዝብ ውስጥ ከዘጠና በመቶው በላይ ኦሮሞ እንዳልሆነ፣ የኦሮሞ ስም ስለተለጠፋባቸው ብቻ ኦሮሞ ነን ብለው እንዲያምኑ የተደረጉትን ሚሊዮኖች ወደ እውነተኛ ማንነታቸው በራሳቸው ፈቃድ እንዲመለሱና፣ ያለስማቸው ስም የሰጣቸውን የኦሮሙማ አስተሳሰብ እንዲጸየፉትና በጽኑ እንዲዋጉት ማድረግ ነው።  ይህ ማድረግ ደግሞ እያንዳንዱን አዲስ ትውልድ በከፍተኛ ትግስትና ትጋት ሳያሰልሱ ማስተማርን የሚጠይቅ የዘመናት ፕሮጀክት ነው።

አጼ ሚኒሊክ ያማራን ግዛቶች እንዳስመልሱ፣ አረመኔው የገዳ ሠራዊት የፈጠራቸውን የሰውና የቦታ የጭፍጨፋ ስሞች በቀላሉ ማጥፋት ይችሉ ነበር።  ይህን አድርገው ቢሆን ኖሮ ደግሞ ወሎ፣ ወረኢሉ፣ ጉለሌ፣ ሰላሌ የሚባሉ፣ አሁን ላይ አማራን ለመጨፍጨፍ የሚያገለግሉ ቃሎች ከመቶ ዓምታት በፊት ድምጥማጣችው በጠፋ ነበር።  ለማ መገርሳና ሽመልስ አብዲሳ የሚባሉ፣ ኦሮሞ ሳይሆኑ ከእውነተኛ ኦሮሞወች በላይ ኦሮሞ ነን የሚሉ፣ ባማራ ጥላቻ ያበዱ የማንነት በሽተኞች ባልተፈጠሩ ነበር።

አጼ ምኒሊክ ግን በቀላሉ ማድረግ ይችሉት የነበረውን ባንድም በሌላም ምክኒያት (ምናልባትም ደግሞ የጨፍጫፊን ስያሜ መቀበል ለጨፍጫፊ የልብ ልብ ከመስጠት ሊቆጠር እንደሚችል ስላልታያቸው) ሳያደርጉት ቀሩ።  ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለዘላለም ማረጋገጥ የሚችለው፣ አጼ ምኒሊክ የጀመሩትን መንገድ በመጨረስ፣ ጨፍጫፊው የፈጠራቸውን የጭፍጨፋ ስሞች አንዳቸውም ሳይቀሩ ሁሉንም ለዘላለም በማጥፋት ብቻ ነው።  ይህን ሲያደርግ የኦሮሙማ ምንጭ ለዘላለሙ ስለሚደርቅ፣ ኦነግና መሰሎቹ በሂደት ይከስማሉ፣ ያማራ ሕዝብ የሕልውና ችግርም መችም እንዳይመለስ ሁኖ ከምንጩ ይወገዳል።   ነገር ከፍንጩ፣ ውሃ ከምንጩ።

 

ያማራ ሐለወት አደጋ ላይ ወድቆ፣ እየተቀበረ በማሽን ተዝቆ፣

ጽንፈኛ ኦሮሞ ጉቱም ሆነ ዋቆ፣ ይቀየማል ብሎ ማውራት ተጠንቅቆ

ትርፉ መዋረድ ነው ፈሪ አስብሎ አስንቆ፡፡

 

ኦነግ ቄሮን ሲግት ያኖሌን ፈጠራ፣ የሉባን ጭፍጨፋ ማለት አይወራ፣

ሜዳውን በመተው ላባዱላ ሤራ፣ ትርፉ ማባባስ ነው ያማራን መከራ፡፡

 

ሱማሌ በጅራፍ ያስወጣው ከኦሞ፣ የሉባው ሠራዊት የገዳው ኦሮሞ፣

ሐበሻን ሲያገኘው በግራኝ ተዳክሞ፣ ጨለማ ተላብሶ እያረደ አጋድሞ፣

ባበሻ ምድር ላይ በያቅጣጫው ተሞ፣ የተንሰራፋ ነው እንደ አረማሞ፡፡

 

በጦቢያ ምድር ላይ ከጣና እስከ ጫሞ፣ በኦሮምኛ ቃል ያለ ተሰይሞ

ከመስፋፋት በፊት ሁሉም አስቀድሞ፣ አይደለም ኦሮሞ ወይም የኦሮሞ፡፡

 

በስሙ ኦሮሞ ከሆነው ሕዝብ ላይ፣ ዘጠና በመቶ ወይም ከዚያ በላይ

በደሙ ያይደለ ብሔሩን የረሳ፣ ወይ ጉዲፈቻ ነው አለያም ሞጋሳ።

 

በስሙ ቢባልም ኤጀርሳ፣ ኤለሞ፣ በደሙ ያልሆነ ሐበሻና ጋሞ

እንዲሁም ወላይታ፣ ሐድያ፣ ሲዳሞ፣ እስኪ ተናገሩ የቱ ነው ኦሮሞ?

 

ሽመልስ አብዲሳ ያልተገራው ስዱ፣ ነፍጠኛን ሰበርነው ሲል እንደልማዱ፣

የቦረና ውልዱ ሳለ የምጣዱ፣ አትንጣጣ በሉት አንተ የሰፌዱ፡፡

 

ኦሮሞን አይተነው በዚህ ረገድ ዓይን፣ ሕዝቡን ስንመዝነው በትክክል ሚዛን፣

መሆን ይቅርና የጦቢያ ብዙሃን፣ እጅግ ያነሰ ነው ከሁሉም ሕዳጣን፡፡

 

ኬኛ፣ ኬኛ እያለ ራሱን በማግለል፣ ከጦቢያ ብሔሮች እኔ በመነጠል

ካልፈጠርኩኝ ካለ የኦሮሞ ክልል፣ ባሌም አይገባው ላሥር ሳይከፈል፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com
https://amharic-zehabesha.com/archives/187442
https://youtu.be/upHQom17F3c?si=DatJZBiZCsRQCaMx

የአብይ የጦር መሳሪያ ልመና፥ የአማራ ህዝብ ተጋድሎ፥ ሰሜን ሸዋ ምን አለ፥ የአሜሪካን አምባሳደርና 'ፊንፊኔ' ፥ የአዲስ አበባ ንቅናቄ
https://amharic-zehabesha.com/archives/187453
https://youtu.be/upHQom17F3c?si=DatJZBiZCsRQCaMx

የአብይ የጦር መሳሪያ ልመና፥ የአማራ ህዝብ ተጋድሎ፥ ሰሜን ሸዋ ምን አለ፥ የአሜሪካን አምባሳደርና 'ፊንፊኔ' ፥ የአዲስ አበባ ንቅናቄ
https://amharic-zehabesha.com/archives/187453

Tuesday, November 28, 2023

https://youtu.be/hWkgGfhCom4?si=ZnNKiLFcu9pV3wGI

ሰበር የድል ዜና! ሰሜን ሸዋ አጣየ/ ይሙሎ! "ሰራዊቱ እረግፏል" The Voice of Amhara Daily News
https://amharic-zehabesha.com/archives/187436
https://youtu.be/hWkgGfhCom4?si=ZnNKiLFcu9pV3wGI

ሰበር የድል ዜና! ሰሜን ሸዋ አጣየ/ ይሙሎ! "ሰራዊቱ እረግፏል" The Voice of Amhara Daily News
https://amharic-zehabesha.com/archives/187436

Monday, November 27, 2023

የሃይማኖት ጉዳይ ሊያስጨንቀን የሚገባው ለምድነው?
November 25, 2023

ጠገናው ጎሹ

ለዚህ አስተያየቴ ይህንን ርዕስ የመረጥኩት ስለ ሃይማኖት ምንነትና እንዴትነት ለማስተማር ወይም ለመስበክ አይደለም። ለማድረግ ብፈልግም ለዚህ የሚያበቃ እውቀቱና ችሎታውም ስለሌለኝ አላደርገውም።

ታዲያ ለምንድነው?  የሚል ጥያቄ ስለሚነሳና መነሳቱም ተገቢ ስለሆነ ይህንኑ ግልፅ ለማድረግ አስተያየቴን በጥያቄ መልክ በማቅረብ መልሱን ሃይማኖትን ጨምሮ መሠረታዊ ሰብአዊ መብት ፣ ነፃነት፣ ፍትህ (ዴሞክራሲ) ፣ ሰላም፣ ፍቅር ፣ የጋራ እድገት ፣ ወዘተ የሚረጋገጥበትና የሚከበርበት ሥርዓት እውን እንዲሆን ከምር ለሚሹ ወገኖች እተወዋለሁ።

ስለምንከተላቸው የሃይማኖት ተቋማት ነፃነትና ስኬታማነት ስንነጋገር ከምንኖርበት (ከምንገኝበት) የፖለቲካ ሥረዓት ለምንነት ፣ ለማንነት  ፣ እንዴትነት እና ከየት ወደ የትነት አንፃር መሆኑን መዘንጋት የለብንም።

 

እናም ልቀጥል፦

1)   ከማሰቢያ ረቂቅ አእምሮና ከማከናወኛ ብቁ አካል ጋር በክርስቶስ አምሳል የተፈጠረ ሰብአዊ ፍጡር ከፈጣሪው እርዳታ ጋር መሠረታዊ መብቱ ተጠብቆ፣ እርስ በርሱም ተከባብሮ፣ ተረደዳቶ ፣ ተፋቅሮ፣ ሰላምን ተንከባክቦ ፣ በጋራ በልፅጎ ፣ ወዘተ እንዲኖር እና እነዚሁ ወርቃማ እሴቶቹ ከሞት በኋላ ተስፋ ለሚያደርገው ህይወት ስንቅ እንዲሆኑት መርዳትና ማስቻል የሃይማኖት ዓላማና ግብ ካልሆነ ሌላ ምን?

 

2)   እነዚህን እጅግ መሠረታዊ እሴቶች ለምድራዊውና ተስፋ ለሚያደርገው የዚያኛው ዓለም ህይወት ስኬታማነት በአግባቡ ይጠቀምባቸው ዘንድ በነፃነት እና በራስ መተማመን አቋምና ቁመና እንዳይነቀሳቀስ (ጥረት እንዳያደርግ) የሚያሰናክሉ ወይም የሚከለክሉ እኩያን ገዥዎችና ግብረ በላዎቻቸው የሚፈፅሙትን እጅግ ክፉ ፖለቲካ ወለድ ወንጀል አቁመውና ንስሃ ገብተው የህዝብ መከራና ውርደት አብቅቶ ለሁሉም የሚበጅ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ይሆን ዘንድ ሚያደርገውን ተጋድሎ እንዲያግዙ ከምር የሚቆጣና የሚመክር እና አስፈላጊም ከሆነ አስፈላጊውን መስዋእትነት ለመቀበል ፈቃደኛና ዝግጁ የሆነ  አመራር የማፍራትና የማሠማራት ሃላፊነትን መወጣት የሃይማኖት ተቋማት መሠረታዊ ተልእኮ ካልሆነ ሌላ ለምንና ለማን ?  

 

3)   እርግጥ ነው ይህንን እውን ለማድረግ መንገዱ አልጋ ባልጋ አይሆንም። ሃይማኖትን ጨምሮ መሠረታዊ መብቶች በተጠየቁ ቁጥር ሥልጣነ መንበራቸው ሥጋት ላይ የወደቀ እየመሰላቸው ነፃነትና ፍትህ በሚጠይቀው መከረኛ ህዝብ ላይ የጭካኔ ሰይፋቸውን የሚመዙ እኩያን ገዥዎችን አግባብነት ባለውና በማይታጠፍ መንፈሳዊ መሪነት መጋፈጥ የግድ መሆኑን ተረድቶና ተቀብሎ የእረኝነት ሃላፊነትንና ተልእኮን የመወጣት ጉዳይ የሃየማኖት መሪዎች ካልሆነ ሌላ የምንና የማን?

 

4)   በእኩያን ገዥዎች ፖለቲካ ወለድ ወንጀል ምክንያት በግፍ ግድያ፣ ከገዛ አገር በመፈናቀል ፣ በጅምላ ግዞትና እስር ፣ በርሃብ ቸነፈር ፣ በእርዛት አለንጋ ፣ የወላድ መካን በመሆን ሁለንተናዊ ስቃይ ፣በወላጅ አልባነት መሪር ሰቆቃ ፣ እና በአጠቃላይ ለመግለፅ በሚያስቸግር የውድቀት አዙሪት  ውስጥ በመጓጎጥ ላይ ለሚገኝን መከረኛ ህዝብ ቀድሞ የመድረስ ሃላፊነት ካለባቸው ወገኖች መካከል የሃይማኖት መሪዎችና ሊቃውንት ዋነኞቹ  ካልሆኑ ሃይማኖት ለምንና ለነማን?

 

5)   በዚህ ረገድ ከዘመን ዘመን ከመሻሻል ይልቅ በእጅጉ እየባሰበት የመጣው ውድቀታችን አይደለም ወይ ሃይማኖቶቻችን ከፍተኛ ፈተና ላይ እየጣላቸው የሚገኘው? ይህንን እጅግ አሳሳቢና አስፈሪ ሁኔታ በጥሞና እና አርአያነትን በተላበሰ የሃይማኖት አርበኝነት ማስተካከል የሚገባቸው የሃይማኖት መሪዎችና ሊቃውንት ራሳቸው ሆነው ሳለ በሥልጣነ መንበር ላይ እየተፈራረቁ  የመከራውንና የውርደቱን ዘመን በአስከፊ ሁኔታ እያራዘሙ ካሉት ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች ጋር  እየተሻሹ ዘመን ጠገብ የሆነውንና የማይደፈረውን ሃይማኖታዊ  ዶግማና ቀኖና በአፍ ጢሙ ሲደፉትና ሲያስደፉት ማየትና መስማት የሃይማኖት ምንነትንና እንዴትነትን ከባድ ፈተና ላይ ቢጥል ለምን ይገርመናል?

 

 

6)   በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስና የእስልምና ሃይማኖቶች ከነችግራቸውም ቢሆን ለረጅም ዘመን ከመኖቸው ጋር ተያይዞ የጋራ የሆኑ ማህበራዊ፣ ትውፊታዊ፣ ባህላዊ፣ ሥነ ልቦናዊ፣ ሥነ ምግባራዊ ፣ ወዘተ እሴቶችን አጣምረው የያዙ ከመሆናቸው አንፃር የባለጌና ጫካኝ ገዥ ቡድኖች ርካሽ የፖለቲካ ጨዋታ ሰለባዎች ሲሆኑ ማየት ከምር የማያስበን ከሆነ ስለየትኛው ሃይማኖትና የሃይማኖት ነፃነት ነው የምናወራው?

 

7)    የትኛውም ሃይማኖት  ከማሰቢያ አእምሮና ከብቁ የማከናወኛ አካል ጋር በክርስቶስ አምሳል የተፈጠረው የሰው ልጅ  (የአገሬ ሰው) የገዛ ምድሩ በባለጌ፣ ሸፍጠኛ፣ ሴረኛና ጨካኝ የጎሳና የቋንቋ አጥንት ስሌት ፖለቲካ  ገዥ ቡድኖች ምድረ ሲኦል ስትሆንበት በጋራ ቆሞ ቢያንስ ነውር ነው ካላለና ካልገሰፀ ምን አይነትና እንዴት አይነት ሰብአዊ ሃይማኖት እንደሆነ ለመረዳት አያስቸግርም እንዴ?

 

8)    ሲኖዶስን እና መጅሊስን የባለጌና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ነጋዴዎች መፈንጫ ከማስደረግ የከፋ የሃይሃይማኖት መሪነት (አባትነት) ኪሳራ ይኖራል እንዴ?  ሃይማኖታዊ ሃላፊነትና ተልእኮ ባፍ ጢሙ ሲደፋ ማየትና መስማት  እውነተኛ ሃይማኖተኛ ነኝ ለሚል ወገን የሚያስከትለውን የህሊና ህመም የምንረዳው ስንቶቻችን ነን?

 

9)   የሃይማኖት “መሪዎችና  ሊቃውንት”  በየራሳቸው ጊዜና  ተጨባጭ ሁኔታ በታሪክ ሂደት ከተፈፀሙት ስህተቶች በአግባቡና ከምር ትምህርት በመውሰድ  የዛሬውንና የነገውን ትውልድ የሚጠቅሙ  ሥራዎችን ሠርቶ መገኘት ሲገባቸው  የክስተቶችን ትኩሳት እየተከተሉ  በግልብ ስሜት የመነዳት ሰለባዎች የመሆናቸው ግዙፍና መሪር እውነታ ህሊናውን የማይኮሰኩሰው እውነተኛ አማኝና አገር ወዳድ የሚል የአገሬ ሰው ይኖር ይሆን?  "ክርስቶስ ነን የሚሉ ሃሳዊያን ይነሳሉና ተጠንቀቁ ተብሏልና አስተውሉ" እያሉ ሲሰብኩን የኖሩ የሃይማኖት መሪዎች ውድቀት ግልፅ የሆነው ለአሽከርነት ክድርና ፍፁም በሚመቹ ብአዴን ተብየ የአገር ጉዶች ተባባሪነት የህወሃትን የበላይነት አስወግዶ  ቤተ መንግሥቱን የተረከበውንና የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሰብዕና ዝቅጠት የተጠናወተውን  አብይ አህመድን ለመገምገም የሚያስችል ጊዜና ትእግሥት ሳይወስዱ የኢትዮጵያ "ትንሳኤ ብርሃን" አድርገው የነገሩን  እለት አይደለም እንዴ?

 

10)        ምንም እንኳን ይህንን ስህተት ለመከላከል የሚያስችል አሳማኝ ምክንያት ባይኖርም ሊያጋጥም እንደሚችል ቆጥረን እንዳናልፈው የሥልጣነ መንበሩን አራጊነቱንና ፈጣሪነቱን (ጠርናፊነቱን) የጠቀለለው ተረኛ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቡድን (ኦህዴድ/ኦነግ/ብልፅግና) ይኸውና ለአምስት ዓመታት አገርን ምድረ ሲኦል እያደረገ ሲቀጥል እንኳንስ ስህተታቸውን አርመው ሃላፊነታቸውንና ተልእኳቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይባስ ብለው የሃይማኖት አሿሿሙንና የሥራ ቦታ አመዳደቡን “ጥንብ ነው” እያሉ የሚሰብኩን የጎሳና የዘር አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት አካል የማድረጋቸው መሪር እውነት ልቡን የማያደማው እውነተኛ አማኝ ይኖር ይሆን?

 

11)        እረኛው ነን የሚሉትን አማኝ ህዝብ ጉድፍ (ስህተት) የመረዳትና በንስሃ ለማንፃት  መንፈሳዊ ሥልጣንና አቅም እንዳላቸው የሚሰብኩን የሃይማኖት መሪዎችና ሰባኪዎች  ለአምስት ዓመታት              የመጡበትንና አሁንም እጅግ አስከፊና በሆነ ፈተና ውስጥ የምገኙበትን በተቃርኖ የተሞላ አስተሳሰባቸውንና አካሄዳቸውን ከተግባር ጋር በተዋሃደ  ፆምና ፀሎት ለማስተካከል ጥረት  ከማድረግ         ይልቅ ድርጊት አልባ ፀሎተ ምህላ አዋጅ በማወጅና ተሰብስቦ በእንባ የታጀበ እግዚኦታ በማስተጋባት ለምድሩም ሆነ ለሰማያዊው ህይወት የሚበጅ ለውጥን እውን ለማድረግ እንዴት እንደሚቻል         ለማመን አያስቸግርም እንዴ?

 

12)        ከዚህ የፀሎተ ምህላ አዋጅ ጋር ተያይዞ ፈፅሞ ለመግለፅ በሚያስቸግር ፖለቲካ ወለድ ወንጀል የበሰበሰውን (የከረፈውን) የፖለቲካ ሥርዓት በልፍስፍስ የአንተም ተው የአንተም ተው ሽምግልና ወደ         የእርቅና  የሰላም ጠረጴዛ ለማምጣት የሰላም ኮሜቲ ወይም ግብር ሃይል መሰል ቡድን የማቋቋም  አስፈላጊነት ዜናን ሰምተናል።

``

በምሥራችነት በተነገረን ዜና  እና ዜናውን የሚነግሩን የሃይማኖት መሪዎች    በመጡበትና በሚገኙበት እጅግ ደካማ አቋምና ቁመና  መካከል ያለውን  ርቀት በምን ይሉኛል ደካማ አቀራረብ ሳይሆን እውነተኛና ዘላቂ መፍትሄንና  አስተሳሰብን ግምት ውስጥ በሚያስገባ ሚዛናዊ  ህሊና  ለሚያስተውል  ሰው የሃይማኖታዊ እምነት ነፃነት  ከብልሹ ሥርዓት መወገድ ወይም አለመወገድ  ጋር በጥብቅ የተያያዘ መሆኑን ለመገንዘብ ይሳነው ይሆን ?

 

13)      ቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረትና ርብርብ የሚጠይቀውን የመከረኛ ወገን ህይወት ከመታደግ ይልቅ ባህርና ውቅያኖስ ማዶ ለሚሠራ ቤተክርስቲያንና ገዳም በብዙ ሚሊዮኖች የሚገመት ዶላር ብትሰጡ “ገነት ትገባላችሁ” በሚል  ዘመቻ ላይ መጠመድ እውን የእውነተኛ ሃይማኖታዊ ምንነታችንንና እንዴትነታችንን ይመጥናል እንዴ?  ለመሆኑ በየዋህነትም ሆነ በአንዳንድ የግልና የቡድን ጥቅም አሳዳጆች የሚካሄደውን ይህንን ዘመቻ “ልጆቻችንና ባልደረቦቻችን ሆይ፦ እስካሁን ከቆየንበት (ከኖርንበት) አይብስምና እባካችሁ መፅናኛ ላጣው ወገናችን የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተን እንረባረብ ፤ ሌላው ቀጥሎ ይደርሳል/ይሆናል ” የሚል የሃይማኖት መሪና ሊቀ ሊቃውንት እንዴት ይታጣል?

 

14)   አዎ! በእውነት ከተነጋገርን የክርስቶስ ማደሪያዎች ወይም ቤተ መቅደሶች የሆኑ በአያሌ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ንፁሃን ወገኖች ህይወት እየተደረመሰ (እየወደመ) ባለበት መሪር ሁኔታ ውስጥ የሚገነባው  ቤተ ክርስቲያን ወይም ገዳም ለየትኛው እግዚአብሔር ነው ማረፊያና ማደሪያ የሚሆነው? ፈጣሪን ጨምሮ ለመከረኛ ፍጡሮቹ ቅድሚያ ከመስጠት ይልቅ በየባህርና በየውቅያኖስ ማዶ ድንቅ ህንፃዎችን (ቤተ ክርስቲያናትንና ገዳማትን) በማሠራት የሚደሰት ጨካኝ ለምን እናስመስለዋለን?

ከችግራችን ዘመን ጠገብነትና ውስብስብነት የተነሳ ልቀጥል ብል ጥያቄን ጥያቄ እየወለደው እቸገራለሁና ለማሳያነት ይሆናሉ ያልኳቸውን ካነሳሁ ይበቃኛል።

አያሌ የዋህ አማኝ ወገኖች እና የህዝብ መከራና ሰቆቃ እንደሌለ በሚያስመሰል አኳኋን በባህርና በውቅያኖስ ማዶ የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት በሚል ዘመቻ የተጠመዱ ወገኖች ከላይ እንደ ዋነኛ ማሳያ ያነሰኋቸውን ግልፅና ቀጥተኛ ጥያቄዎች እንደ እግዚአብሔር አልባነት ወይም እንደ መርገምት  በመቁጠር የውግዘትና የእርግማን ናዳ ቢሰነዝሩ ያሳዝነኝ እንደሆን እንጅ ከቶ አይገርመኝም። ለምን ቢባል  ያፈጠጠውንና ያገጠጠውን የገዛ ራሳችንን የውድቀት አዙሪት በዓለማዊና በመንፈሳዊ የአርበኝነት አቋምና እና ቁመና  በመጋፈጥ ለምድራዊውም ሆነ ለሰማያዊው ህይወት የሚበጀንን ሥርዓተ ማህበረሰብ አምጠን ከመውለድ ይልቅ የጥንካሬና የስኬታማነት እሴቶችን አጣምሮ የያዘውን ሃይማኖታዊ እምነት የድክመቶቻችን መሸፈኛ (መሸሸጊያ) የማድረግን እጅግ አስቀያሚ  ድክመት  በፍፁምነት ማስወገድ ባንችልም ከቁጥጥራችን እየወጣ ተገዥው እንዳያደርገን ለማድረግ ገና ብዙ እንደሚቀረን እረዳለሁና ።

የሃይማኖታዊ እምነቶቻችን ምንነት፣ ለምንነትና ለማንነት ፣ እንዴትነት እና ወዴትነት ሊያሳስበን የሚገባውም ከዚሁ መሠረታዊ እሳቤ አንፃር ነው የሚል ፅዕኑ እምነት አለኝ።

ከፈጣሪ እገዛ ጋር ከዘመን ጠገቡና ከአስከፊው ውድቀታችን ተምረን ለሁላችንምና ለሁሉም አይነት ነፃነትና እኩልነት የምትመች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያንና አኩሪ የሆነ እኛነነትን እውን እንደምናደርግ እየተመኝሁ አበቃሁ!

 

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/187427
የሃይማኖት ጉዳይ ሊያስጨንቀን የሚገባው ለምድነው?
November 25, 2023

ጠገናው ጎሹ

ለዚህ አስተያየቴ ይህንን ርዕስ የመረጥኩት ስለ ሃይማኖት ምንነትና እንዴትነት ለማስተማር ወይም ለመስበክ አይደለም። ለማድረግ ብፈልግም ለዚህ የሚያበቃ እውቀቱና ችሎታውም ስለሌለኝ አላደርገውም።

ታዲያ ለምንድነው?  የሚል ጥያቄ ስለሚነሳና መነሳቱም ተገቢ ስለሆነ ይህንኑ ግልፅ ለማድረግ አስተያየቴን በጥያቄ መልክ በማቅረብ መልሱን ሃይማኖትን ጨምሮ መሠረታዊ ሰብአዊ መብት ፣ ነፃነት፣ ፍትህ (ዴሞክራሲ) ፣ ሰላም፣ ፍቅር ፣ የጋራ እድገት ፣ ወዘተ የሚረጋገጥበትና የሚከበርበት ሥርዓት እውን እንዲሆን ከምር ለሚሹ ወገኖች እተወዋለሁ።

ስለምንከተላቸው የሃይማኖት ተቋማት ነፃነትና ስኬታማነት ስንነጋገር ከምንኖርበት (ከምንገኝበት) የፖለቲካ ሥረዓት ለምንነት ፣ ለማንነት  ፣ እንዴትነት እና ከየት ወደ የትነት አንፃር መሆኑን መዘንጋት የለብንም።

 

እናም ልቀጥል፦

1)   ከማሰቢያ ረቂቅ አእምሮና ከማከናወኛ ብቁ አካል ጋር በክርስቶስ አምሳል የተፈጠረ ሰብአዊ ፍጡር ከፈጣሪው እርዳታ ጋር መሠረታዊ መብቱ ተጠብቆ፣ እርስ በርሱም ተከባብሮ፣ ተረደዳቶ ፣ ተፋቅሮ፣ ሰላምን ተንከባክቦ ፣ በጋራ በልፅጎ ፣ ወዘተ እንዲኖር እና እነዚሁ ወርቃማ እሴቶቹ ከሞት በኋላ ተስፋ ለሚያደርገው ህይወት ስንቅ እንዲሆኑት መርዳትና ማስቻል የሃይማኖት ዓላማና ግብ ካልሆነ ሌላ ምን?

 

2)   እነዚህን እጅግ መሠረታዊ እሴቶች ለምድራዊውና ተስፋ ለሚያደርገው የዚያኛው ዓለም ህይወት ስኬታማነት በአግባቡ ይጠቀምባቸው ዘንድ በነፃነት እና በራስ መተማመን አቋምና ቁመና እንዳይነቀሳቀስ (ጥረት እንዳያደርግ) የሚያሰናክሉ ወይም የሚከለክሉ እኩያን ገዥዎችና ግብረ በላዎቻቸው የሚፈፅሙትን እጅግ ክፉ ፖለቲካ ወለድ ወንጀል አቁመውና ንስሃ ገብተው የህዝብ መከራና ውርደት አብቅቶ ለሁሉም የሚበጅ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ይሆን ዘንድ ሚያደርገውን ተጋድሎ እንዲያግዙ ከምር የሚቆጣና የሚመክር እና አስፈላጊም ከሆነ አስፈላጊውን መስዋእትነት ለመቀበል ፈቃደኛና ዝግጁ የሆነ  አመራር የማፍራትና የማሠማራት ሃላፊነትን መወጣት የሃይማኖት ተቋማት መሠረታዊ ተልእኮ ካልሆነ ሌላ ለምንና ለማን ?  

 

3)   እርግጥ ነው ይህንን እውን ለማድረግ መንገዱ አልጋ ባልጋ አይሆንም። ሃይማኖትን ጨምሮ መሠረታዊ መብቶች በተጠየቁ ቁጥር ሥልጣነ መንበራቸው ሥጋት ላይ የወደቀ እየመሰላቸው ነፃነትና ፍትህ በሚጠይቀው መከረኛ ህዝብ ላይ የጭካኔ ሰይፋቸውን የሚመዙ እኩያን ገዥዎችን አግባብነት ባለውና በማይታጠፍ መንፈሳዊ መሪነት መጋፈጥ የግድ መሆኑን ተረድቶና ተቀብሎ የእረኝነት ሃላፊነትንና ተልእኮን የመወጣት ጉዳይ የሃየማኖት መሪዎች ካልሆነ ሌላ የምንና የማን?

 

4)   በእኩያን ገዥዎች ፖለቲካ ወለድ ወንጀል ምክንያት በግፍ ግድያ፣ ከገዛ አገር በመፈናቀል ፣ በጅምላ ግዞትና እስር ፣ በርሃብ ቸነፈር ፣ በእርዛት አለንጋ ፣ የወላድ መካን በመሆን ሁለንተናዊ ስቃይ ፣በወላጅ አልባነት መሪር ሰቆቃ ፣ እና በአጠቃላይ ለመግለፅ በሚያስቸግር የውድቀት አዙሪት  ውስጥ በመጓጎጥ ላይ ለሚገኝን መከረኛ ህዝብ ቀድሞ የመድረስ ሃላፊነት ካለባቸው ወገኖች መካከል የሃይማኖት መሪዎችና ሊቃውንት ዋነኞቹ  ካልሆኑ ሃይማኖት ለምንና ለነማን?

 

5)   በዚህ ረገድ ከዘመን ዘመን ከመሻሻል ይልቅ በእጅጉ እየባሰበት የመጣው ውድቀታችን አይደለም ወይ ሃይማኖቶቻችን ከፍተኛ ፈተና ላይ እየጣላቸው የሚገኘው? ይህንን እጅግ አሳሳቢና አስፈሪ ሁኔታ በጥሞና እና አርአያነትን በተላበሰ የሃይማኖት አርበኝነት ማስተካከል የሚገባቸው የሃይማኖት መሪዎችና ሊቃውንት ራሳቸው ሆነው ሳለ በሥልጣነ መንበር ላይ እየተፈራረቁ  የመከራውንና የውርደቱን ዘመን በአስከፊ ሁኔታ እያራዘሙ ካሉት ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች ጋር  እየተሻሹ ዘመን ጠገብ የሆነውንና የማይደፈረውን ሃይማኖታዊ  ዶግማና ቀኖና በአፍ ጢሙ ሲደፉትና ሲያስደፉት ማየትና መስማት የሃይማኖት ምንነትንና እንዴትነትን ከባድ ፈተና ላይ ቢጥል ለምን ይገርመናል?

 

 

6)   በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስና የእስልምና ሃይማኖቶች ከነችግራቸውም ቢሆን ለረጅም ዘመን ከመኖቸው ጋር ተያይዞ የጋራ የሆኑ ማህበራዊ፣ ትውፊታዊ፣ ባህላዊ፣ ሥነ ልቦናዊ፣ ሥነ ምግባራዊ ፣ ወዘተ እሴቶችን አጣምረው የያዙ ከመሆናቸው አንፃር የባለጌና ጫካኝ ገዥ ቡድኖች ርካሽ የፖለቲካ ጨዋታ ሰለባዎች ሲሆኑ ማየት ከምር የማያስበን ከሆነ ስለየትኛው ሃይማኖትና የሃይማኖት ነፃነት ነው የምናወራው?

 

7)    የትኛውም ሃይማኖት  ከማሰቢያ አእምሮና ከብቁ የማከናወኛ አካል ጋር በክርስቶስ አምሳል የተፈጠረው የሰው ልጅ  (የአገሬ ሰው) የገዛ ምድሩ በባለጌ፣ ሸፍጠኛ፣ ሴረኛና ጨካኝ የጎሳና የቋንቋ አጥንት ስሌት ፖለቲካ  ገዥ ቡድኖች ምድረ ሲኦል ስትሆንበት በጋራ ቆሞ ቢያንስ ነውር ነው ካላለና ካልገሰፀ ምን አይነትና እንዴት አይነት ሰብአዊ ሃይማኖት እንደሆነ ለመረዳት አያስቸግርም እንዴ?

 

8)    ሲኖዶስን እና መጅሊስን የባለጌና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ነጋዴዎች መፈንጫ ከማስደረግ የከፋ የሃይሃይማኖት መሪነት (አባትነት) ኪሳራ ይኖራል እንዴ?  ሃይማኖታዊ ሃላፊነትና ተልእኮ ባፍ ጢሙ ሲደፋ ማየትና መስማት  እውነተኛ ሃይማኖተኛ ነኝ ለሚል ወገን የሚያስከትለውን የህሊና ህመም የምንረዳው ስንቶቻችን ነን?

 

9)   የሃይማኖት “መሪዎችና  ሊቃውንት”  በየራሳቸው ጊዜና  ተጨባጭ ሁኔታ በታሪክ ሂደት ከተፈፀሙት ስህተቶች በአግባቡና ከምር ትምህርት በመውሰድ  የዛሬውንና የነገውን ትውልድ የሚጠቅሙ  ሥራዎችን ሠርቶ መገኘት ሲገባቸው  የክስተቶችን ትኩሳት እየተከተሉ  በግልብ ስሜት የመነዳት ሰለባዎች የመሆናቸው ግዙፍና መሪር እውነታ ህሊናውን የማይኮሰኩሰው እውነተኛ አማኝና አገር ወዳድ የሚል የአገሬ ሰው ይኖር ይሆን?  "ክርስቶስ ነን የሚሉ ሃሳዊያን ይነሳሉና ተጠንቀቁ ተብሏልና አስተውሉ" እያሉ ሲሰብኩን የኖሩ የሃይማኖት መሪዎች ውድቀት ግልፅ የሆነው ለአሽከርነት ክድርና ፍፁም በሚመቹ ብአዴን ተብየ የአገር ጉዶች ተባባሪነት የህወሃትን የበላይነት አስወግዶ  ቤተ መንግሥቱን የተረከበውንና የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሰብዕና ዝቅጠት የተጠናወተውን  አብይ አህመድን ለመገምገም የሚያስችል ጊዜና ትእግሥት ሳይወስዱ የኢትዮጵያ "ትንሳኤ ብርሃን" አድርገው የነገሩን  እለት አይደለም እንዴ?

 

10)        ምንም እንኳን ይህንን ስህተት ለመከላከል የሚያስችል አሳማኝ ምክንያት ባይኖርም ሊያጋጥም እንደሚችል ቆጥረን እንዳናልፈው የሥልጣነ መንበሩን አራጊነቱንና ፈጣሪነቱን (ጠርናፊነቱን) የጠቀለለው ተረኛ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቡድን (ኦህዴድ/ኦነግ/ብልፅግና) ይኸውና ለአምስት ዓመታት አገርን ምድረ ሲኦል እያደረገ ሲቀጥል እንኳንስ ስህተታቸውን አርመው ሃላፊነታቸውንና ተልእኳቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይባስ ብለው የሃይማኖት አሿሿሙንና የሥራ ቦታ አመዳደቡን “ጥንብ ነው” እያሉ የሚሰብኩን የጎሳና የዘር አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት አካል የማድረጋቸው መሪር እውነት ልቡን የማያደማው እውነተኛ አማኝ ይኖር ይሆን?

 

11)        እረኛው ነን የሚሉትን አማኝ ህዝብ ጉድፍ (ስህተት) የመረዳትና በንስሃ ለማንፃት  መንፈሳዊ ሥልጣንና አቅም እንዳላቸው የሚሰብኩን የሃይማኖት መሪዎችና ሰባኪዎች  ለአምስት ዓመታት              የመጡበትንና አሁንም እጅግ አስከፊና በሆነ ፈተና ውስጥ የምገኙበትን በተቃርኖ የተሞላ አስተሳሰባቸውንና አካሄዳቸውን ከተግባር ጋር በተዋሃደ  ፆምና ፀሎት ለማስተካከል ጥረት  ከማድረግ         ይልቅ ድርጊት አልባ ፀሎተ ምህላ አዋጅ በማወጅና ተሰብስቦ በእንባ የታጀበ እግዚኦታ በማስተጋባት ለምድሩም ሆነ ለሰማያዊው ህይወት የሚበጅ ለውጥን እውን ለማድረግ እንዴት እንደሚቻል         ለማመን አያስቸግርም እንዴ?

 

12)        ከዚህ የፀሎተ ምህላ አዋጅ ጋር ተያይዞ ፈፅሞ ለመግለፅ በሚያስቸግር ፖለቲካ ወለድ ወንጀል የበሰበሰውን (የከረፈውን) የፖለቲካ ሥርዓት በልፍስፍስ የአንተም ተው የአንተም ተው ሽምግልና ወደ         የእርቅና  የሰላም ጠረጴዛ ለማምጣት የሰላም ኮሜቲ ወይም ግብር ሃይል መሰል ቡድን የማቋቋም  አስፈላጊነት ዜናን ሰምተናል።

``

በምሥራችነት በተነገረን ዜና  እና ዜናውን የሚነግሩን የሃይማኖት መሪዎች    በመጡበትና በሚገኙበት እጅግ ደካማ አቋምና ቁመና  መካከል ያለውን  ርቀት በምን ይሉኛል ደካማ አቀራረብ ሳይሆን እውነተኛና ዘላቂ መፍትሄንና  አስተሳሰብን ግምት ውስጥ በሚያስገባ ሚዛናዊ  ህሊና  ለሚያስተውል  ሰው የሃይማኖታዊ እምነት ነፃነት  ከብልሹ ሥርዓት መወገድ ወይም አለመወገድ  ጋር በጥብቅ የተያያዘ መሆኑን ለመገንዘብ ይሳነው ይሆን ?

 

13)      ቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረትና ርብርብ የሚጠይቀውን የመከረኛ ወገን ህይወት ከመታደግ ይልቅ ባህርና ውቅያኖስ ማዶ ለሚሠራ ቤተክርስቲያንና ገዳም በብዙ ሚሊዮኖች የሚገመት ዶላር ብትሰጡ “ገነት ትገባላችሁ” በሚል  ዘመቻ ላይ መጠመድ እውን የእውነተኛ ሃይማኖታዊ ምንነታችንንና እንዴትነታችንን ይመጥናል እንዴ?  ለመሆኑ በየዋህነትም ሆነ በአንዳንድ የግልና የቡድን ጥቅም አሳዳጆች የሚካሄደውን ይህንን ዘመቻ “ልጆቻችንና ባልደረቦቻችን ሆይ፦ እስካሁን ከቆየንበት (ከኖርንበት) አይብስምና እባካችሁ መፅናኛ ላጣው ወገናችን የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተን እንረባረብ ፤ ሌላው ቀጥሎ ይደርሳል/ይሆናል ” የሚል የሃይማኖት መሪና ሊቀ ሊቃውንት እንዴት ይታጣል?

 

14)   አዎ! በእውነት ከተነጋገርን የክርስቶስ ማደሪያዎች ወይም ቤተ መቅደሶች የሆኑ በአያሌ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ንፁሃን ወገኖች ህይወት እየተደረመሰ (እየወደመ) ባለበት መሪር ሁኔታ ውስጥ የሚገነባው  ቤተ ክርስቲያን ወይም ገዳም ለየትኛው እግዚአብሔር ነው ማረፊያና ማደሪያ የሚሆነው? ፈጣሪን ጨምሮ ለመከረኛ ፍጡሮቹ ቅድሚያ ከመስጠት ይልቅ በየባህርና በየውቅያኖስ ማዶ ድንቅ ህንፃዎችን (ቤተ ክርስቲያናትንና ገዳማትን) በማሠራት የሚደሰት ጨካኝ ለምን እናስመስለዋለን?

ከችግራችን ዘመን ጠገብነትና ውስብስብነት የተነሳ ልቀጥል ብል ጥያቄን ጥያቄ እየወለደው እቸገራለሁና ለማሳያነት ይሆናሉ ያልኳቸውን ካነሳሁ ይበቃኛል።

አያሌ የዋህ አማኝ ወገኖች እና የህዝብ መከራና ሰቆቃ እንደሌለ በሚያስመሰል አኳኋን በባህርና በውቅያኖስ ማዶ የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት በሚል ዘመቻ የተጠመዱ ወገኖች ከላይ እንደ ዋነኛ ማሳያ ያነሰኋቸውን ግልፅና ቀጥተኛ ጥያቄዎች እንደ እግዚአብሔር አልባነት ወይም እንደ መርገምት  በመቁጠር የውግዘትና የእርግማን ናዳ ቢሰነዝሩ ያሳዝነኝ እንደሆን እንጅ ከቶ አይገርመኝም። ለምን ቢባል  ያፈጠጠውንና ያገጠጠውን የገዛ ራሳችንን የውድቀት አዙሪት በዓለማዊና በመንፈሳዊ የአርበኝነት አቋምና እና ቁመና  በመጋፈጥ ለምድራዊውም ሆነ ለሰማያዊው ህይወት የሚበጀንን ሥርዓተ ማህበረሰብ አምጠን ከመውለድ ይልቅ የጥንካሬና የስኬታማነት እሴቶችን አጣምሮ የያዘውን ሃይማኖታዊ እምነት የድክመቶቻችን መሸፈኛ (መሸሸጊያ) የማድረግን እጅግ አስቀያሚ  ድክመት  በፍፁምነት ማስወገድ ባንችልም ከቁጥጥራችን እየወጣ ተገዥው እንዳያደርገን ለማድረግ ገና ብዙ እንደሚቀረን እረዳለሁና ።

የሃይማኖታዊ እምነቶቻችን ምንነት፣ ለምንነትና ለማንነት ፣ እንዴትነት እና ወዴትነት ሊያሳስበን የሚገባውም ከዚሁ መሠረታዊ እሳቤ አንፃር ነው የሚል ፅዕኑ እምነት አለኝ።

ከፈጣሪ እገዛ ጋር ከዘመን ጠገቡና ከአስከፊው ውድቀታችን ተምረን ለሁላችንምና ለሁሉም አይነት ነፃነትና እኩልነት የምትመች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያንና አኩሪ የሆነ እኛነነትን እውን እንደምናደርግ እየተመኝሁ አበቃሁ!

 

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/187427

Sunday, November 26, 2023

አዲስ አበቤ ተናሳ! ትግላችን ከመሰልቀጥ ለመዳን ነው! ‘’አዲስ አበባን ራስ ገዝ እናደርጋታለን!
https://youtu.be/tG2h0dUK3sc?si=ZlAXl-Lq8XKjyin_

አዲስ አበቤ ተናሳ! ትግላችን ከመሰልቀጥ ለመዳን ነው! ‘’አዲስ አበባን ራስ ገዝ እናደርጋታለን

 

https://youtu.be/rbwpo9UkBkU?si=PhOPbHjMw95kwAkV
https://amharic-zehabesha.com/archives/187418
      በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ሁለ-ገብ የኢኮኖሚ ዕድገት ለብሄራዊ ነፃነት መከበርና ለተሟላ ሰላም መስፈን ወሳኝ ነው!
ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)

ህዳር 26፣ 2023

 

በአገራችንም ሆነ በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ያለው ትልቁ ችግር ወደ ውስጥ ያተኮረ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ሰፋ ያለ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ እንዲሁም የሚያማምሩ ከተማዎችና መንደሮች መገንባትና፣ እነዚህም በተለያዩ የመመላለሻ ዘዴዎች መያያዝ እንዳለባቸው ያለመረዳት ነው። አንድ ህዝብ በአስተማማኝ የኑሮ ሁኔታ ሲኖርና፣ የሰለጠነና በሁሉም አቅጣጫ በምሁራዊ ዕውቀት መንፈሱ የዳበረ ሰፋ ያለ የህብረተሰብ ክፍል ካለ አንድ አገርና ህዝብ በቀላሉ በውጭ ኃይሎች ሊታለሉና ህዝቦቻቸውም ከውጭ በሚመጣ የተበላሸ ባህል ሰለባ በመሆንና በገንዘብ በመታለል የአገራቸውን ህልውና በፍጹም አይሸጡም።  እንደሚታወቀው አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች በባሪያ ንግድ የተነሳና፣ በኋላ ላይም በቅኝ-ግዛት አስተዳደር ውስጥ በመውደቃቸው ወደ ውስጥ ያተኮረ በስራ-ክፍፍል ላይ የተመሰረተ ማህበረሰብ እንዳይመሰርቱ ተደርገዋል። የቅኝ ግዛት አስተዳዳሪዎች አፍሪካን እናሰለጥናለን ብለው ቢሄዱም ያደረጉት ነገር እስከዚያ ጊዜ ድረሰ የነበሩትን ዕድገቶችና የታሪክ ቅርሶች እንዳሉ ነው ያወደሙባቸው። አንዳንድ በማደግ ላይ የነበሩ ከተማዎችንና ቤተመንግስቶችን እንዳለ ነው ያፈራረሱባቸው። በተጨማሪም በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ የዕድገትና የስልጣኔ ምልክቶች የነበሩ የታሪክ ቅርፆችን እየነቃቀሉ ነው ወደ አዎሮፓ ዋና ዋና ከተማዎች ማጋዝ የጀመሩት። እነዚህ  ከብረታ-ብረት፣ ከዕብነ-በረድ፣ ከተለያዩ የዲንጋይ ዐይነቶችና ከእንጨት የተሰሩ የሚያማምሩ ቅርፃ ቅርፆች በአሁኑ ወቅት በየሙዚዬሞች ውስጥ በመቀመጥ በህዝብ የሚጎበኙ ናቸው። በዚህ የተነሳና የኋላ-ኋላም ከቅኝ-ግዛት ከተላቀቁና ነፃነታቸውን ተቀዳጁ ከተባሉ በኋላ በተዘዋዋሪ የቅኝ-ግዛት እንዲሆኑ ነው የተደረገው። የተለያዩ በነፃ ገበያ ስም ሳይንሳዊ ያልሆኑና ወደ ውስጥ ህዝባዊ ሀብት ሊፈጥሩ የማይችሉ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ብለው የሚጠሯቸውን ራሳቸው ባቋቋሟቸው የዓለም አቀፍ ተቋማት ብለው በሚጠሯቸው እያስገደዱ ነው ወደ ተግባርነት እንዲመነዘሩ ለማድረግ የበቁት። የነጩ የኢሊጋርኪ መደብ በማንአለኝበት መንፈስ በመወጠር አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች  በራሳቸው ጥረትና በምሁሮቻቸው ጥናትና ክርክር ጠንካራ ኢኮኖሚና ማህበረሰብ እንዳይገነቡ  የዕድገቱን መንገድ ለመዝጋት በቅቷል። አንዳንዶች ከዚህ ዐይነቱ የስውር ቅኝ አገዛዝ ለመላቀቅ ጥረት ሲያደርጉና አንዳንድ ዕርምጃዎች ሲወስዱ የመንግስት ግልበጣ ሊደረግባቸው ችሏል። አንዳንዶች በራሳቸው ጓዶች እንዲገደሉ ለመደረግ በቅተዋል። ይህም የሚያመለክተው በምንም ዐይነት የነጩ ኦሊጋርኪ መደብ ጥቁር አፍሪካውያን ጠንካራና የበለፀገ ማህበረሰብ እንዳይገነቡ ቀን ከሌት እንደሚሰራና፣ ካስፈለገም በተዘዋዋሪ የርስ በርስ ጦርነት በማስነሳት የኋላ-ቀርነት ዘመኑ እንዲራዘም እንደሚያደርግ ነው። ዛሬ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች የሚካሄዱት የርስ በስር ጦርነቶች በመሰረቱ የውክልና ጦርነቶች ሲሆኑ፣ የሚካሄዱትም የእስላም አክራሪን ኃይል ለመዋጋትና የራስን የጂኦ ፖለቲካ ጥቅም ለማስጠበቅ በሚል ስም ነው።

 

ወደ አገራችን ስንመጣ ግን አገራችን ለጥቂት ጊዜያት ካልሆነ በስተቀር የቅኝ ግዛት ሰለባ ባትሆንም ህዝባችን ብሄራዊ ነፃነቱን ለማስከበር የሚያስችለው በሳይንስና በቴክሎጂ ላይ የተመሰረተ፣ የሚያማሩ ከተማዎችና መንደሮች፣ እንዲሁም እነዚህን የሚያያዙ ልዩ ልዩ የመገናኛ ዘዴዎች ባለመዘርጋታቸው ህዝባችንና አገራችን የመከበር ዕድል በፍጹም አላገጠማቸውም። ይህንን ዐይነቱን ጉድለት የተረዳ የተገለጸለት ምሁራዊ ኃይል ብቅ ማለት ባለመቻሉና፣ ጥቂት ተማርኩ ነኝ የሚለው የአሜሪካ ርዕዮተ-ዓለም ሰለባ በመሆንና የእሱም የጥፋት ድርጊት ተላላኪ በመሆን የአገራችን ብሄራዊ ነፃነት እንዳይከበርና፣ አልፎም በመሄድ አገራችን እንድትፈራርስ የማይሰራው ሴራ የለም። ይህ ዐይነቱ የመንፈስ ድክመትና ለውጭ ኃይል መገዛትና ብሄራዊ ነፃነትን በመሸጥ አገራችን በጠንካራ መሰረት ላይ እንዳትገነባ ማድረግ ከሁሉም ብሄረሰብ በተውጣጡ ኤሊቶች የሚሳበብ ሳይሆን ከተወሰኑ ብሄረሰቦች የተውጣጡ ኤሊቶች ዋና ተግባር ሊሆን በቅቷል። በተለይም ከአደሬ ብሄረሰብ፣ ከአማራው፣ ከትግሬና ከኦሮሞ ብሄረሰብ የተውጣጡና የመማር ዕድል ያገጠማቸው ኢሊት ነን ባዮች ንቃተ-ህሊናቸው በጣም ዝቅተኛ ስለሆነ ባለፉት አርባና ሃምሳ ዓመታት በአሜሪካን የስለላ መረብ ውስጥ በመካተት የዕድገትና የብሄራዊ ነፃነት ጠንቅ በመሆን ህዝባችንና አገራችን ፍዳቸውን እያዩ እንዲኖሩና እንዲዋረዱም ለማድረግ በቅተዋል።  ያም ሆነ ይህ ይህንን ጉዳይ ዘርዘር በማድረግና በማነፃፀር  ከህብረ-ብሄር ምስረታ አኳያ የብሄራዊ ነፃነትንና  የየዜጎችን መብት መከበር ጉዳይ ጠጋ ብለን እንመልከተው።

 

እንደሚታወቀው በ18ኛውና በ19ኛው ክፍለ-ዘመንም ሆነ ከዚያ ቀደም ብሎ ህብረ-ብሄሮች እንደዛሬው ዘመን በአንድ ግዛት ውስጥ ተጠቃለውና መለያ የሚሆናቸው የየራሳቸው ባንዲራ ሳይኖራቸው በነበረበት ዘመን ኃያል ነን የሚሉ መንግስታት ደካማ አገሮችን ጦራቸውን በማዝመት ነው በቀጥታ የሚወሯቸው የነበረው። በቀድሞው ዘመን አንዳንድ አገዛዞች በውጭ ኃይሎች ግዛቴ ተደፈረ፣ ተወረርኩም በማለት ህዝባቸውን በማስተባበር የወረራቸውን ኃይል መክተው ለመመለስ የሚጠቀሙበት ዘዴ በቀጥታ ከወረራቸው ኃይል ጋር በመፋለም ነው ብሄራዊ ነፃነታቸውን የሚያስከብሩት። በዚህ መልክ በቀጥታ የተወረሩ አገሮች አገዛዞች የተገለፀላቸው ከሆነ እንደገና ላለመወረር ሲሉ ቶሎ ብለው የሚወስዱት እርምጃ የተበታተነውን ህዝብና  በአንድ ማዕከላዊ አገዛዝ አልገዛም በማለት የሚያስቸግረውን የክልል አገዛዝ በመሰብሰብና በማታለል፤ እንዲያም ሲል በማሸነፍ ወደ ውስጥ ያተኮረ ሁለ-ገብ የሆነ የአገር ግንባታና ለሰፊው ህዝብ የስራ መስክ የሚከፍት ትናንሽና የማዕከለኛ ኢንዱስትሪዎችን በማቋቋም ነው አገራቸውን ዘመናዊ ለማድረግ የበቁት። ከዚህም አልፈው በመሄድ ህዝባቸውና ቀስ በቀስ እያደገ የሚመጣው የንዑስ ከበርቴው የህብረተሰብ ክፍል ብሄራዊ ስሜት እንዲያድርባቸውና አገራቸውንም በጋራ እንዲጠብቁ የሚወስዱት እርምጃ መንፈስን የሚሰበስቡና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚያስተናግዱ ከተማዎችንና መንደሮችን መገንባት ነው።  ከዚያም አልፈው በመሄድ ከተማዎችንና መንደሮችን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በማስተሳሰር የንግድ ልውውጥና እንቅስቃሴ እንዲዳብር ማድረግ ነው። በተጨማሪም እዚህና እዚያ ለመኖሪያ የሚሆኑ ቤቶችን መገንባት፣ የተለያዩ የትምህርት ዘርፎችንና የሙያ ማስልጠኛ ማዕከሎችን በማስፋፋትና፣  ክሊኒኮችንና የገበያ አዳራሾችን፣ እንዲሁም  ለሰፊው ህዝብ የመዝናኛ ማዕከሎችን በመገንባት አንድ ህዝብና ተከታታዩ ትውልድ ተከብረው የሚኖሩበት አገር ጥለው ያልፋሉ። ለሰፊው ህዝብ የሚጠቅሙና ግልጋሎትም የሚሰጡ የሰለጠኑ ተቋማት በመገንባት ማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ ለህዝባቸው አለኝታ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ። ተከታታይ አገዛዞችም በዚህ ዐይነቱ አገርን መገንባትና የህዝብ አገልጋይ መሆን መንፈስ ተኮትኩተው ስለሚያድጉ እነሱም በበኩላቸው አገራቸውን በተሻለ መልክ በመገንባት ለተከታታዩ አገዛዝ የሚሆን በቀላሉ ሊደፈርና በተለያዩ የውስጥ ኃይሎች በቀላሉ ሊረበሽ ወይም ሊናጋ የማይችል አገርና ማህበረሰብ ጥለው ያልፋሉ።

 

በዚህ መልክ በ19ኛው ክፍለ-ዘመን በቀጥታ በውጭ ኃይሎች ይደፈሩ የነበሩ እንደጀርመን፣ ጃፓን፣ የኋላ ኋላ ደግሞ ደቡብ ኮርያና፣ ከ1949 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ቻይና  እንደገና በውጭ ኃይሎች ላለመወረር ሲሉ እንደምንም ብለው በድል አድራጊነት ከወጡ በኋላ ተግባራዊ ማድረግ የጀመሩት በሁለ-ገብ የአገር ግንባታ ላይ በመሰመራት ነው አገሮቻቸውን በጠንካራ መሰረት´ ላይ ለመግንባት የቻሉት። ለዚህ ነው ጀርመን እስከ 1871 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ የውጭ ኃይሎች በመወረሯና ወደ ውስጥ ያተኮረ የአገር ግንባታ ማካሄድ ባለመቻሏ ይህንን  ድክመት የተረዱት የፕረሽያ ሞናርኪዎችና ሁለ-ገብ ዕውቀት ያላቸው ምሁራን ዋናውን ምክንያት በመፈለግና የሚያስቸግሯቸውን ኃይሎች ድል በማድረግና ሌሎችንም በማታለል በፈረንሳይ ላይ ድልን ከተቀዳጁ በኋላ በሙሉ ኃይል ወደ ውስጥ ያተኮረ ሁለ-ገብ የአገር ግንባታ ማካሄድ የጀመሩት። በተለይም ለዕውቀት ማዕከላዊ ቦታ በመስጠትና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚጠቅም ሁለ-ገብ የሆነ የትምህርት የጥገና ለውጥ በማካሄድና፣ በተለይም በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ትምህርት በማስፋፋት፣ ከዚህም በላይ ለኢንጂነሪንግና ለዕደ-ጥበብ ሙያዎች ከፍተኛ አትኩሮ በመስጠት ነው ጀርመን በአንድ ትውልድ ጊዜ ውስጥ እንግሊዝንና ፈረንሳይን ቀድማ ለመሄድ የቻለችው። ተግባራዊም በሆነው ሰፋና ጠለቅ ያለ የትምህርት የጥገና ለውጥ አማካይነት ነው ጀርመን በ20ኛው ክፍለ-ዘመን ሁለት-ሶስተኛውን የሚሆን የኖቭል ዋጋ ተሸላሚ ሳይንቲስቶችን ማፍራት የቻለችው።

 

ወደ አገራችን ስንመጣ ጣሊያን ሁለት ጊዜ ከመውረሩ በፊት ኢትዮጵያችን በተለያዩ የጎረቤት አገሮች ትደፈር ነበር። በጊዜው ህዝቡን የሚያስተባብር ማዕከላዊ ግዛት ባለመኖሩና በየክልሉም ፊዩዳላዊ አገዛዝች በመኖራቸው ይህ ዐይነቱ የውስጥ ሽኩቻ ለውጭ ኃይሎች ወረራ አመቺ ነበር። ይህንን ድክመት የተረዱት አፄ ቴዎድሮስ አሻፈረኝ የሚለውን ኃይል በሙሉ በማሸነፍ ነበር የድርጅትን አስፈላጊነት በመረዳት አገራቸውን የኢንዱስትሪ አብዮት ባለቤት ለማድረግ ከእንግሊዙ ሞናርኪ ጋር ይጻጻፉ የነበረው። በአንድ በኩል የጥገና ለውጥን አሻፈረኝ የሚለው ፊዩዳላዊ ኃይልና ሌሎች፣ በሌላው ወገን ደግሞ በእንግሊዝ መንግስት ተንኮለኛነት የተነሳ አፄ ቴዎድሮስ የተመኙትን አገርን በአስተማማኝ መሰረት የመግንባት ዕድል አላገጠማቸውም። በጊዜው አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዙ ንግስት ከነበሩት ከንግስት ቪክቶሪያ ጋር ይጻጻፉ የነበረው ኢንጂነሮችን፣  የዕደ-ጥበብ ሙያተኞችን፣ የከተማ ግንባታ አዋቂዎችንና ሌሎችንም ለአገር ግንባታ ይጠቅማሉ የሚሏቸውን ሙያተኞችን እንዲልኩላቸው ነበር። ንግስት ቪክቶሪያና አገዛዛቸውም አፄ ቴዎድሮስ የጠየቁትን ሙያተኞች ከመላክ ይልቅ ሃይማኖትን የሚያስፋፉና የሚሰብኩ ቄሶችን  ነበር። በዚህ ድርጊት የተናደዱት አፄ ቴዎድሮስ የተላኩትን ቄሶችንና ሌሎችን ቀሳውስቶች በማሰር ነው ብረታ-ብረት እንዲቀጥቅጡና ልዩ ልዩ መሳሪያዎችንም እንዲሰሩ ያስገድዷቸው የነበረው።  በአፄ ቴዎድሮስ ድርጊት የተናደደችው እንግሊዝ ጦሯን በመላክ ነው አፄ ቴዎድሮስ በሰው ልጅ ከምገድል ይልቅ በማለት ራሳቸውን የገደሉት። አፄ ቴዎድሮስ ራሳቸውን ካጠፉ በኋላ አገርን በጠንካራ መሰረት ላይ መገንባቱ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ  የኋላ ኋላ በአፄ ምኒልክ ትከሻ ላይ ነው ሊወድቅ የቻለው።

 

አፄ ምኒልክ እ.አ. አ በ1896 በአደዋ  በጣሊያን ላይ ድልን ከተቀዳጁ በኋላ ተግባራዊ ማድረግ የጀመሩት እርምጃ ቢያንስ ህዝባቸውን የሚያስተሳስርላቸውንና ብሄራዊ ስሜቱ እንዲያድር የሚያደረገውን አገርን የመገንባት የመጀመሪያውን እርምጃ ነው መውሰድ የጀመሩት። ትምህርት ቤቶችን መክፈት፣ ድልድዮችን ማሰራት፣ የብሄራዊ ባንክ መክፈትና ለመገበያያ የሚሆን በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው ገንዘብ አትሞ ማሰራጨት፣ የባቡር ሃዲድ ማሰራትና የፖስታ ቤት መክፈት ለህብረ-ብሄር ምስረታ የሚያመቹb  የመጀመሪያዎች  እርምጃዎች ነበሩ። ህብረ-ብሄር ለመመስረት የሚያስችሉ በየቦታው የተሰሩና የተገነቡ ከተማዎች ስላልነበሩና፣ በተለይም ወደ ደቡቡ የኢትዮጵያ ግዛት አብዛዎችም መሬቶች ጠፍ ስለነበሩና፣ በየቦታውም የተገለጸለት ወይም የተማረ ኃይል ባለመኖሩ አፄ ምኒልክም  ሀ ብለው መጀመር ነበረባቸው። ወደ ማዕከላዊ መንግስት አካባቢም ስንመጣ በሁለ-ገብ ዕውቀት የሰለጠነ ምሁራዊ ኃይል ባለመኖሩ የአፄ ምኒልክን ፍላጎትና ምኞት በመረዳት የማህበራዊ መሰረት በመሆን ምኞታቸውን ዕውን የሚያደርግ ኃይል ሊኖር ባለመቻሉ ኢትዮጵያን ዘመናዊ የማድረጉ ጉዳይ ሙሉ በሙሉ ሊሳካ አልቻለም።  ከተማዎችንና መንደሮችን በአስተማማኝ መሰረት  ላይ መገንባት አልተቻለም። የተዘረጋው የባቡር ሃዲድ ለውጭ ገበያ እንዲያመች በመሆኑ ለውስጥ ገበያ ዕድገት የሚያመቹ ልዩ ልዩ የመገናኛ ዘዴዎች ለመገንባት ባለመቻላቸውና፣ ይህንንም ተግባራዊ የሚያደርግ በኢንጂነሪንግ ሙያ የሰለጠነ የህብረተሰብ ኃይል ባለመኖሩ ለአንድ አገር ብሄራዊ ነፃነት መከበር አስፈላጊ የሆነው የአገር ውስጥ ገበያ ዕድገት አስፈላጊው አትኩሮ ሊሰጠው በፍጹም አልተቻለም። ከዚህም ጋር ተያይዞ ለብሄራዊ ገበያና ለብሄራዊ ሀብት መፈጠር በጣም አስፈላጊ የሆነው የማሺን ኢንዱስትሪ ስለማይታወቅና በዚህም የተነሳ ተግባራዊ ለመሆን ባለመቻሉ የአገራችን ህዝብ ከእጅ ወደ አፍ አልፎ ሊሄድ በማይችል የግብርናና የዕደ-ጥበብ ሙያ ነው ይተዳደር የነበረው። ይሁንና አፄ ምኒልክ ጥለው የሄዱት መሰረት ህዝባችን ብሄራዊና አገራዊ ስሜት እንዲያድርበት ለማድረግ  በቅቷል ማለት ይቻላል።

 

አፄ ምኒልክ ከሞቱ በኋላ አገርን በፀና መሰረት ላይ ለመገንባት የጃፓናዊ ዐይነት እንቅስቃሴ ቢኖርምና ቀስ በቀስም ምሁራዊ ኃይሎች ብቅ ቢሉም በሁለተኛው የጣሊያን ወረራ ምክንያት የተነሳ በ1920ዎች የነበረው የዘመናዊነት እንቅስቃሴ ሊዳፈን ቻለ። በጊዜው የነበረው ትንሽ ምሁራዊ ኃይል በጣሊያኑ ወራሪ ኃይል ደበዛው እንዲጠፋ ለመደረግ በቃ።  ጣሊያን ድል ከሆነና አፄ ኃይለስላሴ እንደገና ስልጣናቸውን ሲረከቡ ሁሉም ነገር በሳቸው ትከሻ ላይ የወደቀ ነበር ማለት ይቻላል። ጣሊያን ህዝባችንን እንደዚያ እየጨፈጨፈ፣ በሌላ ወገን ደግሞ ሊሰራ የሚችለውን የአገራችንን ህዝብ ከጣሊያኑ ጋር በማሰማራት በአምስት ዐመት ያህል ጊዜ ውስጥ ትላልቅ ከተማዎችን ለመገንባት ችሏል። አንዳንዶች ከተማዎችም በብዙ ሺሆች የሚቆጠርን ህዝብ ለማስተናገድ የሚችሉ የተሟላ የከተማ አገነባብና ተቋማት እንደነበራቸው የማይታበል ሃቅ ነው። ጣሊያንም አገራችንን ሲወር እዚህና እዚያ ኢንዱስትሪዎችን ተክሏል፤ መንገዶችንም ገንብቷል፤ የሬዲዮ ጣቢያም አቋቁሟል። ይሁንና እንግሊዞች አፄ ኃይለስላሴን ይዘው ከመጡ በኋላ የአገዛዙን ድክመት በመመልከት ጣሊያን የተከላቸውን ኢንዱስትሪዎችና የሬዲዮ ጣቢያዎች፣ እንዲሁም የአየር ላይ ባቡር ማስኬጃ የብረት ገመዶችን እየነቀለችና እያፈራረስች ነው ወደ ሌላ የቅኝ ግዛቶቿ ማጋዝ የጀመረችው። ይህም ማለት አፄ ኃይለስላሴ ኢትዮጵያን እንደገና ዘመናዊ ለማድረግ ሲፈልጉ ሀ ብለው መነሳት ነበራባቸው። በጊዜው የአገራችንም ዋናው ድክመት የውጭ ኃይሎችን አሻጥር የሚረዳ ሰፋ ያለ ምሁራዊና ብሄራዊ ባህርይ ያለው የከበርቴ መደብ አለመኖሩ ነው።  ከ1950ዎቹ ዐመታት መጀመሪያ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች ቢስፋፉም፤ ኢንዱስትሪዎችም ቢተከሉምና፣ ሀኪም ቢቶችም ቢስፋፉና መንገዶችም ቢሰሩ፣ በተለይም የትምህርት ቤቶች መስፋፋትና የትምህርት ስርዓቱ ለመሰረታዊና ስር-ነቀል ለሆነ ሁለ-ገብ ዕድገት የሚያመቹ አልነበረም። መንፈስን የሚገልጽና ንቃተ-ህሊናን የሚያዳብር ለመሆን ባለመቻሉ በዚህ ዐይነቱ የተኮላሸ የትምህርት አሰጣጥ ዘዴ ሊፈጠር የቻለው ትዕቢተኛ የሆነና ለብሄራዊ ነፃነቱ የማይቆረቆር ኤሊት ነኝ ባይ ነው። በተለይም የፍጆታ ምርትን ለማምረት ብቻ የተቋቋሙት ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ ቀላል ምርቶችን ከማምረት አልፈው ለተሟላና ለሁለ-ገብ ዕድገት የሚያመቹ አልነበሩም። እንደሚታወቀው የኋላ ኋላ ወደ ውስጥ ያተኮረና ተከታታይነት ያለው ዕድገት የተጎናፀፉ አገሮች ስርዓት ያለው(Systematic Industrialization)  የኢንዱስትሪ ፖለቲካን የተከተሉት በማሽን ኢንዱስትሪ ላይ በማትኮርና፣ ይህንንም ከምርምርና ከዕድገት (Research and Development)  ጋር በማማያዝ ነው። በማሽን ኢንዱስትሪ መኖርና በማኑፋክቸሪንግ አማካይነት ነው የተለያዩ ምርቶችን፣ ማለትም የአጭርና የረጅም ዕድሜ ያላቸውን የምርት መሳሪያዎች ሊያመርቱና ለአምራች ኃይሉም ሊያቀርቡ የሚችሉት። በዚህም አማካይነት ብቻ ነው ግልጽነት ያለው የውስጥ ገበያ(Home Market) ሊያድግና ሊስፋፋ የሚችለው። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ አንድ አገር በባህል፣ ማለትም በስነ-ጽሁፍ፣ በሙዚቃ፣ በስዕል፤ በሳይንሳይዊ ምርምርና በሌሎችም መጥቃ ልትሄድ የምትችለውና በማንኛውም የውጭ ኃይል ለመከበር የምትችለው ይህንን ዐይነቱን የተሟላ የዕድገት ፖሊሲ ስትከተል ብቻ ነው። ይህንን መሰረታዊ የሆነ ለተሟላና ለተስተካከለ የሁለ-ገብ ዕድገት መሰረት ሊሆን የሚችለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ፖሊሲና ለባህላዊ ለውጥ የሚያመቸውን ሂደት የተረዳ ኃይል ሊኖር ባለመቻሉ ዛሬ የወደቅንበት የብሄራዊ ውርደትና ወደ አገር መፈራረስ አደጋ ላይ ልንደርስ በቅተናል። ዛሬም እንደትላንትናው ሁሉም በትናንሽ አስተሳሰብ በመወጠርና ልዩ ልዩ ተንኮሎችን በመፍጠር ለዕድገት የሚያመች የተሟላ ሳይንሳዊ ዕውቀት እንዳይስፋፋ የማይሸርበው ተንኮል ይህ ነው አይባልም። ለአገሩ ብሄራዊ ነፃነት ከመታገልና ለህዝቡ የሚሆን አስተማማኝ ሁኔታ ከመፍጠር ይልቅ ለነጭ የኦሊጋርኪ መደብ የበላይነት ካለደርኩ እያለ እዚህና እዚያ የሚቅበዘበዘው ኃይል ቁጥሩ ትንሽ ነው አይባልም። አብዛኛው ደግሞ በጥራዝ ነጠቅ የአካዴሚክስ ዕውቀት የተካነ በመሆኑ ከዚህ በመላቀቅ ሰፋ ያለ ምርምርና ጥናት ለማድረግ አይፈልግም። በአካዴምክስ ዕውቀት ብቻ እየኮራ አገሩ ወደ አዘቅት ውስጥ ስትወድቅ ዝም ብሎ እየተመለከተ ነው። ይህ ዐይነቱ የህብረተሰብ ኃይል በዚህች ዓለም ለምን እንደሚኖርና ተልዕኮውም ምን እንደሆነ የተረዳ ባለመሆኑ ከራሱ ጊዜያዊ ጥቅም ባሻገር ለማሰብ የሚችል አይደለም። ስለሆነ ይህ ዐይነቱ የህብረተሰብ ኃይል ለተሟላ ዕድገት እንቅፋት የሆነነ የህዝባችንን ድህነትና ኋላ-ቀርነት የሚያራዝም ነው ማለት ይቻላል።

 

ያም ሆነ ይህ በአፄው ዘመን አንዳንድ ለውጦች ቢታዩም በተለይም የሰፊውን ህዝብ ፍላጎት ለሟሟላት የሚችሉ ባለመሆናቸውና፣ ከዚህም በላይ በየቦታው የመስፋፋት ኃይላቸው ደካማ በመሆኑ የተነሳ ወደ ውስጥ ያተኮረ  ኢኮኖሚያዊ ግንባታ ማካሄድ አልተቻለም። በአፄ ኃይለስላሴ ዘመንም ህዝቡን የሚያስተሳስረው ትንናንሽና ትላልቅ መንደሮችና ከተማዎች ስርዓት ባለው መልክ ባለመገንባታቸውና፣ ከተማዎችን በአማረ መልክ የመገንባት አስፈላጊነት የተረዳ ኃይል ባለመኖሩና፣ በተለይም ሰፊው ህዝብ ከአንድ ቦታ ወደሌላ ቦታ ለመጓዝ እንዲችል የባቡር ሃዲዶች ባለመዘርጋታቸው የተነሳ በበቁሎና በእግሩ የሚጓዘው የህብረተሰብ ክፍል ቁጥሩ ትንሽ አልነበረም። የእርሻ መስኩም በተለያየ ደረጃ ዘመናዊና ምርታማ እንዲሆን በጊዜው አስፈላጊው የጥገና ለውጥ ስራዎች ባለመሰራታቸው ህዝባችን በተደጋጋሚ ለሚከሰት ረሃብ ይጋለጥ ነበር። አፄውና አገዛዛቸው በጊዜው የነበረውንና የሰፈነውን ሰላምና፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነበረውን በጊዜው ለሁለ-ገብ ዕድገት የሚያመቸውን ሁኔታ ባለመረዳትና አስፈላጊውን እርምጃ ተግባራዊ ለማድረግ በላመቻላቸው ህዝባችንና አገራችን በቀላሉ ሊደፈሩበት የሚችሉበትን ሁኔታ ሳያውቁት አመቻችተው ሂደዋል ማለት ይቻላል። በአፄው ዘመን እዚያው በዚያው ኋላ-ቀርነትና የተኮላሸ የዘመናዊነት ዕርምጃዎች አንድ ላይ ይጓዙ ስለነበር፣ በተለይም የተማረው ኃይል በግልጽ የሚመራበት መመሪያ አልነበረውም። ቤተ-መጻህፍትና ሌሎች የዕውቀት ማዕከሎች በየቦታው ባለመስፋፋታቸው የተነሳ በወጣትነት ጊዜው ለጭንቅላት ዕድገትና ለፈጠራ ስራ የሚጠቅሙ ዕውቀቶችን ለመቅሰም የሚችለው ወጣት ጊዜውን ባልባሌ ቦታዎች ነበር የሚያባክነው ማለት ይቻላል።

 

ይህንን ዐይነት ያልተሟላ ዕድገትና፣ ህዝባችንን በድህነትና በተደጋጋሚ ረሃብ የሚያሰቃየውን ሁኔታ ለማሰወገድ በአብዮት ወቅት አንዳንድ የጥገና ለውጦች ቢካሄዱም በጊዜው በነበረው የርስ በርስ መሻኮት የተነሳና፣ በተለይም ስልጣንን የጨበጠው ደርግ የሚባለው ከወታደሩ የተውጣጣ ያልተገለጸለትና በምሁራዊ ዕውቀት ጭንቅላቱ ያልታነፀ የወታደር ስብስብ በጊዜው የሚታዩ ችግሮችን በፖለቲካ ዘዴ ከመፍታት ይልቅ ወደ አመፅ ነው ያመራው። ሌሎች ታጋይ ነን ይሉ የነበሩ ኃይሎችም በጊዜው የነበረውን ድክመት በመረዳት ሁኔታውን ለማርገብ ዘዴ ከመፈለግ ይልቅ በተቀጣጠለው እሳት ላይ የባሰውን ቤንዚን ማርከፍከፍ ነው የጀመሩት። ይህ ዐይነቱ በብስለትና በምሁራዊ ዕውቀት የማይመራ ፖለቲካ የሚሉት ፈሊጥ ቀስ በቀስ የደርግን አገዛዝ ´ከሰረሰረ በኋላ አገርን ለመከፋፈልና ለማዳከም ለሚችሉ በጣም አደገኛ ኃይሎች ነው ሁኔታውን አመቻችቶ ጥሎ የሄደው።  የደርግንና የተቀረውን የሚሊተሪና የስለላ ኃይል የዕውቀት ደረጃ ስንመለከት ደግሞ አብዛኛዎቹ በአሜሪካን ጭንቅላትን በሚያደነዝዝ “የሚሊተሪ ሳይንስ” ብለው በሚጠሩት የሰለጠኑ ናቸው። የቢሮክራሲውና የቴክኖክራሲውም አሰለጣጠን አገርን በተሟላ መንገድ ላይ እንዲገነባ በሚያደርግ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ ባለመሆኑ በቀላሉ ለአሜሪካኖች የሚያጎበድድና አገርንም የሚሸጥ ነበር። በሌላ ወገን ግን ብሄራዊ ነፃነታቸውን ያስከበሩና ጠንካራ ኢኮኖሚን በመገንባት ህዝባቸውን ከድህነት በማላቀቅ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ የሁኑ አገሮችን የመንግስታት አወቃቀር ስንመለከት አንዳቸውም መንግስታት ውጭ ሰልጠነውና የአሜሪካንን ርዕዮተ-ዓለምን በሚያራምዱና አገራቸውን በሚያደኸዩ አጎብዳጅ ኃይሎች አልተሰገሰጉም። እንደነዚህ ዐይነት ኃይሎች ካሉም በፍጥነት ነው እርምጃ የሚወሰድባቸው። ወደ አገራችን ስንመጣ ግን ለአሜሪካን የስለላ ድርጅት መስራትና አገርን ማፈራረስ እንደትልቅ ነገር ነው የሚታየው። እንደዚህ ዐይነቱም ሰው  ነው በጣም  የሚከበረው። ይህም የሚያረጋግጠው የአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኤሊት ጭንቅላትና የአንዳንድ የታወቁ ሰዎች ተከታዮቻቸው ጭንቅላት የቱን ያህል ጨቅላ እንደሆነ ነው።

 

ህወሃት ወይም ወያኔ የሚባለው አገዛዝ በአሜሪካንና በእንግሊዝ ኢምፔሪያሊስት ኃይሎችና በሰለላ ድርጅቶቻቸው ተደግፎና ተረድቶ ስልጣንን ሲጨብጥ ሆን ብሎ የጀመረው ስራ አገርን በፍጥነት ማዳከምና ብሄራዊ ነፃነቷ እንዲደፈር ማድረግ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ የጎሳ ፌዴራሊዝም ብሎ የሚጠራውንና የሚያቆላብሰውን አገርን የሚሰነጣጥቅውንና  የህዝቡን ብሄራዊ ስሜት የሚያዳክመውን ነው ተግባራዊ ያደረገው። ከዚህም በላይ ይህ ዐይነቱ ሂደት ጠንካራ ህብረ-ብሄር እንዳይመሰረት የሚያደርግ አደገኛ አካሄድ ነው። ተፈጥሮአዊ ከሆነው የህብረ-ብሄር ምስረታ አንፃርም ስንመረምረው የኋሊት ጉዞ የሆነና የህብረ-ብሄርንና የተፈጥሮ ህግን የሚጥስ ኢ-ሳይንሳዊ አካሄድ ነው።  በመሰረቱ የጎሳ ፌዴራሊዝም  ለብሄረሰቦች ዕውነተኛ ነፃነትን ያጎናፀፈና የፈጠራ ኃይላቸው እንዲዳብር ያደረገ ሳይሆን ለራሱ ለወያኔ የከፋፍለህ ግዛው ፖሊስና በየአካባቢው የሚገኙ የጥሬ-ሀብቶችን እንዲበዘብዝ የሚያመቹ ናቸው። ህወሃት ወይም ወያኔ በዓለም ኮሙኒቲውና ተላላኪዎቻቸው በሆኑት፣ በዓለም የገንዘብ ድርጅትና(IMF) በዓለም ባንክ(World
https://amharic-zehabesha.com/archives/187409
አዲስ አበቤ ተናሳ! | ሁላችን ወጠን እንግጠማቸው የጀግናው ፋኖ አቀባበር ስነ ስርዓት በጎጃም ሙሉ ቪድዮ
https://youtu.be/gbuE0lWPrDg?si=oKMCLyt_j8VkZxFW

 

ሁላችን ወጠን እንግጠማቸውየጀግናው ፋኖ አቀባበር ስነ ስርዓት በጎጃም ሙሉ ቪድዮ

 

https://youtu.be/tG2h0dUK3sc?si=0gVGP09Vfs1M_z37

 

https://youtu.be/hdeYa1c7Ajw?si=_y6XmAU_y2tLtVn9
https://amharic-zehabesha.com/archives/187412
      በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ሁለ-ገብ የኢኮኖሚ ዕድገት ለብሄራዊ ነፃነት መከበርና ለተሟላ ሰላም መስፈን ወሳኝ ነው!
ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)

ህዳር 26፣ 2023

 

በአገራችንም ሆነ በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ያለው ትልቁ ችግር ወደ ውስጥ ያተኮረ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ሰፋ ያለ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ እንዲሁም የሚያማምሩ ከተማዎችና መንደሮች መገንባትና፣ እነዚህም በተለያዩ የመመላለሻ ዘዴዎች መያያዝ እንዳለባቸው ያለመረዳት ነው። አንድ ህዝብ በአስተማማኝ የኑሮ ሁኔታ ሲኖርና፣ የሰለጠነና በሁሉም አቅጣጫ በምሁራዊ ዕውቀት መንፈሱ የዳበረ ሰፋ ያለ የህብረተሰብ ክፍል ካለ አንድ አገርና ህዝብ በቀላሉ በውጭ ኃይሎች ሊታለሉና ህዝቦቻቸውም ከውጭ በሚመጣ የተበላሸ ባህል ሰለባ በመሆንና በገንዘብ በመታለል የአገራቸውን ህልውና በፍጹም አይሸጡም።  እንደሚታወቀው አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች በባሪያ ንግድ የተነሳና፣ በኋላ ላይም በቅኝ-ግዛት አስተዳደር ውስጥ በመውደቃቸው ወደ ውስጥ ያተኮረ በስራ-ክፍፍል ላይ የተመሰረተ ማህበረሰብ እንዳይመሰርቱ ተደርገዋል። የቅኝ ግዛት አስተዳዳሪዎች አፍሪካን እናሰለጥናለን ብለው ቢሄዱም ያደረጉት ነገር እስከዚያ ጊዜ ድረሰ የነበሩትን ዕድገቶችና የታሪክ ቅርሶች እንዳሉ ነው ያወደሙባቸው። አንዳንድ በማደግ ላይ የነበሩ ከተማዎችንና ቤተመንግስቶችን እንዳለ ነው ያፈራረሱባቸው። በተጨማሪም በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ የዕድገትና የስልጣኔ ምልክቶች የነበሩ የታሪክ ቅርፆችን እየነቃቀሉ ነው ወደ አዎሮፓ ዋና ዋና ከተማዎች ማጋዝ የጀመሩት። እነዚህ  ከብረታ-ብረት፣ ከዕብነ-በረድ፣ ከተለያዩ የዲንጋይ ዐይነቶችና ከእንጨት የተሰሩ የሚያማምሩ ቅርፃ ቅርፆች በአሁኑ ወቅት በየሙዚዬሞች ውስጥ በመቀመጥ በህዝብ የሚጎበኙ ናቸው። በዚህ የተነሳና የኋላ-ኋላም ከቅኝ-ግዛት ከተላቀቁና ነፃነታቸውን ተቀዳጁ ከተባሉ በኋላ በተዘዋዋሪ የቅኝ-ግዛት እንዲሆኑ ነው የተደረገው። የተለያዩ በነፃ ገበያ ስም ሳይንሳዊ ያልሆኑና ወደ ውስጥ ህዝባዊ ሀብት ሊፈጥሩ የማይችሉ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ብለው የሚጠሯቸውን ራሳቸው ባቋቋሟቸው የዓለም አቀፍ ተቋማት ብለው በሚጠሯቸው እያስገደዱ ነው ወደ ተግባርነት እንዲመነዘሩ ለማድረግ የበቁት። የነጩ የኢሊጋርኪ መደብ በማንአለኝበት መንፈስ በመወጠር አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች  በራሳቸው ጥረትና በምሁሮቻቸው ጥናትና ክርክር ጠንካራ ኢኮኖሚና ማህበረሰብ እንዳይገነቡ  የዕድገቱን መንገድ ለመዝጋት በቅቷል። አንዳንዶች ከዚህ ዐይነቱ የስውር ቅኝ አገዛዝ ለመላቀቅ ጥረት ሲያደርጉና አንዳንድ ዕርምጃዎች ሲወስዱ የመንግስት ግልበጣ ሊደረግባቸው ችሏል። አንዳንዶች በራሳቸው ጓዶች እንዲገደሉ ለመደረግ በቅተዋል። ይህም የሚያመለክተው በምንም ዐይነት የነጩ ኦሊጋርኪ መደብ ጥቁር አፍሪካውያን ጠንካራና የበለፀገ ማህበረሰብ እንዳይገነቡ ቀን ከሌት እንደሚሰራና፣ ካስፈለገም በተዘዋዋሪ የርስ በርስ ጦርነት በማስነሳት የኋላ-ቀርነት ዘመኑ እንዲራዘም እንደሚያደርግ ነው። ዛሬ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች የሚካሄዱት የርስ በስር ጦርነቶች በመሰረቱ የውክልና ጦርነቶች ሲሆኑ፣ የሚካሄዱትም የእስላም አክራሪን ኃይል ለመዋጋትና የራስን የጂኦ ፖለቲካ ጥቅም ለማስጠበቅ በሚል ስም ነው።

 

ወደ አገራችን ስንመጣ ግን አገራችን ለጥቂት ጊዜያት ካልሆነ በስተቀር የቅኝ ግዛት ሰለባ ባትሆንም ህዝባችን ብሄራዊ ነፃነቱን ለማስከበር የሚያስችለው በሳይንስና በቴክሎጂ ላይ የተመሰረተ፣ የሚያማሩ ከተማዎችና መንደሮች፣ እንዲሁም እነዚህን የሚያያዙ ልዩ ልዩ የመገናኛ ዘዴዎች ባለመዘርጋታቸው ህዝባችንና አገራችን የመከበር ዕድል በፍጹም አላገጠማቸውም። ይህንን ዐይነቱን ጉድለት የተረዳ የተገለጸለት ምሁራዊ ኃይል ብቅ ማለት ባለመቻሉና፣ ጥቂት ተማርኩ ነኝ የሚለው የአሜሪካ ርዕዮተ-ዓለም ሰለባ በመሆንና የእሱም የጥፋት ድርጊት ተላላኪ በመሆን የአገራችን ብሄራዊ ነፃነት እንዳይከበርና፣ አልፎም በመሄድ አገራችን እንድትፈራርስ የማይሰራው ሴራ የለም። ይህ ዐይነቱ የመንፈስ ድክመትና ለውጭ ኃይል መገዛትና ብሄራዊ ነፃነትን በመሸጥ አገራችን በጠንካራ መሰረት ላይ እንዳትገነባ ማድረግ ከሁሉም ብሄረሰብ በተውጣጡ ኤሊቶች የሚሳበብ ሳይሆን ከተወሰኑ ብሄረሰቦች የተውጣጡ ኤሊቶች ዋና ተግባር ሊሆን በቅቷል። በተለይም ከአደሬ ብሄረሰብ፣ ከአማራው፣ ከትግሬና ከኦሮሞ ብሄረሰብ የተውጣጡና የመማር ዕድል ያገጠማቸው ኢሊት ነን ባዮች ንቃተ-ህሊናቸው በጣም ዝቅተኛ ስለሆነ ባለፉት አርባና ሃምሳ ዓመታት በአሜሪካን የስለላ መረብ ውስጥ በመካተት የዕድገትና የብሄራዊ ነፃነት ጠንቅ በመሆን ህዝባችንና አገራችን ፍዳቸውን እያዩ እንዲኖሩና እንዲዋረዱም ለማድረግ በቅተዋል።  ያም ሆነ ይህ ይህንን ጉዳይ ዘርዘር በማድረግና በማነፃፀር  ከህብረ-ብሄር ምስረታ አኳያ የብሄራዊ ነፃነትንና  የየዜጎችን መብት መከበር ጉዳይ ጠጋ ብለን እንመልከተው።

 

እንደሚታወቀው በ18ኛውና በ19ኛው ክፍለ-ዘመንም ሆነ ከዚያ ቀደም ብሎ ህብረ-ብሄሮች እንደዛሬው ዘመን በአንድ ግዛት ውስጥ ተጠቃለውና መለያ የሚሆናቸው የየራሳቸው ባንዲራ ሳይኖራቸው በነበረበት ዘመን ኃያል ነን የሚሉ መንግስታት ደካማ አገሮችን ጦራቸውን በማዝመት ነው በቀጥታ የሚወሯቸው የነበረው። በቀድሞው ዘመን አንዳንድ አገዛዞች በውጭ ኃይሎች ግዛቴ ተደፈረ፣ ተወረርኩም በማለት ህዝባቸውን በማስተባበር የወረራቸውን ኃይል መክተው ለመመለስ የሚጠቀሙበት ዘዴ በቀጥታ ከወረራቸው ኃይል ጋር በመፋለም ነው ብሄራዊ ነፃነታቸውን የሚያስከብሩት። በዚህ መልክ በቀጥታ የተወረሩ አገሮች አገዛዞች የተገለፀላቸው ከሆነ እንደገና ላለመወረር ሲሉ ቶሎ ብለው የሚወስዱት እርምጃ የተበታተነውን ህዝብና  በአንድ ማዕከላዊ አገዛዝ አልገዛም በማለት የሚያስቸግረውን የክልል አገዛዝ በመሰብሰብና በማታለል፤ እንዲያም ሲል በማሸነፍ ወደ ውስጥ ያተኮረ ሁለ-ገብ የሆነ የአገር ግንባታና ለሰፊው ህዝብ የስራ መስክ የሚከፍት ትናንሽና የማዕከለኛ ኢንዱስትሪዎችን በማቋቋም ነው አገራቸውን ዘመናዊ ለማድረግ የበቁት። ከዚህም አልፈው በመሄድ ህዝባቸውና ቀስ በቀስ እያደገ የሚመጣው የንዑስ ከበርቴው የህብረተሰብ ክፍል ብሄራዊ ስሜት እንዲያድርባቸውና አገራቸውንም በጋራ እንዲጠብቁ የሚወስዱት እርምጃ መንፈስን የሚሰበስቡና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚያስተናግዱ ከተማዎችንና መንደሮችን መገንባት ነው።  ከዚያም አልፈው በመሄድ ከተማዎችንና መንደሮችን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በማስተሳሰር የንግድ ልውውጥና እንቅስቃሴ እንዲዳብር ማድረግ ነው። በተጨማሪም እዚህና እዚያ ለመኖሪያ የሚሆኑ ቤቶችን መገንባት፣ የተለያዩ የትምህርት ዘርፎችንና የሙያ ማስልጠኛ ማዕከሎችን በማስፋፋትና፣  ክሊኒኮችንና የገበያ አዳራሾችን፣ እንዲሁም  ለሰፊው ህዝብ የመዝናኛ ማዕከሎችን በመገንባት አንድ ህዝብና ተከታታዩ ትውልድ ተከብረው የሚኖሩበት አገር ጥለው ያልፋሉ። ለሰፊው ህዝብ የሚጠቅሙና ግልጋሎትም የሚሰጡ የሰለጠኑ ተቋማት በመገንባት ማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ ለህዝባቸው አለኝታ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ። ተከታታይ አገዛዞችም በዚህ ዐይነቱ አገርን መገንባትና የህዝብ አገልጋይ መሆን መንፈስ ተኮትኩተው ስለሚያድጉ እነሱም በበኩላቸው አገራቸውን በተሻለ መልክ በመገንባት ለተከታታዩ አገዛዝ የሚሆን በቀላሉ ሊደፈርና በተለያዩ የውስጥ ኃይሎች በቀላሉ ሊረበሽ ወይም ሊናጋ የማይችል አገርና ማህበረሰብ ጥለው ያልፋሉ።

 

በዚህ መልክ በ19ኛው ክፍለ-ዘመን በቀጥታ በውጭ ኃይሎች ይደፈሩ የነበሩ እንደጀርመን፣ ጃፓን፣ የኋላ ኋላ ደግሞ ደቡብ ኮርያና፣ ከ1949 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ቻይና  እንደገና በውጭ ኃይሎች ላለመወረር ሲሉ እንደምንም ብለው በድል አድራጊነት ከወጡ በኋላ ተግባራዊ ማድረግ የጀመሩት በሁለ-ገብ የአገር ግንባታ ላይ በመሰመራት ነው አገሮቻቸውን በጠንካራ መሰረት´ ላይ ለመግንባት የቻሉት። ለዚህ ነው ጀርመን እስከ 1871 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ የውጭ ኃይሎች በመወረሯና ወደ ውስጥ ያተኮረ የአገር ግንባታ ማካሄድ ባለመቻሏ ይህንን  ድክመት የተረዱት የፕረሽያ ሞናርኪዎችና ሁለ-ገብ ዕውቀት ያላቸው ምሁራን ዋናውን ምክንያት በመፈለግና የሚያስቸግሯቸውን ኃይሎች ድል በማድረግና ሌሎችንም በማታለል በፈረንሳይ ላይ ድልን ከተቀዳጁ በኋላ በሙሉ ኃይል ወደ ውስጥ ያተኮረ ሁለ-ገብ የአገር ግንባታ ማካሄድ የጀመሩት። በተለይም ለዕውቀት ማዕከላዊ ቦታ በመስጠትና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚጠቅም ሁለ-ገብ የሆነ የትምህርት የጥገና ለውጥ በማካሄድና፣ በተለይም በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ትምህርት በማስፋፋት፣ ከዚህም በላይ ለኢንጂነሪንግና ለዕደ-ጥበብ ሙያዎች ከፍተኛ አትኩሮ በመስጠት ነው ጀርመን በአንድ ትውልድ ጊዜ ውስጥ እንግሊዝንና ፈረንሳይን ቀድማ ለመሄድ የቻለችው። ተግባራዊም በሆነው ሰፋና ጠለቅ ያለ የትምህርት የጥገና ለውጥ አማካይነት ነው ጀርመን በ20ኛው ክፍለ-ዘመን ሁለት-ሶስተኛውን የሚሆን የኖቭል ዋጋ ተሸላሚ ሳይንቲስቶችን ማፍራት የቻለችው።

 

ወደ አገራችን ስንመጣ ጣሊያን ሁለት ጊዜ ከመውረሩ በፊት ኢትዮጵያችን በተለያዩ የጎረቤት አገሮች ትደፈር ነበር። በጊዜው ህዝቡን የሚያስተባብር ማዕከላዊ ግዛት ባለመኖሩና በየክልሉም ፊዩዳላዊ አገዛዝች በመኖራቸው ይህ ዐይነቱ የውስጥ ሽኩቻ ለውጭ ኃይሎች ወረራ አመቺ ነበር። ይህንን ድክመት የተረዱት አፄ ቴዎድሮስ አሻፈረኝ የሚለውን ኃይል በሙሉ በማሸነፍ ነበር የድርጅትን አስፈላጊነት በመረዳት አገራቸውን የኢንዱስትሪ አብዮት ባለቤት ለማድረግ ከእንግሊዙ ሞናርኪ ጋር ይጻጻፉ የነበረው። በአንድ በኩል የጥገና ለውጥን አሻፈረኝ የሚለው ፊዩዳላዊ ኃይልና ሌሎች፣ በሌላው ወገን ደግሞ በእንግሊዝ መንግስት ተንኮለኛነት የተነሳ አፄ ቴዎድሮስ የተመኙትን አገርን በአስተማማኝ መሰረት የመግንባት ዕድል አላገጠማቸውም። በጊዜው አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዙ ንግስት ከነበሩት ከንግስት ቪክቶሪያ ጋር ይጻጻፉ የነበረው ኢንጂነሮችን፣  የዕደ-ጥበብ ሙያተኞችን፣ የከተማ ግንባታ አዋቂዎችንና ሌሎችንም ለአገር ግንባታ ይጠቅማሉ የሚሏቸውን ሙያተኞችን እንዲልኩላቸው ነበር። ንግስት ቪክቶሪያና አገዛዛቸውም አፄ ቴዎድሮስ የጠየቁትን ሙያተኞች ከመላክ ይልቅ ሃይማኖትን የሚያስፋፉና የሚሰብኩ ቄሶችን  ነበር። በዚህ ድርጊት የተናደዱት አፄ ቴዎድሮስ የተላኩትን ቄሶችንና ሌሎችን ቀሳውስቶች በማሰር ነው ብረታ-ብረት እንዲቀጥቅጡና ልዩ ልዩ መሳሪያዎችንም እንዲሰሩ ያስገድዷቸው የነበረው።  በአፄ ቴዎድሮስ ድርጊት የተናደደችው እንግሊዝ ጦሯን በመላክ ነው አፄ ቴዎድሮስ በሰው ልጅ ከምገድል ይልቅ በማለት ራሳቸውን የገደሉት። አፄ ቴዎድሮስ ራሳቸውን ካጠፉ በኋላ አገርን በጠንካራ መሰረት ላይ መገንባቱ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ  የኋላ ኋላ በአፄ ምኒልክ ትከሻ ላይ ነው ሊወድቅ የቻለው።

 

አፄ ምኒልክ እ.አ. አ በ1896 በአደዋ  በጣሊያን ላይ ድልን ከተቀዳጁ በኋላ ተግባራዊ ማድረግ የጀመሩት እርምጃ ቢያንስ ህዝባቸውን የሚያስተሳስርላቸውንና ብሄራዊ ስሜቱ እንዲያድር የሚያደረገውን አገርን የመገንባት የመጀመሪያውን እርምጃ ነው መውሰድ የጀመሩት። ትምህርት ቤቶችን መክፈት፣ ድልድዮችን ማሰራት፣ የብሄራዊ ባንክ መክፈትና ለመገበያያ የሚሆን በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው ገንዘብ አትሞ ማሰራጨት፣ የባቡር ሃዲድ ማሰራትና የፖስታ ቤት መክፈት ለህብረ-ብሄር ምስረታ የሚያመቹb  የመጀመሪያዎች  እርምጃዎች ነበሩ። ህብረ-ብሄር ለመመስረት የሚያስችሉ በየቦታው የተሰሩና የተገነቡ ከተማዎች ስላልነበሩና፣ በተለይም ወደ ደቡቡ የኢትዮጵያ ግዛት አብዛዎችም መሬቶች ጠፍ ስለነበሩና፣ በየቦታውም የተገለጸለት ወይም የተማረ ኃይል ባለመኖሩ አፄ ምኒልክም  ሀ ብለው መጀመር ነበረባቸው። ወደ ማዕከላዊ መንግስት አካባቢም ስንመጣ በሁለ-ገብ ዕውቀት የሰለጠነ ምሁራዊ ኃይል ባለመኖሩ የአፄ ምኒልክን ፍላጎትና ምኞት በመረዳት የማህበራዊ መሰረት በመሆን ምኞታቸውን ዕውን የሚያደርግ ኃይል ሊኖር ባለመቻሉ ኢትዮጵያን ዘመናዊ የማድረጉ ጉዳይ ሙሉ በሙሉ ሊሳካ አልቻለም።  ከተማዎችንና መንደሮችን በአስተማማኝ መሰረት  ላይ መገንባት አልተቻለም። የተዘረጋው የባቡር ሃዲድ ለውጭ ገበያ እንዲያመች በመሆኑ ለውስጥ ገበያ ዕድገት የሚያመቹ ልዩ ልዩ የመገናኛ ዘዴዎች ለመገንባት ባለመቻላቸውና፣ ይህንንም ተግባራዊ የሚያደርግ በኢንጂነሪንግ ሙያ የሰለጠነ የህብረተሰብ ኃይል ባለመኖሩ ለአንድ አገር ብሄራዊ ነፃነት መከበር አስፈላጊ የሆነው የአገር ውስጥ ገበያ ዕድገት አስፈላጊው አትኩሮ ሊሰጠው በፍጹም አልተቻለም። ከዚህም ጋር ተያይዞ ለብሄራዊ ገበያና ለብሄራዊ ሀብት መፈጠር በጣም አስፈላጊ የሆነው የማሺን ኢንዱስትሪ ስለማይታወቅና በዚህም የተነሳ ተግባራዊ ለመሆን ባለመቻሉ የአገራችን ህዝብ ከእጅ ወደ አፍ አልፎ ሊሄድ በማይችል የግብርናና የዕደ-ጥበብ ሙያ ነው ይተዳደር የነበረው። ይሁንና አፄ ምኒልክ ጥለው የሄዱት መሰረት ህዝባችን ብሄራዊና አገራዊ ስሜት እንዲያድርበት ለማድረግ  በቅቷል ማለት ይቻላል።

 

አፄ ምኒልክ ከሞቱ በኋላ አገርን በፀና መሰረት ላይ ለመገንባት የጃፓናዊ ዐይነት እንቅስቃሴ ቢኖርምና ቀስ በቀስም ምሁራዊ ኃይሎች ብቅ ቢሉም በሁለተኛው የጣሊያን ወረራ ምክንያት የተነሳ በ1920ዎች የነበረው የዘመናዊነት እንቅስቃሴ ሊዳፈን ቻለ። በጊዜው የነበረው ትንሽ ምሁራዊ ኃይል በጣሊያኑ ወራሪ ኃይል ደበዛው እንዲጠፋ ለመደረግ በቃ።  ጣሊያን ድል ከሆነና አፄ ኃይለስላሴ እንደገና ስልጣናቸውን ሲረከቡ ሁሉም ነገር በሳቸው ትከሻ ላይ የወደቀ ነበር ማለት ይቻላል። ጣሊያን ህዝባችንን እንደዚያ እየጨፈጨፈ፣ በሌላ ወገን ደግሞ ሊሰራ የሚችለውን የአገራችንን ህዝብ ከጣሊያኑ ጋር በማሰማራት በአምስት ዐመት ያህል ጊዜ ውስጥ ትላልቅ ከተማዎችን ለመገንባት ችሏል። አንዳንዶች ከተማዎችም በብዙ ሺሆች የሚቆጠርን ህዝብ ለማስተናገድ የሚችሉ የተሟላ የከተማ አገነባብና ተቋማት እንደነበራቸው የማይታበል ሃቅ ነው። ጣሊያንም አገራችንን ሲወር እዚህና እዚያ ኢንዱስትሪዎችን ተክሏል፤ መንገዶችንም ገንብቷል፤ የሬዲዮ ጣቢያም አቋቁሟል። ይሁንና እንግሊዞች አፄ ኃይለስላሴን ይዘው ከመጡ በኋላ የአገዛዙን ድክመት በመመልከት ጣሊያን የተከላቸውን ኢንዱስትሪዎችና የሬዲዮ ጣቢያዎች፣ እንዲሁም የአየር ላይ ባቡር ማስኬጃ የብረት ገመዶችን እየነቀለችና እያፈራረስች ነው ወደ ሌላ የቅኝ ግዛቶቿ ማጋዝ የጀመረችው። ይህም ማለት አፄ ኃይለስላሴ ኢትዮጵያን እንደገና ዘመናዊ ለማድረግ ሲፈልጉ ሀ ብለው መነሳት ነበራባቸው። በጊዜው የአገራችንም ዋናው ድክመት የውጭ ኃይሎችን አሻጥር የሚረዳ ሰፋ ያለ ምሁራዊና ብሄራዊ ባህርይ ያለው የከበርቴ መደብ አለመኖሩ ነው።  ከ1950ዎቹ ዐመታት መጀመሪያ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች ቢስፋፉም፤ ኢንዱስትሪዎችም ቢተከሉምና፣ ሀኪም ቢቶችም ቢስፋፉና መንገዶችም ቢሰሩ፣ በተለይም የትምህርት ቤቶች መስፋፋትና የትምህርት ስርዓቱ ለመሰረታዊና ስር-ነቀል ለሆነ ሁለ-ገብ ዕድገት የሚያመቹ አልነበረም። መንፈስን የሚገልጽና ንቃተ-ህሊናን የሚያዳብር ለመሆን ባለመቻሉ በዚህ ዐይነቱ የተኮላሸ የትምህርት አሰጣጥ ዘዴ ሊፈጠር የቻለው ትዕቢተኛ የሆነና ለብሄራዊ ነፃነቱ የማይቆረቆር ኤሊት ነኝ ባይ ነው። በተለይም የፍጆታ ምርትን ለማምረት ብቻ የተቋቋሙት ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ ቀላል ምርቶችን ከማምረት አልፈው ለተሟላና ለሁለ-ገብ ዕድገት የሚያመቹ አልነበሩም። እንደሚታወቀው የኋላ ኋላ ወደ ውስጥ ያተኮረና ተከታታይነት ያለው ዕድገት የተጎናፀፉ አገሮች ስርዓት ያለው(Systematic Industrialization)  የኢንዱስትሪ ፖለቲካን የተከተሉት በማሽን ኢንዱስትሪ ላይ በማትኮርና፣ ይህንንም ከምርምርና ከዕድገት (Research and Development)  ጋር በማማያዝ ነው። በማሽን ኢንዱስትሪ መኖርና በማኑፋክቸሪንግ አማካይነት ነው የተለያዩ ምርቶችን፣ ማለትም የአጭርና የረጅም ዕድሜ ያላቸውን የምርት መሳሪያዎች ሊያመርቱና ለአምራች ኃይሉም ሊያቀርቡ የሚችሉት። በዚህም አማካይነት ብቻ ነው ግልጽነት ያለው የውስጥ ገበያ(Home Market) ሊያድግና ሊስፋፋ የሚችለው። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ አንድ አገር በባህል፣ ማለትም በስነ-ጽሁፍ፣ በሙዚቃ፣ በስዕል፤ በሳይንሳይዊ ምርምርና በሌሎችም መጥቃ ልትሄድ የምትችለውና በማንኛውም የውጭ ኃይል ለመከበር የምትችለው ይህንን ዐይነቱን የተሟላ የዕድገት ፖሊሲ ስትከተል ብቻ ነው። ይህንን መሰረታዊ የሆነ ለተሟላና ለተስተካከለ የሁለ-ገብ ዕድገት መሰረት ሊሆን የሚችለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ፖሊሲና ለባህላዊ ለውጥ የሚያመቸውን ሂደት የተረዳ ኃይል ሊኖር ባለመቻሉ ዛሬ የወደቅንበት የብሄራዊ ውርደትና ወደ አገር መፈራረስ አደጋ ላይ ልንደርስ በቅተናል። ዛሬም እንደትላንትናው ሁሉም በትናንሽ አስተሳሰብ በመወጠርና ልዩ ልዩ ተንኮሎችን በመፍጠር ለዕድገት የሚያመች የተሟላ ሳይንሳዊ ዕውቀት እንዳይስፋፋ የማይሸርበው ተንኮል ይህ ነው አይባልም። ለአገሩ ብሄራዊ ነፃነት ከመታገልና ለህዝቡ የሚሆን አስተማማኝ ሁኔታ ከመፍጠር ይልቅ ለነጭ የኦሊጋርኪ መደብ የበላይነት ካለደርኩ እያለ እዚህና እዚያ የሚቅበዘበዘው ኃይል ቁጥሩ ትንሽ ነው አይባልም። አብዛኛው ደግሞ በጥራዝ ነጠቅ የአካዴሚክስ ዕውቀት የተካነ በመሆኑ ከዚህ በመላቀቅ ሰፋ ያለ ምርምርና ጥናት ለማድረግ አይፈልግም። በአካዴምክስ ዕውቀት ብቻ እየኮራ አገሩ ወደ አዘቅት ውስጥ ስትወድቅ ዝም ብሎ እየተመለከተ ነው። ይህ ዐይነቱ የህብረተሰብ ኃይል በዚህች ዓለም ለምን እንደሚኖርና ተልዕኮውም ምን እንደሆነ የተረዳ ባለመሆኑ ከራሱ ጊዜያዊ ጥቅም ባሻገር ለማሰብ የሚችል አይደለም። ስለሆነ ይህ ዐይነቱ የህብረተሰብ ኃይል ለተሟላ ዕድገት እንቅፋት የሆነነ የህዝባችንን ድህነትና ኋላ-ቀርነት የሚያራዝም ነው ማለት ይቻላል።

 

ያም ሆነ ይህ በአፄው ዘመን አንዳንድ ለውጦች ቢታዩም በተለይም የሰፊውን ህዝብ ፍላጎት ለሟሟላት የሚችሉ ባለመሆናቸውና፣ ከዚህም በላይ በየቦታው የመስፋፋት ኃይላቸው ደካማ በመሆኑ የተነሳ ወደ ውስጥ ያተኮረ  ኢኮኖሚያዊ ግንባታ ማካሄድ አልተቻለም። በአፄ ኃይለስላሴ ዘመንም ህዝቡን የሚያስተሳስረው ትንናንሽና ትላልቅ መንደሮችና ከተማዎች ስርዓት ባለው መልክ ባለመገንባታቸውና፣ ከተማዎችን በአማረ መልክ የመገንባት አስፈላጊነት የተረዳ ኃይል ባለመኖሩና፣ በተለይም ሰፊው ህዝብ ከአንድ ቦታ ወደሌላ ቦታ ለመጓዝ እንዲችል የባቡር ሃዲዶች ባለመዘርጋታቸው የተነሳ በበቁሎና በእግሩ የሚጓዘው የህብረተሰብ ክፍል ቁጥሩ ትንሽ አልነበረም። የእርሻ መስኩም በተለያየ ደረጃ ዘመናዊና ምርታማ እንዲሆን በጊዜው አስፈላጊው የጥገና ለውጥ ስራዎች ባለመሰራታቸው ህዝባችን በተደጋጋሚ ለሚከሰት ረሃብ ይጋለጥ ነበር። አፄውና አገዛዛቸው በጊዜው የነበረውንና የሰፈነውን ሰላምና፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነበረውን በጊዜው ለሁለ-ገብ ዕድገት የሚያመቸውን ሁኔታ ባለመረዳትና አስፈላጊውን እርምጃ ተግባራዊ ለማድረግ በላመቻላቸው ህዝባችንና አገራችን በቀላሉ ሊደፈሩበት የሚችሉበትን ሁኔታ ሳያውቁት አመቻችተው ሂደዋል ማለት ይቻላል። በአፄው ዘመን እዚያው በዚያው ኋላ-ቀርነትና የተኮላሸ የዘመናዊነት ዕርምጃዎች አንድ ላይ ይጓዙ ስለነበር፣ በተለይም የተማረው ኃይል በግልጽ የሚመራበት መመሪያ አልነበረውም። ቤተ-መጻህፍትና ሌሎች የዕውቀት ማዕከሎች በየቦታው ባለመስፋፋታቸው የተነሳ በወጣትነት ጊዜው ለጭንቅላት ዕድገትና ለፈጠራ ስራ የሚጠቅሙ ዕውቀቶችን ለመቅሰም የሚችለው ወጣት ጊዜውን ባልባሌ ቦታዎች ነበር የሚያባክነው ማለት ይቻላል።

 

ይህንን ዐይነት ያልተሟላ ዕድገትና፣ ህዝባችንን በድህነትና በተደጋጋሚ ረሃብ የሚያሰቃየውን ሁኔታ ለማሰወገድ በአብዮት ወቅት አንዳንድ የጥገና ለውጦች ቢካሄዱም በጊዜው በነበረው የርስ በርስ መሻኮት የተነሳና፣ በተለይም ስልጣንን የጨበጠው ደርግ የሚባለው ከወታደሩ የተውጣጣ ያልተገለጸለትና በምሁራዊ ዕውቀት ጭንቅላቱ ያልታነፀ የወታደር ስብስብ በጊዜው የሚታዩ ችግሮችን በፖለቲካ ዘዴ ከመፍታት ይልቅ ወደ አመፅ ነው ያመራው። ሌሎች ታጋይ ነን ይሉ የነበሩ ኃይሎችም በጊዜው የነበረውን ድክመት በመረዳት ሁኔታውን ለማርገብ ዘዴ ከመፈለግ ይልቅ በተቀጣጠለው እሳት ላይ የባሰውን ቤንዚን ማርከፍከፍ ነው የጀመሩት። ይህ ዐይነቱ በብስለትና በምሁራዊ ዕውቀት የማይመራ ፖለቲካ የሚሉት ፈሊጥ ቀስ በቀስ የደርግን አገዛዝ ´ከሰረሰረ በኋላ አገርን ለመከፋፈልና ለማዳከም ለሚችሉ በጣም አደገኛ ኃይሎች ነው ሁኔታውን አመቻችቶ ጥሎ የሄደው።  የደርግንና የተቀረውን የሚሊተሪና የስለላ ኃይል የዕውቀት ደረጃ ስንመለከት ደግሞ አብዛኛዎቹ በአሜሪካን ጭንቅላትን በሚያደነዝዝ “የሚሊተሪ ሳይንስ” ብለው በሚጠሩት የሰለጠኑ ናቸው። የቢሮክራሲውና የቴክኖክራሲውም አሰለጣጠን አገርን በተሟላ መንገድ ላይ እንዲገነባ በሚያደርግ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ ባለመሆኑ በቀላሉ ለአሜሪካኖች የሚያጎበድድና አገርንም የሚሸጥ ነበር። በሌላ ወገን ግን ብሄራዊ ነፃነታቸውን ያስከበሩና ጠንካራ ኢኮኖሚን በመገንባት ህዝባቸውን ከድህነት በማላቀቅ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ የሁኑ አገሮችን የመንግስታት አወቃቀር ስንመለከት አንዳቸውም መንግስታት ውጭ ሰልጠነውና የአሜሪካንን ርዕዮተ-ዓለምን በሚያራምዱና አገራቸውን በሚያደኸዩ አጎብዳጅ ኃይሎች አልተሰገሰጉም። እንደነዚህ ዐይነት ኃይሎች ካሉም በፍጥነት ነው እርምጃ የሚወሰድባቸው። ወደ አገራችን ስንመጣ ግን ለአሜሪካን የስለላ ድርጅት መስራትና አገርን ማፈራረስ እንደትልቅ ነገር ነው የሚታየው። እንደዚህ ዐይነቱም ሰው  ነው በጣም  የሚከበረው። ይህም የሚያረጋግጠው የአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኤሊት ጭንቅላትና የአንዳንድ የታወቁ ሰዎች ተከታዮቻቸው ጭንቅላት የቱን ያህል ጨቅላ እንደሆነ ነው።

 

ህወሃት ወይም ወያኔ የሚባለው አገዛዝ በአሜሪካንና በእንግሊዝ ኢምፔሪያሊስት ኃይሎችና በሰለላ ድርጅቶቻቸው ተደግፎና ተረድቶ ስልጣንን ሲጨብጥ ሆን ብሎ የጀመረው ስራ አገርን በፍጥነት ማዳከምና ብሄራዊ ነፃነቷ እንዲደፈር ማድረግ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ የጎሳ ፌዴራሊዝም ብሎ የሚጠራውንና የሚያቆላብሰውን አገርን የሚሰነጣጥቅውንና  የህዝቡን ብሄራዊ ስሜት የሚያዳክመውን ነው ተግባራዊ ያደረገው። ከዚህም በላይ ይህ ዐይነቱ ሂደት ጠንካራ ህብረ-ብሄር እንዳይመሰረት የሚያደርግ አደገኛ አካሄድ ነው። ተፈጥሮአዊ ከሆነው የህብረ-ብሄር ምስረታ አንፃርም ስንመረምረው የኋሊት ጉዞ የሆነና የህብረ-ብሄርንና የተፈጥሮ ህግን የሚጥስ ኢ-ሳይንሳዊ አካሄድ ነው።  በመሰረቱ የጎሳ ፌዴራሊዝም  ለብሄረሰቦች ዕውነተኛ ነፃነትን ያጎናፀፈና የፈጠራ ኃይላቸው እንዲዳብር ያደረገ ሳይሆን ለራሱ ለወያኔ የከፋፍለህ ግዛው ፖሊስና በየአካባቢው የሚገኙ የጥሬ-ሀብቶችን እንዲበዘብዝ የሚያመቹ ናቸው። ህወሃት ወይም ወያኔ በዓለም ኮሙኒቲውና ተላላኪዎቻቸው በሆኑት፣ በዓለም የገንዘብ ድርጅትና(IMF) በዓለም ባንክ(World
https://amharic-zehabesha.com/archives/187409
አገርና ነፃነት አደጋ ላይ ሲወድቁ ፋኖን የማይደግፍ ከነፃነት ባርነትን የመረጠ ባንዳ ተብሎ በተከታታይ ትውልድ ሲረገምና ሲኮነን ይኖራል!
በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com

እንኳን ኢትዮጵያውያን ዓለም እንደሚያውቀው የአምስት ሺ ዘመኑ የኢትዮጵያ ታሪክ የፋኖ የነፃነት ተጋድሎ ታሪክ ነው፡፡ የፋኖ የነፃነት ታሪክ የጀመረው ዛሬ ብቸኛ የሆነው የአፍሪካ የግዕዝ ፊደል በቅኝ ገዥዎች የላቲን ፊደል በመፋቅ ላይ ባለበት ዘመን ብቻ እንዳልሆነ የታወቀ ነው፡፡

ታሪክ እንደሚያስተምረው አውሮጳውያን አፍሪካን የተቆጣጠሩት በነፍጥ ሳይሆን ከአምስት ያልበለጡ “ሰባኪዎች” በየአገሩ እየላኩ ፊደላቸውን፣ የውሸት ሃይማኖትና ባህላቸውን እየጋቱ እንደነበር እንደ ቹኒያ አቼቤ ያሉ ጸሐፊዎች በታሪክ ቀመስ መጻሕፍቶቻቸው እንዳስተማሩ አንብቦ መረዳት ነው፡፡* የራሱ ያልሆነውን ፊደል፣ ሃይማኖትና ባህል የተጋተ ደግሞ ጋቺዎቹን ወይም ጌቶቹን ለመምሰል ቢጥርም አምላክ እነሱን አርጎ ስላልፈጠረውና እነሱን መሆን ስለማይችል ምርጫው እስከ ዳግም ምጣት የአካል ወይም የመንፈስ ባርያ መሆን ብቻ ነው፡፡

ቅኝ ገዥዎች ኢትዮጵያንም በተመሳሳይ መንገድ ቅኝ ተገዥ ለማድረግ ሰላዮችን ሰባኪ ወይም አማካሪ እያስመሰሉ በተለያዬ ጊዜ ልከው ነበር፡፡ የሩቁን ትተን የቅርቡን እንኳ ብናስታውስ ፋኖው አጤ ቴዎድሮስ በግዞት ያስቀመጣቸው ሰላዮች ለቅኝ ግዛት ዓለማ የተላኩ ነበሩ፡፡ ቅኝ ገዥዎች ኢትዮጵያን እንደ ሌሎች አገሮች በፊደል፣ በሃይማኖትም ሆነ በባህል ሰባኪዎች ቅኝ መግዛት ያልቻሉት ኢትዮጵያ ከእነሱ የበለጠ የረቀቀና ያማረ ፊደል፣ የቀን አቆጣጠር፣ ሃይማኖትና ባህል ስላላትና የዚህ መንፈሳዊ ሐብት ጠባቂቆች በተለይም ፋኖ የሆኑ ሼሆች፣ የቤተክርስትያን ሊቃውንት፣ ጳጳሳት፣ መነኩሳት፣ ቀሳውስትና ሊቃውንት ሕዝባቸውን በማንቃትና ለቅኝ ገዥ “ሰባኪዎች”ን ድባቅ የሚመታ መልስ በቃለም በጽሑፍም በመስጠት ነበር፡፡ ተቅርቦቹ ፋኖ ሊቃውንት አንዱን ብንጠቅስ አርበኛው ሊቀ ሊቃውንት መላከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ለእነዚህ ሳያምኑ ሰባኪ ለሆኑ ቅኝ ገዥዎች “ኮኮሐ ሃይማኖትና” መድሎተ አሚን” የሚባሉ ተነበው የማይጠገቡ መጻሕፍት ጽፈው ማሳፈር ብቻ ሳይሆን ጥልቅ ትምህርት እንደሰጧቸው ሥራቸው ምስክር ነው፡፡

ቅኝ ገዥዎች ካለነፍጥ ኢትዮጵያን በሰባኪዎች ቅኝ ለማድረግ የነበራቸው ተስፋ ሲሟጠጥ በነፍጥ ቅኝ ለማድረግ በተለያዬ ጊዜ ሞከሩ፡፡ በሌላ አነጋገር በመንፈሳዊ ኃይል ድባቅ ሲመቱ በአካላዊ ኃይል ኢትዮጵያ ለማንበርከክ ደጋግመው ሞክሩ፡፡የቅደም አያቶቻችን ታሪክ እንደሚመሰክረው መንፈሱ ፋኖ የሆነ ሰው አካሉም ፋኖ ነው፡፡ የመንፈስ ፋኖነት የሚገነባው የራስ የሆነ መንፈሳዊ ሐብት ሲኖር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፊደላት፣ ቋንቋዎች፣ የቀን አቆጣጠር ቀመር፣ ሃይማኖቶችና ባህሎች መንፈሳዊ ሐብት ናቸው፡፡ በምጣኔ ሐብት ሊበለጥግ ቢችልም የራሱ መንፈስ የሌለው ሕዝብ በፋኖነት ወይም በነፃነት ኮርቶ ይኖራል ተብሎ የማይታሰብ ነው፡፡ የደቡብ አፍሪካ ሕዝብ ዛሬ የአካል ነፃነት አለው የሚባል ነው! በመንፈስ ግን ዛሬም የሌሎችን ፊደል፣ የቀን አቆጣር፣ ቋንቋ፣ ባህልና አመጋገብ የሚጠቀም ነው፡፡ በእነዚህና በሌሎች መንፈሳዊ ሐብቶች የተወረረ ሕዝብ አንገቱን ቀና አርጎ በሙሉ ልብ የሚራመድበት ዘመን ይመጣል ማለት ዘበት ነው፡፡

እንኳን ኢትዮጵያ ውስጥ ከውጪ የተወለዱት የኢትዮጵያ ልጆች ሳይቀር አንገታቸውን እንደ ከንች ቀጥ አርገውና ደረታቸውን እንደ ጋሻ ነፍተው እምቢኝ እንዳለ ፋኖ አየተጎማለሉ የሚሄዱት ከኢትዮጵያ አርሶ አደር፣ የቤተክርስትያን ሊቃውንት፣ ሼሆች፣ ጳጳሳት፣ መነኮሳት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ነጋዴዎች፣ ወጣቶች፣ አዛውንት፣ ወይዛዝርት፣ ሌሎችም የሕብረተስብ ክፍሎች በወጡ ፋኖዎች ታጋድሎ በተጠበቀው የመንፈሳዊ ሐብት ነው፡፡ አለዚያማ የግዕዝ ፊደልን ተፍተህ የላቲን ፊደልን ስትጋት ፈልገህ ቅኝ ተገዥነንትን ወይም ባርነትን መረጥክ እንጅ ነፃነትህ ከምኑ ላይ ነው? የራስህን የቀን አቆጣጠር ትተህ በሌሎች መቁጠር ስትጀምር ሰተት ብለህ ለጌቶች በባርነት ሰገድክ እንጅ ክብርህ ከምኑ ላይ ነው? በተመሳሳይ መንገድ ባህልና እምነት ከቤትህ ሞልቶ ተርፎ ከሌሎች ጉርሻ ለማግኘት እንደ ውሻ ከተልከሰከስክ  እምነትና ማተብህ ከምኑ ላይ ነው?

የነፃነት ትርጉም የገባው እንደሚረዳው ከፊሉ የኢትዮጵያ ግዛትና ሕዝብ በእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ከወደቀ ከሰላሳ ዓመታት በላይ ሆነው፡፡ በእዚህ በእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ከወደቀው የኢትዮጵያ ክፍል ነፃነቷን ጠብቋት የኖረው ፋኖአዊ መንፈሳዊ ሐብቷ እየጠፋ ነው፡፡ የዘፈን ዳርዳርታው እስክስታ ነው እንደሚባለው ፊደሏን፣ ቋንቋዋን፣ ባህሏንና ሃይማኖቷን የቅኝ ገዥዎች መንፈሳዊ ሐብት እየተካ ለቅኝ ተገዥነት እያመቻቸን ነው፡፡ በሃይል መክረው ያልተሳካላቸው ቅኝ ገዥዎችና ወራሪዎች እንደ ሌሎች አፍሪካዊ አገሮች አንገታችንን አቀርቅረን የምንሄድ የመንፈሳዊ ሐብት ባርያዎች ሊያደርጉን እየተጉ ነው፡፡ በየትኛውም ዓለም ወደር የሌላቸው የስብእና፣ የሽምግልና፣ የቃል አክባሪነት፣ የእርቅና የይቅርታ ባህሎቻችን በእሬሳ ጎታች አውሬኣዊነት፣ በወስላታ ኤፍሬም ይሳቃዊ አስታራቂነት፣ በሚዘገንን ቃላ አባይነት፣ በቁማርተኛ እርቅ፣ በወለወልዳ ይቅር ባይነትና ጭልጥ ባለ የማያባራ ክህደት እየተተኩ ነው፡፡ መንፈሳዊ ሐብቱን ያጣ ሕዝብ ደሞ ለባርነት ተንበርካኪ እንደሆነ በባርነት በኖሩት በርካታ አገሮች የታዬ ነው፡፡ ስለዚህ ራሱም ሆነ ልጅ የልጆቹን በባርነት ቀንበር ለለማሳነቀ የሚፈልግ ሁሉ በፋኖ የነፃነት መንፈስ እንደገና የመጠመቂያ ጌዜው ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው፡፡

ከጥንት ጀምሮ ነፃነት አደጋ ውስጥ በገባበት ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚከፈለው ፋኖና ባንዳ ተብሎ በሁለት ብቻ ነው፡፡ ተመሐል ሆኖ ዝም ብሎ እንደ አሳማ ሲዝቅ ኖሮ ለመሞት የቆረጠ ሁሉ በተዘዋዋሪ ባርነትን የመረጠ ባንዳ ነው፡፡ ፋኖነት የነፃነት መንፈስ ስለሆነ እንኳን ተምድር እየኖሩ ተማርስ እየኖሩም የሚተገበር ቅዱስ ምግባር ነው፡፡ እያረሱ፣ ከበት እየጠበቁ፣ እየተማሩ፣ እያስተማሩ፣ እየነገዱ፣ ቤተክርስትያን እየቀደሱ፣ መስጊድ እየሰገዱ፣ መስሪያ ቤት እየሰሩ፣ ኩሽና ወጥ እየሰሩ፣ ውሀ እየቀዱ፣ ክክ እየከኩ፣ ኩበት እየለቀሙ፣ እየጰጰሱ፣ ሺህ እየሆኑ፤ እየቀሰሱ፣ እየደቆኑ፣ እየመነኮሱ ወዘተፈ ሁሉ ፋኖ መሆን የሚቻል ነው፡፡ ቅድመ አያቶቻችን ይኸንን ስለማድረጋቸው ትተውን ያለፉት ተዝቆ የማያልቅ አካላዊና መንፈሳዊ ሕብት ምስክር ነው፡፡ የደብረ ሊባኖስ ገዳም ፋኖ መነኮሳት መጽሐፍ መነኮሳት “ሰይጣንን መር ብለህ ቁንጮን ያዘው**” ብሎ ባዘዘው መሰረት መውዚር አንግተውና ዝናር ታጥቀው መር በማለት የሰይጣኑን ፋሽሽት ቁንጮ ይዘው እንዳስጎሩት ታሪክ ምስክር ነው፡፡ ቅድመ አያት አጥንትና ደሙን ገብሮ ያስረከበን የመንፈሳዊና ቁሳዊ ሐበት አለመጠበቅ በምድርም በሰማይም የሚያስጠይቅ ዕፀጽ ነው፡፡

የዛሬው ከአምስቱ ዘመን ሆነ ከዚያ በፊት ከነበረው ይከፋል! አሁን የደረሰብን የነፃነት አደጋ ከበፊቱ ሁሉ የከፋ መሆኑን በአይኗ ብብረቷ ያየነው ቢሆንም የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ሃይሌ ላሬቦም ደጋግመው ተናግረውታል፡፡ በቅርቡ ባደረጉት ቃለ ምልልስም ለዚሁ አጽንኦት ሰጥተውና ፋኖን እንደ መሲህ ቆጥረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፋኖን እንዲደገፍ ፋኖም አድማሱን ኣስፍቶ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ አቅፎ ይኸንን ከመቼውም ጊዜ የከፋ አደጋ እንዲያስወግድ ተማፅነዋል*፡፡

ከበፊቱም የክፋ ነፃነት አደጋ ላይ ሲሆን ደሞ ተሁሉም ኢትዮጵያዊ ፋኖነት ይጠበቃል፡፡ ነፃነት አደጋ ላይ ሲወድቅና ሰይጣን ሲወር እንደ አምስቱ ዘመን እንኳን የሰው ልጅ ወንዙ፣ ጋራው፣ ሜዳው፣ ሸለቆው፣ ሸንተረሩ፣ የቀንድ ከብቱና የየጋማ ከብቱም ፋኖ ይሆናል፡፡ ሬዲዮኑና ተሌቪዥኑ፣ ጋራውና ሽንተረሩ ሁሉ የነፃነት አውታር የሆኑትን ቀረርቶና ፉከራ ሌተ ተቀን ሳይታክት ያስተጋባል፡፡ ከመቼው ጊዜ የበለጠ አገርና ነፃነት አደጋ ላይ ሲወድቁ ፋኖን የሚቃወም ወይም የማይደግፍ ከነፃነት ባርነትን የመረጠ ባንዳ ተብሎ በምድር በተከታታይ ትውልድ በሰማይም በመለኮት ሲረገምና ሲኮነን እስከ ዘላለም ይኖራል፡፡

ፋኖነት የእምነት ጥንካሬ፣ የቃል ኪዳን ፅናት፣ የነፃነት መሰረት፣ የፍትህ ምንጭና የመንፈስ ልእልና ቁንጮ ነው፡፡ እግዚአብሔር የኢትዮጵያንን ሕዝብ ከፋኖነት መንፍሰ ከመራቅ ያድነው፡፡ አመሰግናለሁ፡፡

ዋቢ፡-

* Books of Chinua Achebe:  Things Fall Apart, No longer at Ease, There Was A Country etc

** ማር ይስሃቅ ገፅ 106፡ እግዚአብሔር ሳንፈራ ሳንበርድ ጸላታችንን (ሰይጣንን ማለቱ ነው) እንገጥመው ዘንድ ያዝዛልና ሳይቀድምህ ቅደመው...ትወጋው ዘንድ መር ብለህ ቁንጮውን ያዘው”

***ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትሩ እንደሚሉት አዲስ “የጋራ ትርክት” አያስፈልጋትም–የታሪክ ምሁሩ ፕሮፈሰር ሃይሌ ላሬቦ - (amharic-zehabesha.com)

 

ህዳር ሁለት ሺ አስራ ስድስት ዓ.ም.

 

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/187406

Saturday, November 25, 2023

https://youtu.be/0olj5fyhmE8?si=pkASda1r5IyZ2bWJ

 

ቀጥታ ከግንባር | “የጀመርነውን ትግል አራት ኪሎ ሳንገባ አናቆምም”  "የሐይማኖት አባቶች እናከብራችኋለን ግን ለሽምግልና አትመጡብን"
https://amharic-zehabesha.com/archives/187396
ያህያ ሌባ የበዛበት ዘመን
ኅዳር 14 ቀን 2016 ዓ/ም ቀሲስ አስተርአየ nigatuasteraye@gmail.com

ይህ ዘመን አህያ ሰርቆ በጫካ ውስጥ አስሮ ከደበቀ በኋላ፡ ያህያዋን ባለቤት አፈላለጊ መስሎ ቀርቦ በማደናበር ላይ የነበረውን ሌባ የሚመስሉ ብዙ ሌቦች፡ ጥንታዊቷን ኦርቶዶካሳዊት ቤተ ክርስቲያንንና ኢትዮጵያን የከበቡበት ዘምን ነው፡፡

ጦማሩን ለምታነቡም ሆነ በቭዲዮ የተቀረጸውን ድምጽ ለምታዳምጡ ወገኖች ስለ ትግስታችሁ እያመሰገንኩ፡ ለሚወስድባችሁም ጊዜ ይቅርታ እየጠየኩ ወደ ዝርዝር ሐተታዬ ከመሻገሬ በፊት የሀሳብ ጠላፊና ነጣቂ አንደበተኛ የበዛበት ዘምን ስለሆነ የማቀርበውን ሀሳብ ከነጣቂወችና ጠላፊወች ለመከላከል ይህችን ማሳሰቢያ ለማስቀደም ተገደድኩ፡፡

ማሳሰቢያ

ያሳደገችኝ ያጠመቀችኝና ያስተማረችኝ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንና ኢትዮጵያ አሁን ያሉበትን አስከፊና አስቃቂ ሁኔታ ለመግለጽ ሳስብ ቅዱስ ጳውሎስ “እኔ የምጽፈው ስለበደለና ስለተበደለ ሰው አይደለም በግዚአብሔርና በሰው ፊት ራሳችሁን እንድታዩ”(2ቆር 7፡12)” ብሎ የተናገረው ማሳሰቢያ ትዝ አለኝ፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ለመናገር የፈለኩት ደጋግሜ ስለማነሳቸው ስለ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋና ስለ ዳንኤል ክብረት ማንነት ለመናገር ሳይሆን፡ የተናገሩት ሕዝብንም እኔንም ያወናበደ መሆኑን ለማሳየት ብቻ ነው፡፡

ይሁን እንጅ ድርጊታቸውን ስቃወም አድራጊወችን መንካቴ አይቀርምና በጥላቻ በግል ቂምና ዘመኑንን ባረከሰው በሴራ ፖለቲካ ተገፋፍቸ አለመሆኑን ለማሳየት እንጅ፡ የነሱን ስም ለማጥፋት ለመክሰስና ለመውቀስ አይደለም፡፡

እኔ “አይጧም አትለፍ፡ ምጣዱም አይሰበር” የሚለውን ስለምከተል፡፡“ለምጣዱ ሲባል አይጧ ትለፍ” እያለ አይጦችን የሚያራባውን አዘናጊና የሸፍጥ መርሆ የሚከተል የዘመኑ ፖለቲከኛ አይደለሁም፡፡

“አይጡን ትቶ ዳዋውን፡ አህያውን ፈርቶ ዳውላውን” እንዲሉ መደብደብ የሚገባቸውን አይጦችን እያራባ ወደ ህዝብ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚልክ፡ ተሸካሚ ጳጵሳትን ትቶ ህዝበ ክርስቲያኑን የሚደበድብ ፖለቲካ የተከሰተበት ዘመን ነው፡፡

ይህ ዘመን ስለተደባዳቢ በደለኛ መናገር ስህተት ነውር፤ ስለሚደበደበው ህዝብ መደብደቡን ገልጾና ተቃውሞ መናገርም ነውር እየሆነና፡ በሁሉም ግልጽ ሆኖ ስለሚታይና መደበቅ ስለማይችሉ ስለድብደባው ብቻ መናገር ባህል የሆነበት ዘመን ነው፡፡

ይህን ባህል የፈጠሩ ፖለቲከኞች እነሱ በሰሩት ስህተትና በደል ህዝቡን እያስደበደቡት እያስጎዱት ነው፡፡ በበደላቸው በመዋሸታቸውና በመቅጠፋቸው አፍረው መጸጸት ንስሀ መግባት ሲገባቸው በፈጠሩት ርኩስ ባህል ራሳቸውን ደብቀው በተግባር የደጸሙትን በደል አሉባልታ እንዲሆን ባሉባልታነት እየሸፈኑት ናቸው፡፡

በክርስትና እምነት ራሱን የሚደብቅና ደብቆ የሚናገር “ዘእኩይ ምግባሩ ይጸልእ ብርሃነ ወኢይመጽእ ኀበ ብርሃን ከመ ኢይትከሰቶ ምግባሩ”(3፡20_21) ብሎ ክርስቶስ እንደተናገርው ደብዳቢው ቀጣፊው ውሸታሙ እራሱን እይገልጽም በሌላ እንዲገለጥም አይፈልግም፡፡

አዳምና ሄዋን ራሳቸው ፍሬዋን ቀጥፈው ከበሉ በኋል እንደገና የበሏትን የራሷን የበለሷን ቅጠል ቀጥፈው ራሳቸውን እንደደበቁባት፡ የብልጽግና ቡድንም ዳንኤል ክብረትን በመሳሰሉ ቀጣፊወች ራሳቸውን ደብቀው የሚፈጽሙት በደልና ኃጢአት እንዳይገለጥባቸው እንደገና በሌላ ቅጥፈት ራሳቸውን እየደበቁ አማራውን፡ አማረኛ ተናጋሪውንና ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን እየደበደቡ ናቸው፡፡

ራሳቸው ዶክተር ዳኛቸው“አንድ የስነ መለኮትና የፍልስፍና ተማሪ “ሄዋን አሳሳተችኝ አትበል ሄዋን አንተነህ” አለ ብለው ከሙሉ ጥራዙ ነጥቀው የጠቀሱት የስነ መለኮትና የፍልፍስና ተማሪ ይህን ከላይ የገለጽኩትን ለመግለጽ የሞከረበት ዓውድ ይመስለኛል፡፡

የተከሰተውን በደልና ኃጢአት ከሰሪው አካል እየነጠሉ የችግሩን ፈጣሪ እየደበቁ መናገር፡ የሰሪውን ሕልውና መካድ ሲሆን ተደብቆ የሚሰራውን ኃጢአት ሳያፍር እንዲቀጥልበት እንዳይጸጸትና ንስሐ እንዳይገባ ማድረግ ነው፡፡

ይህ አካሄድ ሊቃውንት መምህሮቼ የቀኖናችን መስራቾች ሰለስቱ ምዕት “እመቦ ዘይትናገር ውስተ ቤተ ክርስቲያን ነገረ ከንቱ ስላቅ እስመ ጌጋዩ ይከውን ላዕለ ካህን ዘይትለአክ ወአኮ ዘይኤብስ ባሕቱ ዘይትኬነን አላ ዘሂ ይትፌሳህ በኃጢአቱ ወበአሐቲ ኩነኔ ይትኬነኑ”( ሃ አ ም 22፡ቁ4) ብለው የተናገሩትን መሠረት በማድረግ ባንድምታ ጉባኤያቸው ካስተማሩኝ ጋራ የሚቃረን ይሆናል፡፡

ይህም ማለት “በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ዋዛ ፈዛዛ ቀልድና ስላቅ መናገር በደል ነው፡፡ የሚያስከትለው ፍዳ የሚደርሰው በደሉን በሚናገር ሰው ላይ ብቻ አይወሰንም ከተናጋሪው ይልቅ በካህኑ ላይ ይከብዳል”

ባብነቱ ትምህርትም ሆነ ባስኳለው ትምህርት የመደበቅ ግዴታና ጥንቃቄ እንዳደርግ የተማርኩት ለንስሐ በኑዛዜ በግል የተነገረኝን ብቻ ነው፡፡ በህዝብ ላይ ተፈጽሞ በግልጽ የሚታየውን በደል ህዝብ ሊናገረው ያልደፈረውንና ባስመሳዮች ተድበስብሶ የሚነገረውን ገልጦና አብራርቶ አለመናገር ሐላፊነቱ የኔ ብቻ ሳይሆን በቅስና በጳጵስናና በፍልስፍና ሙያ በህዝብ ፊት የቆሙትን ዶክተር ዳኛቸው የመሳሰሉትን ሁሉ የሚመለከት ነው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ “እፈቱ እፍልስ እም ዓለም. . . . ወባህቱ ርቱዕ ይደሉ ሊተ ከመ አሀሉ በሕየወተ ሥጋዬ በእንቲአክሙ“ (ፊል 1፡20_23)”፡፡ ብሎ እንደተናገርው ራሳቸውን ያላስቀደሙ አንዳንድ አስተዋዮች ለሰው ክብር ለሀገር ደህንነት ያቀዱትን የተቀደሰውን ተግባር የሚቃወሙ የሰይጣን ሠራዊቶች የጀመሩትን ከግብ ሳያደርሱ እንዳያጠፏቸው ጀማሪወች ራሳቸውን ሳይገልጹ የብዕእር ስም ቢጠቀሙ ኃጢአት አይደለም፡፡

ያም ሆነ ይህ ዶክተር ዳኛቸው ዳንኤልን የነቀፍነውን ነቅፈው ዳንኤልን ሸፋፍነው ማቅረባቸው “አይጡን ትቶ ዳዋውን አህያውን ፈርቶ ዳውላውን” የሚባለውን ፈጸሙ፡፡

ሐምሌ 16 ቀን 2011 ዓ/ም አህያየን የሰረቃት ሌባ፤ ራሱ ደብቆ አፈላላጊየ ሲሆን አህያየን እንዴት ላገኛት እችላለሁ? ”በሚል ርዕስ የጻፍኳትን ጦማር አስታወሱኝ፡፡ ማሳሰቢያን እዚህ ላይ አቁሜ ወደ ዋናው ነገሬ እሻገራለሁ፡፡

አህያ ሰርቆ በጫካ ውስጥ የሰረቃትን አህያ ደብቆ፡ ጠፍታው በመፈለግ ላይ ያለውን ባለቤቷን የሚያፈላልግ ያህያ ሌባ ታሪክ፡ በዚህ ዘመን ያለነውን የመንፈሳውያንና የፈላስፎችን የሁላችንንም ተግባር እምነትና ምንነት የሚገልጽ መሰለኝ፡፡

ከዚህ በታች የማቀርበው የነዶከተር ዳኛቸውን አካሄድ ይገልጽልኛል ብየ ያሰብኩት የተሰረቀችው ያአህያዋ ታሪክ ነው፡፡

አንድ ባላገር አህያው ጠፋቸው፡፡ ባካባቢው ያህያ አፈላለግ ልማድ “አህያ ያየህ ና ወዲህ በለኝ” እያለ ድምጽ በማሰማት ፍልጋውን ቀጠለ፡፡ ያህያዋን የእግር ምልክት (ዱካዋን) አገኘ። ዱካዋን ተክትሎ ሲሄድ አህያውን የሰረቀ ሌባ ሲመሽ ፈቶ ወደ ቤቱ ይዞ ለመሄድ አስሮ ከሚያቆይበት ጫካ ደረሰ። ሌባው ሲመሽ ፈቶ ወደ ቤቱ እስኪወስዳት ድረስ ጅብ እንዳይበላት ካካባቢው ሳይርቅ ይጠብቃል።

ያህያዋ ባለቤት በእግሯ ምልክት ማልትም በዱካዋ እየተመራ ያህያው ሌባ አህያዋን አስሮ ከጅብ ከሚጠብቅበት ጫካ ደረሰ፡፡ “ያህያዬ የእግር ምልክት (ዱካ) እየመራኝ ከዚህ ደርሻለሁ ፡፡ምናልባት የኔ አህያ በዚህ አካባቢ አይተሀት ከሆነ ልትነግረኝ ትችላለህ? ወንድሜ“ ብሎ አስሮ የደበቃትን ራሱን ያህያውን ሌባው ጠየቀው።

ሌባውም መለሰና “ቀኑን ሙሉ ሳር ሳጭድ ከብቶችንም ሳሰማራ ካካባቢው አልተለየሁም፤ አህያ ግን አላየሁም፡፡ ይህ የምትከተለው ዱካ ያህያ አይደለም፡፡ አንድ ሰው በቅሎ እየነዳ በዚህ አልፏል። የምትከተለው ፋና የበቅሎዋ እንጅ የአህያዋ አደለም። ይልቅስ እየመሸ ነውና ጅብ እንዳይሻማህ በጊዜ ወደ ሌላ ቦታ እንድትፈልጋት እመክርሀለሁ” አለው።

በመፈለግ ላይ ያለው ያህያዋ ጌታም ሌባውን ጠርጥሮ ቆሞ በመተከዝ ላይ ሳለ፡ አህያው ጠፍታው በመፈለግ ላይ መሆኑን ያወቀ አቋርጦ በመሄድ ላይ የነበረ የጎረቤት ሰው “አህያህን አገኛሀት?” ብሎ በምፈለግ ላይ ያለውን የአህያዋን ጌታ ጠየቀው። ያህያዋ ጌታም “አህያየን ሰርቆ የደበቃት ያህያየ ሌባ አፈላላጊየ ሆኖ ሳለ እንዴት አህያየን ላገኛት እችላለሁ? ብሎ መለሰለት።

ሌባው መሽቶ በጀብ ከመነጠቁ በፊት አህያዋን ካሰረበት ጫካ ፈቶ ወደ ቤቱ ይዞ ለመሄድ ቢፈልግም፡ ያህያዋ ባለቤት አህያው ከዚያ ቦታ እንዳልራቀች ተጠራጥሮ ከቆመበት አልሄደም፡፡ ሌባውም ባለቤቷ ትቶለት እንደማይሄድ ተረዳና ፊቱን አዙሮ ቦታውን ለቆ መሄድ ሲጀምር፡ ያህያዋ ባለቤት በተለመደው ያፈላላግ ዘዴ “አህያየን ተሰርቃ ከጫካ ታስራ አግኝቻታለሁ፡፡ በጅብ ተከብቤአለሁና ድረሱልኝ” ብሎ የጥሪ ድምጽ ላካባቢው ሲያሰማ ሌባው ጥሎት ፈረጠጠ፡፡ ባለአህያው አህያውን ሰርቆ ደብቆ አፈላላጊ ሆኖ ከቀረበው ሌባና ከጅብ አተረፋት፡፡

ዘመኑ ጠላፊ ነጣቂ አንደበተኛ የበዛበት ባይሆን ከዚህ በላይ ያቀረብኩት ባህያዋ ሌባ ተካቶ ስለቀረበ ሌላ ሐተታ ባላስፈለገ በበቃ ነበር፡

፡ግን የቀሰቀሰኝ ነገር በፈላስፋው በዶክተር ዳኛቸው ተጠንስሶና ተደፍዶ የቀረበ ስለሆነ በተማርኩት አንድምታ መበጥበጥ ማጥለልና ገፈታውን መለየት አለብኝና ወደ መተርጎሙ እንድገባ ተገደድኩ፡፡

መተርጉም

መተርጉም ቀደም ብሎ የተከሰተውን ተመሳሳይ ነባራዊ ክስተት መነሻ በማድረግ አዲሱን ጥሬ ክስተት በነባራዊው ክስተት መሰለቅ መፍጨትና አዲስ የሚወለደውን ክስተት መጠቆም ማሳየት መግለጽ ማለት ነው፡፡ ከነባራዊውና ካዲሱ ክስተት ድምር የሚገኘው የትርጉም ነጸብራቅ መላምት ይባላል፡፡ እምኀበ አልቦ የመጣ ፈጠራ ስላይደለ ጥንቆላም ትንቢትም አይደለም፡፡ ከነበረውና ካለው ስብቀት የሚወለድ መጻኢውን የሚጠቁም ሐሳብ ነው፡፡

በዚህ ዓለም ስንኖር በኑሯችን የሚገጥሙንን የምንተረጎምባቸው መንገዶች ብዙ ናቸው፡፡ ከብዙወቹ መተርጎሚያ መንገዶች ጥቂቶቹ በባህላችንና በሃማኖታችንና በጠቅላላው ኢትዮጵያውነታችን ውስጥ የተካተቱ ናቸው፡፡

እኔ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መተርጉማን ተማሪ ነኝ፡፡ ኢትዮጵያውያን መተርጉማን ክስተቶችን የሚተረጉሙ ክርስቶስ “የምድሩን ያካባቢህን ሳትረዳ የሰማዩን አውቃለሁ የምትል አንተ ግብዝ”(ማቴ 16፡2) ብሎ የተናገረውን መመሪያ በማድረግ ነው፡፡ ክርስቶስ እንዳለው አስቀድመን በዙሪያችን ባካባቢያችን ያሉትን ክስተቶች መረዳት ነው፡፡ በዙሪያችን ያሉትን ነባራዉያን ክስተቶች ተረድተን አዲስ ማለትም ጥሬና ግርድፍ ክስተቶችን በነባራዊው ክስተት መፍጨትና መሰለቅ ማለት ነው፡፡

በዚህ አቀራረቤ መፍጫው በሌባ ተሰርቃ በጫካ ታስራ በሌባው የተደበቀችው አህያ፡ ደብቆ አስሮ ባለቤቱ ሲጠይቀው ወደ ሌላ ቦታ ሄደህ ፈልግ ያለው ሌባና ባለቤቷ ያህያየ ሌባ አፈላላጊየ ሲሆን እንዴት አህያየን ላገኛት እችላለሁ የሚለው ነባራዊው ክስተት ነው፡፡

የሚፈጨው አንድ አፍታ በሚባለው መገናኛ እስጢፋኖስ አበራ እና ዙሩባሌል ዓለማየሁ በሚባሉት ጠያቂነት በተለያዩ ወቅቶች ቀርበው ዶክተር ዳኛቸው፦

“በየአድባራቱ እየዞረ የኢትዮጵያን ታርክ ቅርስ እየመረመረ ይህን ሁሉ የጻፈውን ሰው ኢትዮጵያን እኔ ነኝ የምወዳት አንተ አትወዳትም አንተ ትጠላትለህ ብየ ለምንድነው በእንደዚህ ያለ ግምት የምንቀሳቀሰው?

ብለው የተናገሩት ነው፡፡

የዶክተር ዳኛቸው ጥራጥሬ ሐሳቦች

Nichel “ሐሰት ማለት በሬ ወለደ ማለት አይደለም፡፡ፊት ለፊት የሚታየውን አላየሁም ማለት ነው፡፡ መንግሥት ስራውን እየሠራ ብቻ አይደለም፡፡ ዓቢይ ለሲኖዶሱ መከፈል ተባባሪ ነው ይባላሉ፡፡ ጠ/ምንስቴሩ ሲኖዶሱ በሶስት ተከፍሎ አያገባኝም፡ ይላሉ፡፡

ባንድ ወቅት ህግ ሲገረሰስ እኔን አይመለከተኝም በሌላ ወቅት በመንግሥቴ ስር ያላችሁ ህግ አስከባሪወች እጃችሁን እንዳታሰገቡ ይሉና እንደገና በሌላ ወቅት የፖለቲካ አዝማሚያ እያዩ አፋጣኝ ርምጃ ማለት ምን ማለት ነው? መንግሥት ወደ ቀልቡ በመመለስ ይቅርታ መጠየቅ አለበት፡፡

አቶ ሽመልስ ሸገርን ሲመሠርት ቤታቸውን አፍርሶባቸውል፡፡ በፈረሰባቸው ዜጎች መካከልና በሽመልስ መካከል ምንስቴሩ ሽማግሌ መሆን አለባቸው፡፡ ይህ

ሁሉ ሲፈጸም ጠ/ ምኒስቴሩ ምንም አልተናገሩም ለጥፋቱ ተባባሪ ናቸው፡፡ እየተባለ ነው፡፡ ወሰን የደረሰውን ግፍ ለኮንግረስ በሰንጠረዥ አቅርበዋለች፡፡ በየአድባራቱ እየዞረ የኢትዮጵያን ታርክ ቅርስ እየመረመረ ይህን ሁሉ የጻፈውን ሰው ኢትዮጵያን እኔ ነኝ የምወዳት አንተ አትወዳትም አንተ ትጠላትለህ ብየ ለምንድነው በእንደዚህ ያለ ግምት የምንቀሳቀሰው? ባሜሪካና በጀርመን ያሉ ያልተማሩ ሚኒሽያወች ናቸው፡፡

እንዲያውም ሕዋት ይሻላል የሞትንም እኛ ያለንም እኛ እያለ ነው፡፡ ደርግ ፓትርያርኩን ገደለ፡፡ ወያኔ አባረረ፡፡ ይህ ደግሞ ሲኖዶሱን ለ3ት ከፍሎ በቁም ቀበረ፡፡ ለፖለቲክ ብለህ ሕግ ከሻርክ ወደክ፡፡

የወልቃይት ነገር በhouse of federation ተመክሮበት በዚያው በፌዴሬሽኑን መነገር ሲገባ ራሱ ጠቅላዩ ከፌዴሬሽኑ ነጥቆ መናገሩ፡ የቀይ ባህር ጉዳይም ተመክሮበት በውጭ ጉዳይ ምንስቴር በኩል መገለጽ ሲገባው ተሽቀዳድሞ መናገሩ በነጣቂነት ባፋኝነት ካገርበጃችን ወደአገርበጄነት መቀልበስ፡ ኮለኔል ደመቀ ከራሱ በላይ አገር ወዳድነቱንና አሳይቷል፡፡

የዲሞክራሲን መኖር የሚገለጹት liberty equality legality ሲንጸባርቁ ነው፡

፡እነዚህ ሶስቱ ከሌሉ የዲሞክራሲን አለመኖር ይገልጻሉ፡፡ በአማራ ክልል በመፋለም ላይ ያለው ፋኖ እንደ ሁለተኛ ኃይል ሆኖ ተከስቷል፡፡

ወሰን በህዝብ ላይ የደረሰው ግፍ ለኮንግረስ በሰንጠረዥ አቅርበዋለች፡፡ ባሜሪካና በጀርመን ያሉ ያልተማሩ ናቸው፡፡ ጠበንጃ እየተነጋገረ ነውና ሁሉም ዝም ይበል”

ከዚህ በላይ የሰፈረው የዶክተር ዳኛቸው ንግግር

“በየአድባራቱ እየዞረ የኢትዮጵያን ታርክ ቅርስ እየመረመረ ይህን ሁሉ የጻፈውን ሰው ኢትዮጵያን እኔ ነኝ የምወዳት አንተ አትወዳትም አንተ ትጠላትለህ ብየ ለምንድነው በእንደዚህ ያለ ግምት የምንቀሳቀሰው?” ከሚለው ንግግራቸው በቀር፡ አግደምድመው አቀረቡት እንጅ እውነት ነው፡፡

ታዲያ አግደምደመውም ቢሆን የተናገሩት ሁሉ ጥፋት በዳንኤል ክብረት ምክር እየተመሩ ጠ/ምንስቴሩ የፈጸሙት ከሆነ የዳንኤል ክብረት መወቀስና መነቀፍ ለምን ዶክተር ዳኛቸውን አመማቸው?

ራሳቸው “አሁን ጠበንጃ እየተናገረ ነው ሰው ዝም ይበል” እንዳሉት፦ አሁን በፋኖ የተነሳውን ጠበንጅ በዝምታ መቀበል ያለባቸው በዳንኤል ምክር የሚመራው ጠ/ም ዐቢይና ፋኖን ጃዊሳ ብሎ የዘለፈው ዳንኤል ክብረት እንጅ የፋኖን ሀሳብ ደግፈው ለኮንግረስ በደሉን ያቀረቡትን ወሰንንና፡ ክወሰን ሀሳብ ጋራ የሚናበብ ሀሳብ ያለንን የሚመለከተን አይመስለኝም፡፡

ባንድ በኩል የተናገሩትን ለምን በሌላ በኩል ራሳቸው በተዘበራረቀ ንግግራቸው ያፈርሱታል? “አንድ የስነ መለኮትና የፍልስፍና ተማሪ ሄዋን አሳሳተችኝ አትበል ሄዋን አንተነህ” ብሎ ተናገረ የሚለውን የጠቀሱት ምናልበት ዓቢይ የሚከሰስበት መልካም ጊዜ ቢከሰት በዳንኤል ምክር ነው በደሉን የፈጸምኩት ብሎ እንዳያመልጥና ለዳንኤል የሚያመልጥበትን ዘዴ በጠማማ መንገድ ለመጥቆም እንጅ ተሰውሯቸው አይመስለኝም፡፡

ዶክተር ዳኛቸው በየጊዜው የተናገሯቸውን በተለያዩ የፍልስፍና ዘርፎች የሰለጠኑ ባለሞያወች ቢፈተሿቸው ዳንኤል ክብረት ለኢትዮጵያ ያለውን ፍቅር ተርጉመው ሊያሳዩን የሞከሩበትን ፈሊጥ (fallacy) የተፋለሰ መሆኑን እኔ

ከማሳየው የበለጠ አድርገው እንዲሚያቀርቡት እርግጠኛ ነኝ፡

ዶክተር ዳኛቸው ከእስጢፋኖስ አበራ እና ከዙሩባሌል ዓለማየሁ ጋራ የተናገሯቸው ጥራጥሬ ሀሳቦች በሀሳብ መፍጫ ዘርፎች መፈጨት ያለባቸው ጥሬ ሐሳቦች ሲሆኑ ለባለሙያወች ትቼ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋራ አያይዘው ስለ ዳንኤል ክብረት በተናገሩት ላይ ብቻ አተኩራለሁ፡፡

ዶክተር ዳኛቸው ስለ ዳንኤል የተናገሩት

በግድምድም ቢሆንም በገለጿቸው እውነቶች “በየአድባራቱ እየዞረ የኢትዮጵያን ታርክ ቅርስ እየመረመረ ይህን ሁሉ የጻፈውን ሰው ኢትዮጵያን እኔ ነኝ የምወዳት አንተ አትወዳትም አንተ ትጠላትለህ ብየ ለምንድነው በእንደዚህ ያለ ግምት የምንቀሳቀሰው?” ብለው ስለዳንኤል ተመራማሪነትና አገር ወዳድነት ተናግረዋል፡፡

ራሳቸው መልሱን በማጣት ተቸግረው በመፈልግ ላይ እንደሆኑና ሌላ መልስ ሰጭ አካል ፈላጊና አፈፈላጊ የፈለጉት መልሱ ጠፍቷቸው አይመስለኝም፡፡

አንድ ጸሐፊ “philistine በብዙ ተብለጭላጭ እውነቶች አንዲትን ሐሰት ሸፋፍኖ በማሾለክ በኑሮ ውጣውረድ በተጠመደው ብዙ ሕዝብ ጭንቅላት ላይ ያሰርጻታል” እንዳለው፦ ዶክተር ዳኛቸው አግደምድመው ባቀረቡት ሐሳብ

የዳንኤልን ሸፍጥ ሸፍነው ተመራማሪነቱንና ለኢትዮጵያ ያለውን ፍቅር በጭንቅላታች ሊያሰርጹብን የፈለጉ ይመስለኛል፡፡

ዲቁናውን፡ ሙሐዘጥበብነቱን፡ ተመራማሪነቱን ጸሐፊነቱንና ለኢትዮጵያ ያለው ፍቅሩን አሁን በሚሰራው ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በነበረበት በኢሀደግ ዘመን በተናገራቸውና በሰራቸው ስመዝናቸው የዶክተር ዳኛቸው ለዳንኤል የሚሰጡት ምስክርነት ለየአይጥ ምስክር ሆና የቀረበችውን የድንቢጥን ምስክርነት የሚገልጥ ነው፡፡

ምንድነው ዲቁና? ተመራማሪነትስ ምንድነው? ሙሐዘጥበብነትስ ምንድነው? ለዳንኤል የተሰጡትን ሶስቱንም የግር ቅጽሎች መዳሰስ ሊኖርብን ነው፡፡

ዲቁና ምንድነው? በቤተ ክርስቲያናች ሕጻናት የመጾር መስቀል ይዘው ሳይገባቸው ሳይረዱ ነጽር እያሉ በቄሱ ላይ “ተንሥኡ” እያሉ በህዝቡ የሚጮሁት ብቻ ይመስላል፡፡ ግን ይህ ብቻ አይደለም፡፡ የእስጢፋኖስን የዲቁና ተግባር ተምረው ሙሉውን ሕዝባዊ የዲቁና አገልግሎት አካተው የያዙ መሆን ይገባቸው ነበር፡፡ መጮህ ያልኩት ዲያቆናት የሚያሰሙትን ቃል ማቃለሌ ሳይሆን በቀኖናችን የተገልጸውን የዲቁናውን ሕዝባዊ ተልእኮ በተግባር ለማዋል ባለመብቃታቸው ነው፡፡

ይህም የሕጻንነት ዲቁና ባንድ ወቅት የተፈጠረ ክስተት ቋሚ ባህል በመሆኑ እንጅ የሕጻናቱ ስሕተት አይደለም፡፡

ታላቁ ሰማእት አባታችን አቡኑ ቴወፍሎስ የዲቁናን ሙሉ አገልግሎት በሰበካ ጉባኤው ቃለ ዓዋዲ መሠረት ባካባቢው ህዝበ ክርስቲያን በተመረጡ በተማሩ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተና መጠበቅና አስፈላጊም ሲሆን ተላልፈው በሚሞቱ ክርስቲያኖች እንዲተካ ሊያስተካክሉት ሞክረው እንደነበረ ደጋጋሜ ገልጨዋለሁ፡፡፡

ከዳንኤል ክብረት ይጠበቅ የነበረው በሰማእቱ ቅዱስ አባታችን በፓትርያርክ ቴወፍሎስ የታወጀውን የሊቀ ዲያቆን ቅዱስ እስጢፋኖስንን ተልዕኮ መፈጸም ነበር፡፡ ነገር ግን ባልተጠበቀበት በተቃራኒ መንገድ በመሄድ በሕጻናቱ የሚካሄደውን እንኳ ተንስኡ ብሎ አያውቅም፡፡ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ በህዝብ ላይ ጥፋት እየፈጸመ ያለውን ብልጽግ ናን አልገሰጸም፡፡ የሚጠራበት የሙሐዘጥበብነት ትርጉም ይዞ አልተገኘም፡፡ የዳንኤል ሙሐዘጥበብነት የሚያንጸባርቀው የጥንቱን philistine ባህርይንና ጠባይ ነው፡፡ በፍልስፍናው ዓውድ philistine ማለት “የገብያ ግርግር ለቀጣፊ በጀው እንዲሉ” በህብረተ ሰብ መካከል ግርግር ሲፈጠር ራሳቸውን አዋቂወች በማድረግ በተቃራኒና በከረረ መንገድ ከአዋቂወች ጋራ ተወዳዳሪወች አድርገው ራሳቸውን በማቅረብ በንግግራቸው ከሌሎች በላይ መስለው ራሳቸውን በማብለጭለጭ ወይም በማብለጥለጥ ላይ ያሉ አብያጽ ሐሳውያን ማለት ነው፡፡

በኢትዮጵያችን አተረጓጎም ሙሐዘ ጥበብ ማለት የፍልስፍና መፍለቂያ ማለት ሲሆን ፡፡ በሁሉም አተርጓጎም ፍልስፍና ማለት የፍቅርና የእውቀት ድምር ማለት እንደሆነ ተነግሮናል፡፡ እንደ ዶክተር ዳኛቸው አገላለጽ በዳንኤል ሕይወት ውስጥ የሚንጸባረቀው የእውቀትና ፍቅር ድምር ፍልስፍና መሆኑ ነው፡፡ ፍልስፍና መሆኑ ቀርቶ መስተዳጉጽ በመሆኑ የዶክተር ዳኛቸው አተረጓጎም ከኢትዮጵያዊውም ከግሪኩም አተረጓጎም ጋራ ተቃረነ፡፡

መስተዳጉጽ ቁራ

በቤታችን አተርጓጎሞ ዳንኤል ከኖኅ መርከብ ከወጣው ቁራ እጅግ የከፋና መስተዳጉጽ ነው፡፡

መስተዳጉጽ ማለት “ወልሳን መስተዳጉጽ ሆኮሙ ለብዙሀን ወአስተፋለሶሙ እምህዝብ ውስተ ሕዝብ ወአሕጉር ጽኑዓተ አመዝበረት ወአብያቲሆሙ ለዐበይት አውደቀት”(ሲራክ 28፡14) ተብሎ በመጽሐፍ በተገለጸው ክፉ ባህርይ የተመረዘ ሰው ነው፡፡

ይህም ማለት የሚናገረው የሚሰራው ህብረተ ስብን አቅጣጫ የሚያስት የህዝብን አመለካከት እያፋለሰ ህዝብንና ህዝብን የሚያጋጭ ሽመልስ አብዲሳ እንደሚያደርገው ሰወች የሚኖሩበርት እያፈረሰ የህብረተ ሰቡን ኑሮ የሚያቃውስ ማለት ነው፡፡

በቤተ ክርስቲያናች ውስጥ በነበረበት ወቅት ዘልቆ ባልተማረው ባልተረዳው ነገረ ማርያምና ነገረ መለኮት በመግባት የውጩን ሲኖዶሱን ከውስጥ ሲኖዶስ ጋራ፡ አቡነ ማትያስን በወቅቱ ከነበረው ከዲሲው ማሕበረ ካህናት፡ ከአኀት አብያተ ክርስቲያናትና ከሰንደቅ ጋዜጣ አዘጋጅ ጋራ በማጋጨት ላይ ተሰማርቶ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከብልጽግና ጎን ተሰልፎ በማጋጨቱ ተግባር በመቀጠል ከኖኅ መርከብ ከወጣው ቁራ የባሰ ሆኖ ቀረበ፡፡

ከኖህ መርከብ የወጣው ቁራ ከመርከብ ከወጣ በኋል ጭልፊቶችን ተሽከርክሪ እባቦችን ጥርሳማ ተኩላወችንና ጅቦችን ይዞን ወደ መርከቡ ተመልሶ አልበጠበጠም፡

ዳንኤል ከቤተ ክርስቲያን ወጥቶ ወደ ብልጽግና ከገባ በኋላ ዓቢይንና በዓቢይ የሚደገፉትን ጳጳሳት አንጋግቶ ተመልሶ መጣ፡፡ እንደገና በዓቢይ የሚደገፉትን ጳጳሳት ይዞ ወደ ቤተ መንግሥት በመሄድ በነ አባ ሳዊሮስ አማካይነት የቤተ ክርስቲያንን ቁልፉ ለጠ/ም ዐቢይ እንዲያስረክቡ አደረገ፡፡ ዳንኤል ለኢትይዮጵያ ያለውን ፍቅር በዚህ ሁሉ ስለካው የምረዳው በዱኩላና በነበር መካከል ያለውን ፍቅር ነው፡፡

በነብርና በድኩላ መካከል ያለ ፍቅር

በዳንኤልና በቤተ ክርስቲያን መካከለ ያለ ፍቅር አድኖ በሚበላት ነብርና ታድና በምትበላዋ ድኩላ መካከል ያለው

ፍቅር ነው እንድል እገደዳለሁ፡፡ ነብሩ ሥጋዋን አላምጦ አጥንቷን ቆርጠሞ ደሟን ጠጥቶ ሆዱን ለመሙላት ጥማቱን ለማርካት ንፍሱ እስኪወጣ ድኩላዋን ይወዳታል፡፡

“አብሮ የበላ አብሮ ይሞታል” የምንለውን ዝየ ልፈጽም ብየ ነው ካላሉን በቀር ዶክተር ዳኛቸው የዳንኤልን አራዊታዊ ፍቅር የተረጎሙበት አተረጓጎም እጅግ የተፋለሰ ነው፡፡ በዚህ አይነት ተፋልሶ አተረጓጎም የሚያሰትምሩ ከሆነ ለተማሪወቻቸው እጅግ አዘንኩላቸው፡፡ የክቡር ብርሃኑ ድንቄንም ንግግር እንዳስታውስ አደረገኝ፡፡

ክቡር ብርሃኑ ድንቄ በከንሳስና በሴንት ሉስ መካከል ባለችው ኮሎምብያ በምትባለው ከተማ ውድቀው የተረሱ ከተላላቅ ኢትዮጵያውያን አንዱ መተርጉም ነበሩ፡፡

ከከንሳስ ወደ ሴንት ሉስ፡ ከሴንት ሉስ ወደ ከንሳስ ስመላለስ ኮሎምብያን ድቅድቂያት ባለፍኳት ቁጥር የተናገሯቸው ትዝ እያሉኝ እንባየ ይፈሳል፡፡

እኒህ ታላቅ አባት በዘመኑ ትምህርት ሰለጠነናል የሚሉ ለሆዳቸው ብቻ የሚጥቅመውን መርጠው በቀረው ኢትዮጵያ ነክ በሆነው ሁሉ እንደሚዘምቱ “ኢትዮጵያውን የኢትዮጵያን ባህልና ስነ ልቡና ከሕሊናቸው አውጥተው ጥለውታል፡፡ የቀራቸው እንጀራ ብቻ ነው፡፡ እንጀራውንም እስካሁን የጠበቁት ስለ ባህልነቱ ስለቀርስነቱ አክብረውት ሳይሆን የሆድ ነገር ስለሆነባቸው ነው” ብለው ተናግረው ነበር፡፡

ዳንኤል የጻፈው ለቅርስ ለታሪክና ለኢትዮጵያዊነት ብሎ ሳይሆን የደራ ገብያ እየፈለገ መጽሐፍ ሸጦ የሚያገኘውን ገንዘብ ለመሰብሰብ ለሆዱ ብሎ ነው፡፡ ዶክተር ዳኛቸው መደገፋቸው “አብሮ የበላ አብሮ ይሞታል” የሚለውን እዳ ለመወጣት ነው፡፡

ዶክተር ዳኛቸው “አንተ ትጠላትለህ ብየ ለምንድነው በእንደዚህ ያለ ግምት የምንቀሳቀሰው?” ብለው ለጠየቁት አንድ ዕብራዊ ጸሐፊ ዳንኤልን ለሚመስሉ ዕብራውያን “የሰሙት ቃል ከሰሚወች ጋራ በእምነት ስላልተዋሀደ አልጠቀማቸውም” (ዕብ 4፡2) ብሎ የተናገረው ተጨማሪ መልስ በመሆን የበለጠ የሚያረካቸው ይምስለኛል፡፡

ዳንኤል የመገልበጥ እንጅ የመመራመር ስሜት አልነበረውም፡፡ የገለበጣቸው ስለ ሰው ክብር ተላልፎ መሞትን የሚያንጸባርቁ የጻድቃን ሰማእታት ተጋድሎ ናቸው፡

፡እየተመራመረ ቢጽፍ ኖሮ ጻድቃን ሰማእታት ካደረጓቸው ብዙ ነገሮች አንዲት ነገር በህሊናው ብቅ ትልለት ነበር፡፡

ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ የዳንኤል ፈላስፋነት ከደበቁበት ፈልቅቆ ወደ ብርሃን ማውጣት እንዳይችል አድረገው በማይገሰስ ግንብ ውስጥ ከተው በማይፈታ መስነግት ቆልፈውበታል፡፡ ቤተ ክርስቲያኔ የሰጠችኝን “አናቅጸ ሲኦል ኢይሄይልዋ” የሚለውን ጧፍ አብርቼ ወደ ውስጥ ስገባ የዶክተር ዳኛቸውን የተሳሳተ ምለምታ አገኘሁ፡፡

መላ ምትነቱን የሳተው የዶክተር ጌታቸው መላ ምት፡፡

ፈላስፋ በፖለቲካ የማይጠለፍ ከነባራዊ በመነሳት አዲሱን ክስተት በነባራዊው ክስተት ተርጉሞ “ጻድቃን የሐውርወ ወኃጣን ይስእንዎ” እንዲል የኔ ቢጤ ያልተማረ ሚኒሽያው መተርጎምና መገምገም ያልቻለውን ለመገምገም ብቃት ያለው ማለት ነው፡፡ ባሜሪካና በጀርመን ያለን ያልተማርን ሚኒሽያወች ማየት የተሳነንን ቀድመው በማያት ለማንቃት ለመጠቆም ነበር፡፡ ይህ ሐላፊነት በመንፈሳውያን ቀሳውስት መሪወች ላይ የበለጠ ቢሆንም እንደ ዶክተር ዳኛቸው ያለውን ፈላስፋ እኩል ይመለከተው ነበር፡፡

ዶክተር ዳኛቸው ህዝቡ ከጭንቅላቱ ውስጥ አውጥቶ የጣለውን ዳንኤል ክብረትን መልሰው በህዝብ ጭንቅላት ላይ አክሊል አድርገው ለመጫን ባደረጉት ሙከራ “በዚህ እድሜየ” እያሉ በጠቀሱት ረዥሙ ዕድሜያቸው ባጠራቀሙት ልምዳቸውና በፍልስፍናቸው አሽሞንሙነው አቅረበውታል፡፡

እንኳን ዳንኤልን ከወደቀበት ሊያነሱት “ብእሲ ምሁር ዘተገሰጸ ብዙኃ የአምር ወዘአፈድፈደ ሕማመ ጥበበ ይነግር“(ሲራክ 31፡9)፡፡ በሚለው ምንባብ ላይ የተመሰረተው ኢትዮጵያዊው የአንድምታ አተርጓጎም ራሳቸውንም ከዳንኤል ጋራ ደምሮ አውርዶ ጥሏቸዋል፡፡

ማለትም፦ የተማረ ይልቁንም በረዥም ዕድሜው ውጣ ውረድ ሕይወቱ የተስተካከለ ሰው ካንደበቱ የሚፈልቀው ሰሚውን ከስህተት የሚያድን ጥበበኛ ነው፡፡ በዶክተር ዳኛቸው ይህንን ጥበብ አላገኘሁትም፡፡

ይልቁንም “እስመ ለብዙኃን አስሐቶሙ ሕልም ወወድቁ እንዘ ኪያሁ ይሴፉ”(ሲራክ 31፡7) እንዲል፦ማለትም፦ የተመኙትና ተስፋ ያደረጉት ሕልማቸው ብዙወቹን አሳሳታቸው ተብለው ከተፈረጁት አንዱ ሆነው አገኘኋቸው፡፡

ዶከተር ዳኛቸው እንደ ቀደሙ ፈላስፎች ከውጭ ሰርገው የሚገቡትን የማይጠቅሙ ሐሳቦች ይቅሩና የራስቸውን ሕልም እንኳ ከነባራዊው ክስተት ያላፈነገጠ ከሕዝብ ፈቃድ ያልወጣ እንዲሆን በመጣር ባሜሪካና በጀርመን ከምንገኝና አልተማራችሁም ሚንሻወች ናችሁ ከሚሉን የበለጠ የተጠነቀቁ ሊሆኑ ይገባቸው ነበር፡፡

ያልተማሩ ሚኒሽያ ናቸው ብለው የሚአጣጥሉን ባሜሪካና በጀርመን የምንኖር ቀድመን ተረድተን ዳንኤልን ለጠቅላይ ምንስቴሩ የምትሰጠው ምክር አገር እየጎዳ ነው፡፡ ይልቁንም ሕዝበ ክርስቲያኑን እያስጨፈጨፈ ነው እያልን ድምጻችንን እያሰማን ሳለን ራሳቸው “እኔ ገና አጣጣሜ ሳልጨርስ” እንዳሉት በዳንኤል ምክር የሚካሄደውን ገና በማጣጣም ላይ ነበሩ፡፡

ዶክተር ዳኛቸው በማጣጣም ላይ የነበሩበትን ጣእም እንመልከተው፡፡

ያጣጥሙት የነበረው የኢትዮጵያ ገጸ ምድርግ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በኦርቶዶክሳውያን ወገኖች አካል ሬሳ መሸፈኑን ነው? የገጸ ምድሩ አፈር ከፈሰሰው ከክርስቲያኖች ደም ጋራ ተቀላቅሎ በሚተንፈሱት አየር ባፍንጫቸው መጋታቸውን ነው? ከሚመነጩት ወንዞች ጋራ ተቀላቅሎ የሚጎርፈውን የወገንን ደም መጠጣቸውን ነው? በመላ ኢትዮጵያ የሚንፍሰው አየር ከወገን ደም አጽምና ሥጋ ጋራ የተቀላቀለውን አፈር ከመሬት እየጋፈ ቆሞ በሚሄደው አካላቸው ላይ በመበተን በቁማቸው መቀበራቸውን ነው? ሕጻናቱ በሙታን እናቶች ደረት ላይ ተጣብቀው ከደረቀ ጡት ወተት ለማመንጨት ሲታገሉ ማየታቸውን ነው? እናቶች የሞቱ ልጆቻቸውን እሬሳ ታቅፈውና በልጆቻቸው ሬሳ ላይ ወድቀው ማየታቸውን ነው? በትግራይ ያሉት እናቶች በልጆቻቸው ገዳዮችና አሰገዳዮች መርዶ ነጋሪነት በማልቀስ ላይ መሆናቸውን ነው? ዶክተር ዳኛቸው ይህ ሁሉ በሚፈጸምባት ኢትዮጵያ አልነበርኩም ሊሉ ነው?

ብልጽግና በወገን ላይ እያደረሰ ያለውን ይህንን ሁሉ ግፍ ለማስቆም በመታገል ያለውን ፋኖን ጃዊሳ ብሎ ዳንኤል በመዝለፉ ከብልጽግና ደጋፊ በቀር የቀረውን ሁሉ ዜጋ አስቆጥቷል፡፡ በገር ውስጥ ባሜሪካና በጀርመን የምንኖረው

ዳንኤል ለጠ/ም የሚሰጠው ምክር ልክ አለመሆኑን ገልጸን ለማሳይት ሞክረናል፡፡

በዳንኤል ላይ የተሰነዘረውን ተግሳጽ በመቃወም ዶክተር ዳኛቸው በአሜሪካና በጀርመን ያለነውን ኢትዮጵያውያን ያልተማሩ ሚኒሻወች በማለት የተናገሩት የተሰለፉበትን ሙያ “ወጉርዔ ይፈልጦ ለኩሉ ጣእመ እክል ወከማሁ ልቡ ለጠቢብ ይፈልጥ ነገረ ሐሰት”(ሲራክ 36፡29) በሚለው መጽሐፍ ስፈትሸው ገና በርበሬና ጨው አጣጥሞ ያልተረዳ ሕጻን ሆነው አገኘኋቸው፡፡

ማለትም፦ ጉረሮ ከመዋጡ በፊት የህሉን ጣእም አጣጥሞ እንደሚያውቅ የተማረ አዋቂ ነኝ ብሎ ለማስተማር በሰው ፊት የሚቆም ሰው በሀሰት በእውነት መካከል ያለውን ቁልፍልፍ ለይቶ ሊያውቅ ይገባል፡፡ ይሁን እንጅ ዶክተር ዳኛቸው በዚህ ንግግራቸው በሙያቸው ልክ ሆነውና በቅተው አላየኋቸውም፡፡

“ዕቀብ ልበከ እምነ ዘይመክረከ ቅድመ አእምር ትካዘ በዘይፈቅደከ እስመ እንበይነ ርእሱ ያመክረከ (37፡8)፡፡ እንዳለው መጽሐፍ በህዝብና ባገር ላይ ያንዣበበውን መከራ በጀርመንና ባሜሪካ ካለን ሚኒሽያውች አስቀድመው ተረድተው በገለጹት ነበር፡፡ ይህም ማለት፦”ህሊናህን ስልሎ ከሚንቅህ የቅርብ ጠላት ራስህን ጠብቅ፡፡ ወደራሱ ምኞት በመጎተት ይፈታተንሀልና ወዴት እንደሚጎትትህ እወቅ”

እንደ ዶክተር ዳኛቸው ያሉ የፍልስፍና መምህራን እንደነ ዳንኤል የመሳሳሰሉ ሸፍጠኞች በተብለጭላጭ ሸፍጣቸው የህዝብን ጭንቅላት እያሽከረከሩ ህዝብን ካደጋ አገርን ከመፍረስ እንዲታደጉ ነበር፡፡

እንዲያውም በ cortex ሀሳብ በሚመዘግበው ጨቅላቱ ላይ ምንም ያልተሳለበት መገምገሚያ የሌለው ገና ከናቱ መሕጸን ዛሬ የተወለደ ጨቅላ ሆነው የዳንኤልን ሐሳብ እንዳለ በመጋት እኛንም ሊግቱን ሞከሩ፡፡

“ዘፍጡነ የአምን ቀሊል ልቡ ወዘይገብር ኃጢአተ ላዕለ ነፍሱ ይኤብስ ”(ሲራክ 19፡4) እንዳለው ማለትም፦ የተነገርውን ሳይመረምር ሳያበጥር ፈጥኖ በመቀበል አምኖ የሚከተል ህሊናውን በጸጸት የሚጎዳ ኃጢአት የሚሰራ ቀሊለ ልብ ሆኑ፡፡

ከተማሯቸው ትምህርቶች ካነበቧቸው መጻሕፍቶች በአሜሪካና በኢትዮጵያ በቆዩባቸው ዘመናት ካጠራቀሟቸው ትዝብቶች የዳንኤልን ሸፍጥ መለየት የምታስችል ትንሽ የፈሊጥ ብልጭታ እንዴት ያጣሉ?

ዶክተር ዳኛቸው የዳንኤልን ሸፍጥ መለየት የሚያስችል ትንሽ የፈሊጥ ብልጭታ ማጣታቸው፡ ዓለም በጨለማው በነበረችበት ዘመን ጭንቅላታቸው እንደ አጥቢያ ኮከብ ያበራ የነበሩት መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ የተናገሩት እንዳጤነው አደረገኝ፡፡

መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ “የኢትዮጵያን ስነ ልቡና

ሳንቀርጽባቸው ኢትዮጵያውነትን ሳናሰርጽባቸው

ስንዋጋቸው ወደ ነበሩት ፈረንጆች ይማሩ እያልን አንላኳቸው፡

፡ኢትዮጵያ የተጠበቀችበትን ስነ ሕሊና ሳናስረዳቸው ወደ ውጭ የሚሄዱ ሁሉ ባዶ ሸክላወች ናቸው፡፡ ቂማቸውን የማይረሱ ጠላቶቻችን ባዶ ጭንቅላት ሲያገኙ የራሳቸውን አመድና አተላ ይሞሏቸዋል፡፡ በባዶ ጭንቅላታቸው የዛቁቱን አተላና አመድ አምጥተው በኢትዮጵያ ላይ ይደፉባትና ለማጥራት በሚታገሉት ጀግኞች ልጆቻችን ላይ መከራ እንጭንባቸዋለን”፡ ያሉት ታሪካዊው ንግርታቸው ዛሬ ዶክተር ዳኛቸውን በመሳሰሉ ያስኳላ ተመሪወች የተፈጸመ መሰለኝ፡፡

ታላቁ ፈላስፋ አባታችን መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ባንድምታ አተረጓጎም ክሂሎታቸው በነባራዊው ኢትዮጵያዊ ኩነት ከውጭ የሚመጡትን ክስተቶች አበጥረው በማየታቸው ከሁለቱ ስብቀት የተፈነጠረውን መላምት ገለጹት እንጅ ህልምም ጥንቆላም አልነበረም፡፡

እነሆ ዛሬ ኢትዮጵያና የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ያህያ አፈላላጊ በሚመስሉ በብዙ philistines ማለቴ አብያጽሐሳውያን ተከበዋል፡፡ ዶክተር ዳኛቸው በመሳሰሉ ያስኳላ ተማሪወች ከውጭ እየዛቁና እየተሸከሙ አምጥተው በኢትዮጵያዊነት በኦርቶድክስነት ባማረኛ ቋንቋና ባማራነት ላይ የደፉትን አተላና አመድ ለመጥረግ በመታገል ላይ ባሉት በፍኖወችና በመሳሰሉት ኢትዮጵያውያን ላይ ወደቀባቸው፡፡

የዶክተር ዳኛቸው ንግግር ቀስቅሶኝ ያቀረብኩትን ሀተታ ባንድ ሌላ ኢትዮጵያዊ ሊቅ አነጋገር እደመድማለሁ፡፡

ባንድ ዘመን አቶ በዛ አቶ ለማና አቶ ጀንበር የሚባሉ የምንግሥት ሹማምንት ሌቦች ያገሩን ሁሉ በረት እየከፈቱ ጉረኖ ጋጥ እየሰበሩ ሙክቱን በሬውን ላሙን እየዘረፉ ሕብረተ ሰቡን አስቸገሩ፡፡ ባለአገር ለመንግሥት ቢጠቁምም ምንግሥት ራሱ ከሌቦች ጋራ እየተናበበ አድራጊና አሰድራጊ ሆኖ የሚጠቁመውን ባለአገር መደብደብ ማሰር ጀመረ፡፡

በህዝቡ መሰቃየት ይናደዱ ይበሳጩ የነበሩ መላከ ብርሃን አድማሱን የመሰሉ ሊቅ፡ ላውጫጭኝ ስብሰባ በተሰበሰበው ሕዝብ መካከል ቆሙና “ወገኔ ባላገር ሆይ እኔን ስማኝ” ብለው በጭብጨባ ህዝቡን ዝም ካሰኙ በኋላ “ሌባው ባካባቢያችን በዛ፡፡ ባገራችንም ሌባው ለማ፡ ጀንበር በሰረቀ ቁጥር እንዴት እኛ ባላገሮች ስንሰቃይ እንኑር? ብለው ባረፍተ ነገር የሌቦችን ስም ደርድረው ተናገሩ፡፡

በምንግሥት ተደግፈው ህዝብ ሲዘርፉና ሲገሉ የነበሩትን አቶ በዛ፡ አቶ ለማና አቶ ጀንበር የተባሉትን የመንግሥት ሹመኞች ቅኔውን የተረዳው ፋኖ ከህዝቡ መካከል እዚያው አንቆ ይዞ የፍጥኝ አሰራቸው፡፡ ባለአገርም ከግፈኞች ተገላገላገለ፡፡

ይህ ዘመን በዳንኤል ክብረት ምክር እንደ ጠ/ም ዓቢይ የሚመሩ ያህያ አፈላላጊወች የበዙበትና የለሙበት ዘመን ነው፡

25

ጀንበር በወጣችና በጠለቀች ቁጥር የሚሰማው ዘረፋ መፈናቀል ስደት ብዝበዛ ግድያና ዋይታ ነው፡፡

“አሀያ ያየህ ና ወዲህ በለኝ፡ አህያየን አግኝቻታለሁና በከበባት ጅብ እንዳትበላ ርዱኝ” እያለ በውስጥም በውጭም ያለው ፋኖ ድምጹን እያሰማ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ይህን የመሰለ ችግር ሲገጥማት እጆቿን የምት ዘረጋው ወደ እግዚአብሔር ነው፡፡ የምትዘረጋቸው እጆች የማይዳሰሱ አካል የሌላቸው ጥላወች አይደሉም፡፡ የኢትዮጵያ እጆች ተብትበው አስረው አፈላላጊ መስለው ከሚቀርቡ አፈላሊጊ ሌቦችና ከከበቧት ጅቦች ለማትረፍ በመታገል ያሉት የፍኖወች እጆች ናቸው፡፡

ካፈላላጊ ሌቦች ራሳችሁን አላቃችሁ ከፋኖ ጋራ እጆቻችሁን ለግዚአብሔር በመዘርጋት ድምጻችሁን ለዓለም በማሰማት ለሙያችሁ ክብር ብትቆሙ የሞራል ግዴታችሁን የምትወጡ ይመስለኛል ብየ ለዶክተር ዳኛቸውና ለመሰላ ችሁት ሁሉ ፋላስፎች ካልተማሩት ሚኒሽያወች አንዱ የሆንኩ ወንድማችሁ መልእክቴን በትህትና አቀርብኩላችሁ፡

ይቆየን
https://amharic-zehabesha.com/archives/187377

Friday, November 24, 2023

በመጽሐፈ መነኮሳት ሲመዘኑ ”አቡነ ኤርምያስ” ከድጡ ወደ ማጡ ሰመጡ!
በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ከመጻሕፍተ መነኮሳት አንዱ የሆነው ፊልክስዩስ  ገጽ 106 ላይ “እንኪያስ መነኮሳት ነውር ነቀፋ የሌለባቸው ሁነው በፍጹም ሥራ ሊኖሩ ይገባቸዋል” ይላል፡፡* ሌላኛው መጽሐፍ መነኮሳት ማር ይሳቅ እንደዚሁ ገፅ 106 ላይ “አቡነ” ኤርምያስ ስሙን የዘረፉትን ቅዱስ ኤርምያስን ከጠቀሰ በኋላ “ እግዚአብሔር ሳንፈራ ሳንበርድ ጸላታችንን (ሰይጣንን ማለቱ ነው) እንገጥመው ዘንድ ያዝዛልና” ብሎ “ሳይቀድምህ ቅደመው...ትወጋው ዘንድ መር ብለህ ቁንጮውን ያዘው”* እያለ ያዝዛል፡፡

ሰይጣን እግዚአብሔርን የከዳ ቀደም ሲል ከመላእክት አንዱ እንደነበር ይታወቃል፡፡ መላእክት ደሞ እንደ ሰው አካል ወይም እጅና እግር እንደሌላቸው ይታወቃል፡፡ ሰይጣን ወይም ሳጥናኤል የሚጠቀመው እጅና እግር ያላቸውን ዋሾዎች፣ ቀጣፊዎች፣ ከሃዲዎችትን፣ ዘራፊዎች፣ አረምኔዎችና ጭራቆችን  መሆኑን “አቡነ ኤርምያስና ጓዶቻቸው” የዘነጉት ይመስላል፡፡ ሰይጣን የእርጉዝ ሆድ በመቅደድ፣ ሰው ዘቅዝቆ በመስቀል፣ ሕዝብን ከነነፍሱ በማቃጠል፣ እሬሳ በመጎተት፣ ገዳማትና ቤተከርስትያንን በማቃጠል እንደሚከሰት ለማመን ለግመዋል፡፡ “ይሁን ይሁን፤ አይሆንምን አይሆንም በል” የሚለውን የመጣፍ ቃል ተላልፈው እንኳን ሰይጣንን ቁንጮውን ሊይዙ  ሰይጣንን ሰይጣን ለማለትም እንጀራ አንቋቸዋል፡፡

አደራቸውን ለመወጣት ከመልገምም አልፈው “አቡነ ኤርምያስ” የአማራን ሕዝብ በሚጨፈጭፉት ሰይጣን በተሰቀላቸው ወታደሮች ታጅበው ፋኖን ስለመወረፋቸው ሲጠየቁ ሕዝቡን እየራበው ስለሆነ ለሆዱ ሲል ላጀቧቸው ጪራቅ ገዥዎች እጅ ይስጥ ዓይነት ቃለ መልስ ሰጥተው አርፈዋል**፡፡

“ጳጳሱ” ቅዱስ ዳዊትን በጎልያድ ላይ ያነሳው እግዚአብሔር ፋኖን በጭራቆች ላይ እንዳስነሳው ለማመን ተቸግረው ፋኖን ተማብጠልጠል አልፈው ጳጳስ ነኝ በሚሉበት አገር እሬሳ እንደ ግንድ መሬት ለመሬት የጎተተውን አረመኔ ትተው በውጭ ያሉ የፋኖ ደጋፊዎችን “የሬሳ ነጋዴዎች” ብለው ትርፍ ቃል ተናግረዋል፡፡

“ዶሮ ብታልም ጥሬዋን” ይባላል፡፡ ሆዳም እሚያልም ምግቡን እንጅ እውነትን፣ ፍትህን፣ ክብርንና እምነትን ስላልሆነ እንደ ”አቡነ” ኤርምያስ ምክር ወይም ትዕዛዝ ተሆነ አማራ ለሆዱና ለህክምና ሲል ክብሩን፣ ማእረጉን፣ እምነቱን፣ ፍትህና እውነትን መጣል አለበት፡፡ እኒሁ “ጳጳስም” ሆነ ሌሎች ጓደኞቻቸው የአማራ ሕዝብ ለግማሽ ክፍለ-ዘመን በእቅድ አገር አልባ እንዲሆን ከተቻለም እንዲጠፋ የተፈረደበት መሆኑን ያውቃሉ፡፡ መስቀል ጨብጠውና ቆብ ደፍተው ግን ይኸንን በአማራ ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ የክቡር አቶ ታዲዎስ ታንቶን ያህል የመናገር የእምነትም ሆነ የሞራል ብቃት አላገኙም፡፡

ጳጳሳት ከወራት በፊት እነ ሄሮድና ጲላጦስ ስልጣናቸው ሊነጥቋቸው ሲሉ ለሕዝቡ የድረሱልን ጥሪ አቅርበውና ሕዝብ አስፈጅተው ስልጣናቸውን ታረጋገጡ በኋላ ሕዝቡን ከፈጁት አረመኔዎች ጋር መላላስ እንደ ጀመሩ የሚታወቅ ነው፡፡ ህፃናት ሳይቀር በሚያርዱት በእነ ሄሮድስ ተገደውም አሜሪካን አገር በአስገድዶ መድፈር ሙከራ የተከሰሱ “ መነኩሴ ነኝ” ባይ ጣኦተኛ ጳጳስ አድርገውን ስልጣን እንደሰጡ የሲኖዶስ ተብየው ስራ አስኪያጅ የተናገሩትን ልብ ያለው የሚያስታውሰው ነው፡፡ ይህ ሁሉ እየሆነ “አቡነ ኤርሚያስ” ቤተክርስትያኗን እየጠበቁ እንደሆነ ሲናገሩ መስቀላቸውን ያነገቱበት ማተብ ትንሽም አልገታቸው፡፡

ምእመናን ሆይ፡-ቤተከርስትያን ማለት የቤተክርስቲያናን አእዋፍ (ራስ) ክርስቶስን፣ ሕዝብና የአምልኮት ሥፍራን (ቤተክርስትያናትና ገዳማትን) የሚያጠቃልል ነው፡፡ እነደሚታወቀው ቤተክርስትያኗን ቀጥ አርጎ የያዘው የአማራ ሕዝብ የህልውና አደጋ የተጋረጠበትና  በድሮን በመጨፍጨፍ ላይ ያለ ሕዝብ ነው፡፡ የአምልኮት ቦታውም በአህዛብና በአውሬዎች እየተቃጠለ ነው፡፡ ክርስቶስም ከእርሱ ይልቅ ይህቺን ምድራዊ ዓለም በመረጡ ጳጳሳትና አቡን እየተከዳ ነው፡፡ ታዲያ ቤተክርስትያኗን እየጠበቅን ነው የሚሉት የትኛውን የቤተክርስትያን ክፍል ጠብቀውት ነው?

ፋኖን ያብጠለጠለው የአቡነ ኤርምያስ አንደበት ለምእመናኑም እውቅና ባይሰጥም እግዚአብሔር ምስጋና ይግባውና የኢትዮጵያ ቤተክርስትያን እየተጠበቀች ያለችው ለምኖ ሳይቀር አስራት በሚከፍለው ጽኑ እምነት ባለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፡፡ ቤተክርስትያኗ እየተጠበቀች ያለችው አንገቱን ለሰይፍ ሊሰጥ በተዘጋጀ አማኝና ሰማእት በመሆን ላይ ባሉ የቤተክርስትያን አገልጋይ ካህናት ነው፡፡ ጳጳሳትና አቡኑ ሰማእትነታቸውን የስልጣን ማደላደያ ያደረጓቸው የሻሸመኔ መእመናንና ካህናት ለዚህ ምስክር ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተክርስትያን እየተጠበቀች ያለችው በህይወት ሳሉ በተዋደቁላት ቅዱሳን በአቡነ ጴጥሮስ፣ አቡነ ሚካኤል፣ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ መላከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬና በሌሎችም መንፈስ ነው፡፡

የዛሬዎቹ አቡንና ጳጵሳት ያልሰነፉት የምእመናን አስራት በደሞዝና ውሎ አበል ስም መላፍና ቁንጣን ሲይይዛቸውም ወደ ውጪ ሄደው መታከሚያ ማድረግ ነው፡፡ “አቡነ ኤርምያስ” የቤተ-ክርስትያኗ ግድግዳና ማገር የሆነው የአማራ ሕዝብ እየተራበና የህክምና አገልግሎት እንደማያገኝ በተናገሩበት ምላስ አንዱ ጓደኛቸው በአሁኑ ሰዓት ዘመናዊ ሕክምና ለማግኘት አሜሪካን አገር እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በፊቱም ብዙዎቹ አሜሪካና አውሮጳ እየሄዱ ህክምናውንም ሽርሽሩንም አድርገዋል፡፡ መታከሚያ ያጣ ቁስለኛ በቁስሉ እየለመነ አስራት ይከፍላል ጳጳስና አቡን ዶላሩን እንደ ሳር ነስንሶ አውሮጳና አሜሪካ ይታከማል፣ ይዝናናል፡፡ ቲኬት ቆርጦ፣ ለወራት ሆቴል ተከራይቶ፣ ካለምንም ኢንሹራንስ አሜሪካን አገር መጥቶ ለመታከም የሚያስፈልገው ገንዘብ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢያንስ አንድ ሺህ ክሊኒክ አሰርቶ ሥራ ያስጀምራል፡፡  ጳጳስት ምእመናኑ ሲታመሙ ተጠመቁን እየሰበኩ ወደ ፀበል ሥፍራዎች እየላኩ የእነሱ ፀበል ቦታዎች ዘመናዊ የአውሮጳና የአሜሪካ ሆስፒታሎችና ክልኒኮች ሆነዋል፡፡ አስራት ከፋዩ ሕዝብ ሲኖድን በሚያሽከረክሩት ጭራቅ ገዥዎች በችጋርና በበሽታ ሲያልቅ ጳጳስና አቡን እንደሚሰግዱላቸው አረመኔ ገዥዎች ሁሉ አውሮጳና አሜሪካ እየነጎዱ ሆድ ቁርጠትና ራስ ምታት ሲታከሙ ይታያል፡፡ ይኸም ሆኖ ዓይናቸውን በጨው ታጥበው ምዕመናኗ እየተጨፈጨፈ ያለውንና ገዳሟና ሕንፃዋ የሚነደውን ቤተክርስትያን እየጠበቅን ነው ይሉናል፡፡

እንደ ሌሎች የሲኖድ ጓደኞቻቸው ሁሉ በትምህርት፣ በእምነትና በመንፈስ ልዕልና የበሰሉ የማይመስሉት “አቡነ ኤርምያስ” አንዲትም የመጽሐፍ ቃል ሳይጠቅሱ ቃለ መጠየቁን በካድሬ ቃላት ጨርሰዋል፡፡ ለሆዱ ሲል የአማራ ሕዝብ ክብሩን፣ እምነቱን፣ ማእረጉን፣ ህልውናውንና አገሩን ለሰይጣን አሳልፎ ይስጥ ዓይነት የሚያሳፍር ንግግር አድርገውን ተድጡ ወደ ማጡ ወርደዋል፡፡ እግዚኦ!

 

*ምእመናን ሆይ የመነኮሳት፣ ጳጳሳትና አቡኑን መለኮታዊ ግዴታ ለማወቅ እባክዎን መጻሕፍተ መነኩሳትን ያንብቡ፡፡ አመሰግናለሁ፡፡ መጻሕፍተ መነኮሳት 1929 ብርሃንና ሰላም እትም፡፡

 

**ቃለ መጠይቁ የአማራ ህዝብ ተበድሏል። ይህ መንግስት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ ነው። እኔ ፋኖን አልወቀስኩም። ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ - (amharic-zehabesha.com)
https://amharic-zehabesha.com/archives/187352
አማራ የጨበጠውን የነብር ጅራት ከለቀቀ …! ብሥራት ደረሰ
ጨለማ ሊወገድ ሲል ጣጣው ብዙ ነው፡፡ ድቅድቅ ጨለማ ተወግዶ በምትኩ የብርሃን ፀዳል ሊፈነጥቅ ሲል በሚያጋጥም የዐይን መጥበርበር እምብዝም መደናገጥ አይገባም፡፡ ጨለማው ሊወገድ ነው፡፡ ብርሃንም ሊመጣ ነው፡፡ ስንጠብቀው የነበረ ነገር ነው፡፡ ይሁንና አማራው በአለኝታው በኩል የጨበጠው የነብር ጅራት ሊለቅ አይገባውም፤ አይሆንም እንጂ ቢለቀው ግን ከምድረ ገጽ ይጠፋል፤ “አማራ የሚባል ነገድ በምሥራቅ አፍሪካ ይኖር ነበር” ተብሎም በታሪክ ይወሳል፡፡ ለዚህ የአማራ ውድመት ከጠላቶቹ ጋር ተሠልፈው ከውስጥም ከውጪም የሚወጉት የአማራው ነገድ አባላት ቁጥር መብዛቱ ግና የአማራውን የነጻነት ተጋድሎ እያወኩና የትንሣኤን ዘመን እያዘገዩም ይገኛሉ፡፡ በሆዳቸው የሚያስቡ ብአዴናውያን አማሮች ባያስቸግሩት ኖሮ አማራ ይሄኔ ራሱን ቀርቶ ሀገሩን ኢትዮጵያን ነጻ አውጥቶ ነበር፡፡ ግዴለም ይሁን፡፡ ለበጎ ነው፡፡ መጥራት ያለበት ነገር እንዲጠራም ሊሆን ይችላል ይሄ ሁሉ የመከራ ዶፍ መዝነብ ያለበት፡፡ ትልቅ ሰው ሲዋረድ፣ ትንሽ ሰው ሲከብር ማየት የሚቻለው በዚህን መሰሉ የችግርና የመከራ ዘመን ነው፡፡

እየታዬ ያለው ቅጥ ያጣ ሃይማኖት የለሽነትና ሆዳምነት፣ ምግባረ ብልሹነትና ሰይጣናዊነትም ቀድሞ ያልታወቀና ያልተነገረ አይደለም፡፡ ገና ከዚህም የከፋ ሁኔታ ሊገጥመን እንደሚችል መገመት አይከብድም፡፡ ግን ይነጋል፡፡ ሊነጋ ሲል የንጋቱ ጎርፍ የሚጠራርገው የሕዝብ ቁጥር ግን ከሚታሰበው በላይ ነው፡፡ ለወርቃማው ዘመን አድረሰኝ ብሎ ራስን ከኃጢኣት በማቀብ መጸለይ ግን ወሳኝ ነው፡፡ የሚታመኑ በከዱበትና ለከርሳቸው በተንበረከኩበት ወቅት ቆንጆዎቹ ካላሰብነው ቦታ ይወጣሉ፡፡ እንጠብቅ፡፡

ሀገራችን ከላይ እስከታች በዕብዶች የተወረረች ናት፡፡ ይሄ የዘረኝነት ልክፍት በፖለቲካው ውስጥ ከገባብን ወዲህ ላለፉት ዐርባና ሃምሣ ዓመታት የተዘራው የክፋትና የጎጠኝነት ልክፍት ያላበላሸው ሰው የለም፡፡ ትልቁም ትንሹም በዚህ በሽታ ተለክፎ ከሃይማኖትና ከሞራል፣ ከሰብኣዊነትና ከባህል ወጥቷል፡፡ ስለሆነም በሚታዬው የተዘበራረቀ ነገር ብዙም ማዘን አእምሮን ወደማሳጣት ያመራልና እንጠንቀቅ፡፡ ከዘረኝነትና ከሆድ ዕዳ ነጻ በወጡት በነፋንታሁን ዋቄ እንጽናና፤ በነታምራት ነገራ እንጽናና፤ በኢትዮሰማዩ ጌታቸው ረዳና በዶክተር ኃይሉ አርአያ እንጽናና፡፡ እንጂ እንደተዘራው የዘረኝነት እንክርዳድ ቢሆን ኖሮ አብቅቶልን ነበር፡፡

ፍቅርሲዝም የሚባል ሃይማኖት መሠረትኩ የሚለውን ነቢ ደምሳሽ የሚባል ዕብድ የምታውቁት ታውቁታላችሁ፤  ሥራ ስንፈታ አንዳዶቻችንን በጣም ያዝናናናል፡፡ የማርያም እህት ነኝ የምትል ሌላ ወፈፌም አለች፤ በርሷም እንዝናናለን፡፡ በየቸርቹ ሁሉ የሚሰማውና የሚታዬው በክርስቶስ ኢየሱስ ስም የሚደረገው የቁጩ ፈውስና ድራማ ሲታይ ደግሞ በርግጥም እምቢልታ ነፊዎቹ መላእክት ሰንፈው እንጂ የመጨረሻው ዘመን ፊሽካ መነፋት ከነበረበት ጊዜ በእጀጉ እንደዘገዬ መረዳት አይከብደንም - ችግሩ እንግዲህ የእግዜሩና የኛ የሰዎች የዘመንና የቀን አቆጣጠር በእጅጉ መለያየቱ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ ትብታባዊ አፍዝ አደንግዝና የዕብዶች ቱማታ ዋና አለቃና ቁንጮው ሰውዬ ደግሞ አቢይ የተባለው ዕብድ መሆኑ ሊካድ አይገባውም፡፡ ይህ ሰው የሥነ ልና ችግሮች አንድም ሳይቀሩ የሰፈሩበት ዋናው የሣጥናኤል ልዑክ ነው፡፡ የሰይጣን ቁጥሮች 13 እና 666 ደግሞ ከአፉም ከአለባበሱም አይጠፉም፡፡ እዩና ታዘቡ፡፡

የሚገርመው ታዲያ ለዚህ ዕብድ ሰውዬ የሚያሸረግደው ሰው መብዛት ነው፡፡ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ የተሰለፈው የዚህ ሰውዬ አሽከርና ደንገጡር ሲታይ እውነትም ሰይጣን ኃያል ጣዖት መሆኑ ይከሰትልናል፡፡ ከዲያቆን እስከ ጳጳስ፣ ከምሁር እስከ ማይም፣ ከሕጻን እስከሽማግሌ … ይህን ወፈፌ እንደአምላኩ ተቀብሎ የሚሰግድለት ወገን ሲታይ አግራሞታችን ከፍ ይላል፡፡ ዕዝ እኮ ነው!

ከሰሞነኛ ጉዳዮች አንዱን ብንወስድ ለምሣሌ በጣም እወዳቸውና አከብራቸው የነበሩ አንድ ጳጳስ ባልጠበቅሁት መንገድ ከተሣፈሩባት ሕዝባዊ መርከብ ሸርተት ብለው ወደጨለማው የሣጥናኤል ግዛት ወደሚነጉደው የአቢይ መርከብ መዛወራቸው ነው፡፡ ለውጥ ያለና የሚኖር ቢሆንም አንድ ሰው ሲለወጥ ከክፉ ወደ ጥሩ እንጂ ከጥሩ ወደ ክፉ ብዙም የተለመደ አይደለምና የዚህ ሰውዬ ከእግዚአብሔራዊ መንገድ አፈንግጦ ወደሣጥናኤል ጎራ የመቀላቀሉ ነገር ብዙዎቻችንን አስደንግጦናል፤ አሸማቆናልም፡፡ ይህች አንዲት ሆድ አንድን ሰው ምን ያህል እንደምታዋርደው እያየን ነው፡፡ በሚገርም የነገሮች ሂደት ውስጥ እንገኛለን፡፡ በስመ አብ!!

እኔ ስገምት ይህን ሰው ለዚህ ውርደት የዳረገው እነዚህ ሰይጣኖች አንድ የያዙበት ማስፈራሪያ ነገር ቢኖር ነው፡፡ “ይህን ብለህ ካተናገርህ እንትን ስታደርግ የያዝነውን እንትን ለሕዝብ እንትን እናደርገውና እንትን ትሆናለህ ….” የሚል መስፈራርቾ ሳያደርበት የቀሩ አይመስለኝም፡፡ እንጂ በጤናው ሀገራችንን አሁን በያዘው መልክ ብትንትኗን ያወጣ ሰው ለሀገር እንደሚጠቅምና አለ የሚባለውም መከላከያ በርግጥም የኢትዮጵያ እንደሆነ አምኖ ሊሆን አይችልም፡፡ ሁሉም ነገር እኮ የአደባባይ ምሥጢር ነው፡፡

ይህ ሰው አንዴ ራሱን በቁም ገድሏል፡፡ በዚህ ሰውዬ ጊዜን ማባካን አይገባም ባይ ነኝ፡፡ የሚያስጠላው ግን የልቡን ተናግሮ ሲያበቃ ወግ አይቀርምና የክርስቶስን ዘመን የስቅሎ ታሪክ በማውሳት ስቅሎ ስቅሎ አሉኝ ብሎ መናገሩ ነው፡፡ ሌላህን ብላ በሉት፡፡ ሴተኛ አዳሪዋ “አጭበርባሪ አይተኛኝም” ብላለችና ማንም ቅልስልስ የልቡን ሠርቶ ይቅርታ የሚልበት ዘመን ማለፉን ንገሩት፡፡ አሁን አካፋን አካፋ ማለት የተለመደበት የመጨረሻ ወቅት ነው፡፡ አማራንና ትግሬን እያባላ ስንትና ስንት ወንጀል የሠራን የኦሮሙማ ቅልብ ጦር እንደሀገር መከላከያ በመቁጠር አትንኩብኝ ማለቱና ፋኖን “የትም አትደርሺም፤ አርፈሽ ተቀመጪ፤ መሣሪያሽንም አኑረሽ አርሰሽ ብይ” የሚልን ወምበዴ ጳጳስ ከእንግዲህ አማራ ይቀበላል ማለት ሣጥናኤል የሚወዳትን ሲዖልን ትቶ ከገሃነም ወደ መንግሥተ ሰማይ ተመለሰ እንደማለት ነውና ይህ የሚታሰብ አይመስለኝም፡፡ “ነገር ከአፍ ሲያመልጥ ፀጉር ሲመለጥ አይታወቅም፡፡” ሰውዬው በሀብት አማላይነት ተሸንፎም ይሁን፣ በሆነ እንትን ነገር ተይዞም ይሁን አንዴውኑ አማራንም ኢትዮጵያንም ክዶ ለሰይጣን አምላኪዎቹ ተንበርክኳልና ኦርቶዶክስ ራሷም በአጋንንቱ ዓለም ባትያዝ ኖሮ ሥልጣነ ክህነቱ ጭምር ተገፎ ገዛው በተባለው ትልቅ ሆቴል ውስጥ አልጋ አንጣፊ ወይንም ቦይ ሊሆን በተገባው ነበር፡፡ ጊዜው ሲደርስ በግልጽ እንነግረዋለን፡፡ ንስሃ የማያጠፋው ይሁዳዊ ታላቅ ጥፋት ነው ያጠፋው፡፡ ክርስቶስም አለ “የሰውን ልጅ አሳልፎ የሚሰጥ የወፍጮ መጅ በአንገቱ ታስሮ ወደጥልቁ ባህር ይጣል፡፡” እውት ነው፡፡ የሚሊዮኖች ነፍስ ይህን አስመሳይ ጳጳስ ነኝ ባይ ፋረዱታል፡፡ የሚቃጠለው የአማራ ሰብል ይፋረደዋል፡፡ የደብረ ኤሊያስ 570 ካህናትና ቀሳውስት ነፍሳት ይፋረዱታል፡፡ በየቀኑ በድሮን የሚያልቀው የአማራ ሕዝብ ነፍስ እሳት ሆኖ ይፈጀዋል፡፡ “ሁለተኛ አማራ አልሆንም” ያለችው ሕጻን ነፍስ ያቃጥለዋል፡፡ …. አሁንም አደግመዋለሁ - ልጅ አይውጣለት፡፡ (የለውም እንዳትሉኝና እንዳታስቁኝ!)

ሲጀመር አንድ ጳጳስ የሚሊዮኖች ብር ኢንቬስትመንት ባለቤት እንዴት ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ መንኮሰ ሞተ ማለት እንደሆነ እንሰማለን፡፡ የሞተ ሰው ታዲያ የመቶ ሚሊዮን ብር ሆቴል መክፈትና ሲሞት ደግሞ አንድ ሚሊዮን ለእገሊት፣ አንድ ሚሊዮን ለእገሌ እያለ ሚሊዮኖችን በኑዛዜ መስጠት ከምን የመጣ ነው? ኢትዮጵያ ለዓለማችን ጉድ ማሳየቷን ቀጥላለች፡፡ ጳጳሣቷ ጉድ እያፈሉ ነው፤ ካህናቷ በብልጭልጩ ዓለም ጠፍተው በጎቿን በተኩላና ቀበሮ እያስበሉ ነው፡፡ ልጅ አይውጣላቸውና አሁንስ በጣም አበዙት፡፡ በቀደም ለት የሞተው ጳጳስ እኮ ነው ደግሞ በአሥር ሚሊየኖች ለሚፈልጋቸው ሰዎች ተናዞ የሞተው፡፡ ቅሌታሞች!

ፋኖ ጠንቀቅ በል፡፡ የሃይማኖት አባት የለም፡፡ ታቦትና መስቀል በሰይጣን እጅ ገብቷልና አይሠራም፡፡ ቄስ የለም፡፡ ሁሉም ለዲያቢሎስ ሰግዷልና ትክክለኛው የሃይማኖት አባት እስኪገኝ ድረስ አጭርባሪን ጳጳስና ቄስ እግር እግሩን እያልክ ዶሮ ጠባቂ አድርገው፡፡ የአቢይ ተላላኪ ሁላ ዋጋውን ካላገኘ ኢትዮጵያ አትነሳም፤ አማራም ያበቃለታል፡፡ በቃ፡፡ ጊዜው ሰይጣን የሰለጠነበት ነውና ለሰይጣንም ዕድል ተሰጥቶታልና ሁላችንም በያለንበት እንጠንቀቅ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ቀድሞ ጨርሶታል - “ንቁም በበኅላዌነ እስከ ንረክቦ ለአምክነ፡፡” በማለት፤፤ በቅርቡ ቸር ያሰማን፡፡ እንሰማለንም፡፡ እንዲህ ሁሉንም ያንቀዠቀዣቸው ማብቂያቸው መድረሱን አባታቸው ስለነገራቸው ነው፡፡
https://amharic-zehabesha.com/archives/187340
ከገዛ ራሳችን ግዙፍና መሪር እውነታ እየሸሸን ሃይማኖትን መደበቂያ የማድረጉ አስቀያሚ እኛነታችን ይብቃን!
November 23, 2023

ጠገናው ጎሹ

እንደ ሰው በሰላም ለመወለድ ፣ ለማደግ፣ ለመኖር ፣ ለመማር እና የእውቀትና የክህሎት ባለቤቶች ለመሆን እድሉ ቢሰጣቸው እንኳንስ አንድ ወይም ሁለት ወይም ሦስት ቤተ ርስቲያን ወይም ገዳም ወይም መስጊድ መላ አገራቸውን የወርቃማ ህይወት ወይም አኗኗር ባለቤት ሊያደርጉ የሚችሉ አያሌ ሚሊዮን እምቦቃቅላዎች (ህፃናትና ታዳጊዎች) የገዛ አገራቸው ምድረ ሲኦል ስትሆንባቸው ፣ አያሌ ሚሊዮን ንፁሃን ዜጎች በገዛ አገራቸውና ቀያቸው መፈጠርን (ሰው መሆንን)  የሚያስጠላ ወይም “ምነው ሰው ሆነን ባልተፈጠርን” የሚያሰኝ  እጅግ መሪር ፈተና ሲያ ጥማቸው ፣ አያሌ ሚሊዮን አማኞች በባለጌና ጨካኝ የጎሳ አጥንት  ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ዘዋሪዎች እና በአድርባይ (በምንደኛ) የሃይማኖት መሪዎች ተብየዎች እጅግ  አስቀያሚ መተሻሸት ግራ የሚያጋባ ብቻ ሳይሆን በእጅጉ ልብን የሚሰብር ሲሆንባቸው  ፣  የሃይማኖት አገልጋዮችና ተከታዮች ፈጣሪን የሚማፀኑባቸው ቤተ እምነቶችና አንጡራ (መተኪያ የሌላቸው)  ህይውቶቻቸው (ህልውናዎቻቸው) የጨካኝ ገዥዎች ሰይፍ ዒላማዎች ሲሆኑባቸው፣

ህልውናን ከባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች የመከላከልን እርምጃ  ለሁሉም ዜጎች የምትበጅ የጋራ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን  እውን  ከማድረግ ታሪካዊና የተቀደሰ ዓላማ ጋር ይዘው የተነሱና ለዚሁም ሊተካ የማይችለውን ህይወታቸውን ጨምሮ እጅግ ከፍተኛ መስዋእትነት በመክፈል ላይ የሚገኙትን ወገኖች የሚደግፍና የሚበረታታ ህብረተሰብ እንደ ወንጀለኛና ሃጢአተኛ ተቆጥሮ  የርካሽ ፕሮፓጋንዳና የጭካኔ ርምጃ ሰለባ ሲሆን እና ፣  በአጠቃላይ ትውልዳዊው የመከራና የውርደት ቸነፈር  ለማመን ቀርቶ ለማሰብም በሚከብድ ሁኔታ እየሰፋና እየከፋ ሲሄድ በእውነተኛ የአርበኝነት (ጊዜና ሁኔታ በማይሽረው የወገንንና የአገር አፍቃሪነት) ስሜት የሚከታተልና የሚገነዝብ የአገሬ ሰው  ከዚህ የበለጠ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረትና ርብርብ የሚጠይቅ አገራዊ ጉዳይ እንደሌለና እንደማይኖር በፅዕኑ ያምናል የሚል ፅዕኑ እምነት አለኝ። አለመታደል ወይም የፈጣሪ ቁጣ ሆኖብን ሳይሆን ከየትኛውም ጊዜና ሁኔታ የከፋና የከረፋ የተረኛና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ዘዋሪዎችን እንደ ማህበረሰብ ወይም እንደ ህዝብ የጋራ በሆነና በጋራ በሆነ የአንገዛም ባይነት ተጋድሎ በቃችሁ ለማለት ባለመቻላችን የመከራው ጊዜና አስከፊነት እየተራዘመ ነውና ከመቸውም ጊዜና ሁኔታ በበለጠ ሊያሳስበንና ሊያስቆጣን ይገባል።

አዎ! ምንም እንኳ ይበል (እሰየው) የሚያሰኝ በመላው አገርና ወገን ወዳድ ወገኖች (ዜጎች) የተደገፈና የታገዘ እና የግፍ ፅዋ አስከፊነት የወለደው የአማራ ፈኖዎች ተጋድሎ እያየን መሆኑ እውነት ቢሆንም ይበልጥ የተራዘመ ጊዜን መውሰድ የሌለባቸውና በእጅጉ የተጠነከሩ እና ወደ ኋላ የማይመለሱ የትጥቅ ትግልሎችን ፣ የፖለቲካ ጥበቦችን  እና የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረቶችንና የጋራ ርብርብቦችን የሚጠይቁ  ሥራዎች እንዳሉብን ለአንዳፍታም መዘናጋት አይኖርብንም።

ለዚህ ነው በሃይማኖት ስም እየማሉና እየተገዘቱ ፈጣሪ “ከማነኛውም ቤተ መቅደስ በላይ ቤተ መቅደሴ ነው” የሚለው ህዝበ አዳምና ሔዋን  በባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች እና በግብረ በላዎቻቸው ለመግለፅ በሚከብድ ሁኔታ እየፈረሰ (እየተደረመሰ)  ባለበት በዚህ መሪር እውነታ ወቅት በባህር ማዶ እንገነበዋለን ለሚሉት "ታሪካዊ" የቤተ ክርስቲያንና የገዳም  ፕሮጀክት “አያሌ ሚሊዮን ዶላር ካልሰጣችሁን የፅድቁ በር ይዘጋባችኋል ” ለሚል እጅግ የወረደና አዋራጅ  ዘመቻ ተውኔት የቀድሚያ ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው ሌት ተቀን ዶላር የሚለምኑትን (የሚሰበስቡትን) ወገኖች ቢያንስ በግልፅ ቋንቋ ነውር ነው ማለት ከተገቢም በላይ ተገቢ የሚሆነው።

አዎ! እየተነጋገርን ያለነው በእውነት ስለ እውነት ከሆነ ለተንቦረቀቀ የግልና የቡድን "ብልፅግና" ማሳለጫነት በሚገለገሉበት ማህበራዊ  ሚዲያ ህዝበ አማኙ ከሰው ሠራሽ (ከፖለቲካ ሠራሽ) መከራና ሰቆቃ ሰብሮ ይወጣ ዘንድ ታላቅ ሚና ያለውን ታላቁን መጽሐፍ (መጽሐፍ ቅዱስን) መሬት ላይ ከሆነውና እየሆነ ካለው ግዙፍና መሪር እውነታ ጋር ፈፅሞ በማይገናኝ አኳኋን እየጠቀሱና እያነበነቡ “ባህር ማዶ ቤተ ክርስቲያንና ገዳም ዛሬውኑ ካላሠራን የሲኦል እራቶች (ሰለባዎች) መሆናችን ነው” በሚል እጅግ ግልብና አሳሳች በሆነ እና መከራን ይበልጥ በሚያራዝም ዘመቻ ላይ የተጠመዱ ወገኖችን አሁንም አደብ ግዙ ማለት የግድ ነው።

ሰሞኑን ከወደ ኳታር እየታዘብነው ያለውነው የሶሻል ሚዲያ ሽር ጉድ፣ መነባንብ፣ ዝማሬ፣ እልልታ ፣ የመጽሐፍ ቅዱስና የትውፊት ጥቅስ ጋጋታ፣ ግልብና የተሳከረ አዋቂዎችና ታዋቂዎች ነን ባይነት፣ ወዘተ የሚነግረን ቁም ነገር ቢኖር በገዛ ምድራችን (በገዛ አገራችን) ለዘመናት ከሆነውና እየሆነ ካለው እጅግ ግዙፍና መሪር እውነታ እየሸሸን ባህር ማዶ እናሠረዋለን በምንለው ቤተ ክርስቲያንና ገዳም ዘመቻ ስም የምናካሂደውን  እጅግ የተንሸዋረረ አስተሳሰባችንና አካሄዳችን ነው።

አሁንም የሰበብ ድሪቶ እየደረትን ከመሪሩ እውነታ ለመሸሽ ካልፈለግን በስተቀር ከተሰጣቸው ሃይማኖታዊ ሃላፊነትና ተልእኮ ከፍተኛነት አንፃር ሲገመገም ከሲኖዶሱ አባላት የሚጀምረው አስከፊና አስፈሪ ውድቀት ብዙ የሚያነጋግረን እየሆነ መጥቷል።መናገርና መነጋገርም አለብን።

ቀኖና እና ዶግማ እያሉ ሲሰብኩን (ሲያስተምሩን) የኖሩት የሃይማኖት መሪዎች ራሳቸው አፍርሰውና እያፈረሱ እረኞቻችሁ ነን ከሚሉን ጳጳሳትና ሊቀ ጳጳሳት መካከል አንዱ የሆኑት አቡነ ኤርምያስ ይህን ሰሞን የገቡበት እጅግ ከባድ ወለፈንዲነትና የተምታታ አስተሳሰብም (highly hypocritic and delusional way of thinking) የዚሁ አጠቃላይ ውድቀታችን አካል መሆኑን የማይረዳ ባለቅንና ሚዛናዊ ህሊና ባለቤት ወገን ከቶ የሚስተው (የሚያጣው) አይመስለኝም ።

ሁለት ፈፅሞ የሚቃረኑ እውነታዎችን ማለትም በአንድ በኩል ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖችን (መንግሥት ተብየውን) እና በሌላ በኩል ደግሞ ከዘመን ጠገብ መከራና ውርደት ለመላቀቅ እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ የሚያደርገውን ህዝብ (በፋኖ ሃይሎች የሚመራውን ተጋድሎ) የገለፁበትና ያስቀመጡበት ሁኔታ ከለበሱት ልብሰ ሊቀ ጳጳስ እና ከያዙት መስቀል በስተቀር የእውነተኝነት (የአርበኝነት ) የሃይማኖት መሪነትን ወይም የህዝብ እረኝነትን ፈፅሞ አያንፀባርቅም።

ይህ ቀጥተኛና ግልፅ ሂሳዊ አስተያየቴ የሚያስደነግጣቸው ወይም እግዚኦ የሚያሰኛቸው የዋህ አማኝ ወገኖች ቁጥር የትየለሌ እንደሚሆን በሚገባ እረዳለሁ ። ወደድንም ጠላንም መሬት ላይ ያለው ግዙፍና መሪር እውነታ ይኸው ነውና እውነተኛ ክርስቶሳዊያን ነን የምንል ከሆነ የሚሻለው ሃየገዛ ራሳችንን መሪር ሃቅ  መጋፈጥ እና  ዘወትር በውድቀት አዙሪት ውስጥ ከመጓጓጥ (ከመማቀቅ) የሚገላግለንን ሥራ መሥራት ነው እንጅ ሃላፊነቱንና ተልእኮውን ያልተወጣና የማይወጣ የሃይማኖት መሪ ለምን ይተቻል በሚል እግዚኦ ማለትና ሃጢአት ያልሆነውን ሃጢአት እያስመሰሉ ፈጣሪን ጨምሮ ኢምክንያታዊና ጨካኝ በትር የሚያነሳ ማስመሰል ፈፅሞ ትክክል አይደለም።

ሊቀ ጳጳሱ በብዙ የሚዲያ መስኮቶች ቀርበው “ትክክለኝነታቸውን” ለማፅናት ያደረጉት ጥረት ትዝብትን እንጅ አድናቆትን አላስገኘላቸውም። የፀፀትንና የይቅርታን ታላቅ ሰብአዊ እሴትነት አዘውትረው የሚሰብኩንን ያህል ባይሆንም እንኳ አንፃራዊ በሆነ የሞራል ከፍታ “አዎ! ልጆቼ አወንታዊ ንግግሬ እንደተጠበቀ ሆኖ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ስህተቶችን በመሥራቴ መልካም አርአያነት ጎሎኛልና ይቅርታ እጠይቃችኋለሁ” የሚያሰኝ ወኔ የማጣታቸው ጉዳይ በእጅጉ ያሳዝናል። ማሳዘን ብቻ ሳይሆን በእጅጉ ያሳስባልም።

አሁንም ይህንን ለማለት የሚያስችል ወኔ አምጦ በመውለድ ይቅርታ ጠይቆ ስህተትን የማረም አርአያነት የሃይማኖት መሪዎች ባህሪና ተግባር መሆኑን ከማሳየት ይልቅ የሰበብ ድሪቶ እየደረቱ በተለመደው የአባትነት እሳቤ የሚቀጥሉ ከሆነ የሚያስከትለው  አሉታዊ ተፅዕኖ በእርሳቸውና በመሰሎቻቸው ብቻ ሳይሆን ታላቅና ታሪካዊ በምንለው ሃይማኖት ላይ ጭምር ነው የሚሆነው። ይህ ደግሞ ሃይማኖቴን አከብራለሁና እጠብቃለሁ ለሚል አማኝ ከባድ ፈተና ነው የሚሆነው።

በእውነት ስለ እውነት ከተነጋገርን ባለጌና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ዘዋሪዎች (አራጊና ፈጣሪ ቡድኖች) በሥልጣነ መንበር ላይ እየተፈራረቁ አደንቁረው የገዙትና የሚገዙት አብዛኛው አማኝ ወገን ከፈጣሪ የተሰጠውን ረቂቅ የማሰቢያ አእምሮና ብቁ የማከናወኛ አካል እየተጠቀመ እና የፈጣሪውን እገዛ እየጠየቀ (እየተማፀነ) እንደሰው ሰው ሆኖ የሚኖርበትን ሥርዓተ ማህበረሰብ እውን እንዳያደርግ በሃይማኖት ስም የቅድሚያ  ቅድሚያ ትኩረቱንና የጋራ ርብርቡን ምስቅልቅሉን እያወጡበት ያሉትን ወገኖች ለምንና እንዴት ብሎ ለመጠየቅ ቢሳነው ያሳዝን እንደሆነ ከቶ አይገርምም።

አዎ! በአሁኑ ወቅት እያየነውና እየሰማነው ያለነው እጅግ አስቀያሚና አደገኛ ሁኔታ በአንድ በኩል  ከዘመን ዘመን እየተበላሸ የመጣውን የሃይማኖት መሪዎች  አድርባይነትና አስመስሎ የመኖር አስቀያሚ ባህሪ እና በሌላ በኩል ደግሞ የተረኛ ገዥ ቡድኖችን የጭካኔ አገዛዝ ሰይፍ በመሠረታዊ እውቀትና አቋም በተደገፈ  ማንነትና እንዴትነት ለመጋፈጥና በድል አድራጊነት ለመወጣት  ያለመቻላችን አካል (ውጤት) ነው። ይህንን መሪር እውነታ  አምነንና ተቀብለን ተገቢውን  አድርገን ለመገኘት ዝግጁዎችና ቁርጠኞች ሆነን እስካልተገኘን ድረስ የክስተቶችን የትኩሳት መጠን እየተከተልን በምናውጀው ፀሎት፣ ፆም፣ ምህላ (እግዚኦታ) ፣ ቅዳሴ፣ ዝማሬ፣ ቅኔ (ይህም በትክክል ከተደረገ ነው) የሚመጣ አንዳችም በጎ ለውጥ አይኖርም። ከዚህ እጅግ ፈታኝና አስቀያሚ የመሬት ላይ እውነታ የሚነሳ ግልፅና ቀጥተኛ ሃሳዊ አስተያየቴን የሃይማኖት አባትን እንደመዳፈርና የሃጢአት ወይም የሰይጣን  መንገድን እንደመምረጥ  የሚቆጥሩ ወገኖች ቁጥር የትየለሌ እንደሚሆን በሚገባ እገነዘባለሁ። ይህም ለምን? እንዴትና ወዴት? ብሎ ለመጠየቅ የሚያስችል መሠረታዊ እውቀት እንዳይኖረው  ከተደረገ (not well informed ) አማኝ  የሚጠበቅ ነውና አይገርምም። የሚገርመው ቢያንስ ፊደል ቆጠርኩ የሚለውም ከዚሁ  የአስተሳሰብ ጉድለት ሰብሮ በወጣ አማኝነትና ተከታይነት  ሃይማኖቱንና አገሩን ለመታደግ ትርጉም ያለው ሥራ ለመሥራት አለመቻሉ ነው።

የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረትንና ርብርብ የሚጠይቀውን እና ፈጣሪም የሚፈልገውን የአገርና የህዝብ ጉዳይ እንደሌለ ቆጥሮ “ባህር ማዶ ለምንሠራውና ለምናሠራው ድንቅና ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን ወይም ገዳም ዶላር ስጡን” የሚልንና እንቅልፍ የሚያሳጣን ዘመቻ የሚባርክ እውነተኛ አምላክ ሊኖር እንደማይችል ለማወቅ ነብይ ወይም የሃይማኖት ሊቀ ሊቃውንት መሆንን አይጠይቅም። የሚጠይቀው እውነተኛ (ክርስቶሳዊ) አማኝነትን፣ ቅንና አስተዋይ ህሊናን፣ ሚዛናዊና ትውልድ ተሻጋሪ የፖለቲካ ሰብእናን ፣ የሞራልና የሥነ ልቦና ልእልናን ፣ ተንቦርቃቂ (ልክ የሌለው) የግልና የቡድን ፍላጎትን የመቆጣጠር ፈቃደኝነትንና አቅምን ፣ ወዘተ ብቻ ነው። ይህንን እጅግ መሠረታዊና ጊዜ ሊሽረው የማይገባው እሴት  ነው እጅግ አብዛኛው ፊደል የቆጠረ የማህበረሰብ አካል የሳተውና እየሳተው ያለው።

 እናም፦

ይህ መከረኛ ህዝብ ከሚገኝበት እጅግ ግዙፍና መሪር ሁኔታ በሰብሮ ለመውጣት ይችል ዘንድ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረትንና ርብርብን በሚቻለው መጠንና አይነት ሁሉ ከማገዝ  ይልቅ ፦

ሀ) ባህርና ውቅያኖስ እያቋረጡ በመብረር “ይህንን ያህል ገንዘብ (ዶላር)  ቀርቶናልና   ይህንኑ  ብታመጣ  (ብትሰጥ)  የመንግሥተ  ሰማያት  መግቢያ  ቁልፍን   ትረከባለህ”  የሚሉትን  የሃይማኖት ተቆርቋሪ ተብየዎች  አደብ ግዙ ብሎ በግልፅና በቀጥታ ለመንገርና ለመነጋገር የሚቸገር አማኝ የስም ወይም የተለምዶ አማኝ እንጅ እውነተኛ ክርስቶሳዊ አማኝ ሊሆን ከቶ አይችልም። አዎ!  ይህ መከረኛ ህዝብ "ከሁሉም የምትበልጡ ቤተ መቅደሶቸ  እናንተው ናችሁ  የሚል ታላቅ ቃል የተገባልንን  ሰብአዊ ፍጡራን   የግፍ ግድያና የቁም ሞት  ሰለባዎች እየሆን ባለንበት እጅግ ግዙፍና መሪር እውነታ ውስጥ  ለባህር እና ለውቅንያኖስ ማዶ ቤተ ክርስቲያን ወይም ገዳም መግዣ፣ ማሠሪያና ማስፋፊያ ካላመጣችሁ በረከትና ፅድቅ ቀረባችሁ  ማለት ፈፅሞ ትክክል እንዳልሆነ ለመረዳትና ለማሳወቅ እስካልቻለ ድረስ ሃይማኖትን ጨምሮ እውን ሊያደርገው የእውነተኛ ነፃነትና ፍትህ ሥርዓት አይኖርም።

በእንዲህ አይነት ፈፅሞ የቅድሚያ ትኩረትንና የጋራ ርብርብ የሚጠይቀውን ጉዳይ ወደ ጎን ትቶ የሚሠራ ቤተ ክርስቲያንና ገዳምን የሚባርክና ማደሪያው የሚያደርግ እውነተኛ አምላክ ፈፅሞ የለምና እነዚህ በሃይማኖት ስም ልክ የለሽ የግልና የቡድን ብልፅግና ቅዠታቸውን እውን ለማድረግ የሚታትሩትን ደካሞች በቃችሁ ማለት የፅድቅ እንጅ የመርገምት መንገድ አይደለም።

ለ) በሥልጣነ መንበሩ ላይ እየተፈራረቁ በህዝብ (በአገር) ላይ መግለፅ የሚያስቸግር የመከራና የውርደት ዶፍ ሲያወርዱ ከኖሩትና እያወረዱ ከቀጠሉት የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማርተኛ ገዥ ቡድኖች ጋር እየተገለባበጡና እየተሻሹ እጅግ ታላላቅና ጊዜ የማይሽራቸው የሃይማኖታዊ እምነት እሴቶችን የሚያጎሳቁሉ የየትኛውም ሃይማኖት ተቋማት መሪዎችን ፣ ሊቃውንትን፣ ሰባኪዎችንና ባለሌላ ማእረግ አባላትን በግልፅና ገንቢ በሆነ አቀራረብ አደብ ግዙና የተጣለባችሁን የእረኝነት ሃላፊነትና ተልእኮ ተወጡ ማለት የእውነተኛ ክርስቶሳዊነት ባህሪና ሃላፊነት ነው።

ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅሞ የትኛውንም ግለሰብ ወይም ቡድን የርካሽ ፖለቲካ ቁማሩ መሣሪያ የማድረግ ጉዳይ  ከዚህ መንግሥት ተብየ አካል  የማይጠበቅ ይመስል ሰሞኑን አቡነ ኤርምያስን መንግሥት እንዳሳሳታቸው አድርጎ ለመከላከል የተደረገውንና የሚደረገውን ጉንጭ አልፋ እመኑን ባይነት ቢያንስ በግልፅና በቀጥታ ነውር ነው ለማለት የሞራል አቅም ካጣን ስለየትኛው የተሟላ ነፃነት እንደምንናፍቅና እንደምንሰብክ ለመረዳት በእጅጉ ያስቸግራልና ዙሪያውን ከመዞር ሃቁን እናጋፈጥ። በነፍስም ሆነ በሥጋ የሚበጀን ይኸውና ይኸው ነውና ።

የሊቀ ጳጳሱ አስቀያሚ ወለፈንዲነትን (ugly paradox) አባል ከሆኑበት ሲኖዶስ አስነዋሪና አሳሳቢ ውድቀት ነጥሎ ለማሳየት መሞከር እና እንኳንስ በሊቀ ጳጳሱ ደረጃ  ለማነኛውም አስተዋይና ሚዛናዊ ህሊና ላለው ተራ የአገሬ ሰው ግልፅና ግልፅ የሆነውን የአገራችን መሪር እውነታ ከእውቀት ማነስ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን መከጀል ከስህተት ላይ ስህተት መሆኑን በግልፅና በቀጥታ መንገርና መነጋገር የግድ ነው።

ሊቀ ጳጳሱ በህወትና በብልፅግና (ለሁለት በተሰነጠቀው ኢህአዴግ መካከል) በተካሄደው ጦርነት ጊዜ እዚያው ይኖሩበት ከነበረው ህዝብ ጋር መቆየታቸውና የሚችሉትን ማድረጋቸው ከአንድ የሃይማኖት መሪ የሚጠበቅ አነስተኛው ሃላፊነትና ተልእኮ ሆኖ ሳለ  በአግባቡ እውቅና ከመስጠትና ከማበረታት አልፎ የሰማእትነት ገድል እንደፈፀሙ አድርጎ መለጠጥ የሚነግረን ቁም ነገር ቢኖር   የሃይማኖት መሪን ጨምሮ የትኛውም በሃላፊነት ላይ የተቀመጠን ሰው ወይም አካል እንደ አማኝ ወይም እንደ ተከታይ ለምንና እንዴት ብሎ ለመጠየቅ ያለመቻላችን ደካማነት የሚያስከትለውን አሉታዊ ውጤት ነውና ከምር ራሳችንን መጠየቅ እንደሚያሻን ነው። አዎ! በአግባቡ አካፋን አካፋ ማለትን ( to call as it is) ለአባቶች እንደማይሠራ ብቻ ሳይሆን ሃጢአት እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን መሞከር ለሰማያዊውም ሆነ ለምድራዊው ዓለም ፈፅሞ አይበጅምና ለሃይማኖት መሪዎችም ይህንኑ በግልፅና በአግባቡ መንገር ወይም ማሳወቅ የአስፈላጊ ነው።

በአጠቃላይ ከዘመን ጠገቡና በእጅጉ አስከፊና አስፈሪ እየሆነ ከሄደው የገዛ ራሳችን የውድቀት ወይም የቀውስ አዙሪት ሰብረን መውጣት ካለብን በዴሞክራሲ ስም ወንጀል የሚፈፅመውን የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓትን እና ሃይማኖታዊ ሃላፊነታቸውንና ተልእኳቸውን በአግባቡ ከመወጣት ይልቅ ከገዥዎች ጋር እየተሻሹ እጅግ ታላቅ የሆነውን ሃይማኖታዊ እሴት በእጅጉ ፈተና ውስጥ የጣሉትን የሃይማኖት መሪዎችና  ወገኖች  በግልፅ፣ በቀጥታና በአግባቡ በቃችሁ ማለት የግድ ነው።

ለዚህ ደግሞ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለውን እና በአንፃራዊነት ከየትኛውም ጊዜ የተሻለ ትርጉም ባለው ሁኔታና ሁሉንም ነፃነትና ፍትህ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ በማያገል አኳኋን እየተካሄደ ያለውን የፋኖ ተጋድሎ ይበልጥ አሳማኝና አገራዊ የማድረጉ ጉዳይ ልዩ ትኩረትንና የጋራ ርብርብን የሚጠይቅ መሆኑን አምኖ ወደ ፊት መራመድን ይጠይቃል።

ሰላምን የማይፈልግ እና ጦርነት የሚወድ ባለጤናማ ህሊና ሰው ያለ ይመስል ደምሳሳ የሆነ የሰላም ሰባኪነትና የጦርነት አውጋዥነት ዲስኩር  ከቶ የትም አያደርሰንምና  እውነተኛና ዘላቂ ሰላም እንዴትና በነማን እውን ይሆናል? የሚለውን እጅግ ፈታኝ ጥያቄ ወቅቱንና ሁኔታውን በሚመጥን አቋምና ቁመና መመለስ የግድ ነው።

ሰላምና ዴሞክራሲ የሚሰፍንበት ሁኔታ ይፈጠር ዘንድ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ከማድረግ ይልቅ በህዝብና ለህዝብ ተቆርቋሪ በሆኑ ወገኖች ላይ ጨካኝ ሰይፋቸውን መጠቀም ዋነኛ የሥልጣን መቆያና የአገርን ሃብት መዝረፊያ ያደረጉ ባለጌና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ዘዋሪዎችን (አራጊና ፈጣሪዎችን) ለማስወገድ ጦርነት አይቀሬ መሆኑ እየታወቀ ገዳዩንና ተገዳዩን የሰላም ፀሮችና ጦርነት የናፋቂዎች አድርጎ ለመሳል (ለማሳየት) መሞከር   እውነተኛና ዘላቂ ሰላምንና እድገት በፍፁም አያረጋግጥም።  ሃይማኖትን ለዚህ አይነት አተረጓጎም ፣ አስተሳሰብና አካሄድ በሚያመች ሁኔታ እየተጠቀሙ “የሰላምና የፅድቅ  አባቶች ነንና ለምን ከመስመራችን እንድንወጣ ትጠይቁናላችሁ” የሚለው ምሬትና ርግማን ትክክለኛ የሆነ መንፈሳዊም ሆነ ዓለማዊ  ስሜት የለውም።

ከዚህ ግዙፍና መሪር እውነታ እየሸሹ ባህር ወይም ውቅያኖስ ማዶ ለሚሠራ ቤተ ክርስቲያንና ገዳም በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር የመሰብሰብ ተውኔተ ዘመቻ ላይ መጠመድም የእውነተኛ ክርስቲያንነት ባህሪና ድርጊት አይደለምና ልብ ያለው ልብ ይበል!

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/187325
የዕምነት ተቋማት ገለልተኛነት አስከ የት?   
በአንድ ወቅት በ17ኛዉ ክ/ዘመን የፈረንሳይ ንጉስ በዘመኑ ይታተም የነበር ወርኃዊ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መፅሄት “ቤ/ክርስቲያን እናትም ፍቅርም ናት  ”  ቅጂ  ንጉሰ መገስቱ እንዲደርሳቸዉ ይደረግ ነበር ፡፡

በዚህ የ17ኛ ክ/ዘመን ፈረንሳይ በሚያሳስብ ሁኔታ ቸነፈር እና ርኃብ ነበር ተንሰራፍቶ ህዝ ፈረንሳይ እንደ ቅጠል ሲረግፍ ቤ/ክርስቲያኗ ሠማይ ጠቀስ ፎቆችን ስታስገነባ ነበር ፡፡

ይህን የሚያዉቁት ንጉሰ ነግስት በዚያ የመከራ እና ጭለማ ዘመን ሲከነክናቸዉ የነበረዉ የዜጎች ስቃይ እና  የቤ/ክርስቲያን ዝምታ የመፅሄቷን ቅጂ በእጃቸዉ ሲቀበሉ ርዕሱን ቀይሩ ልጆቿ እያለቁ እያላት እና መድረስ ስትችል አይታ የማታይ እናት ስለማትኖር ቤተ ክርስቲያን እናትነቷን ትታለች እና የመፅሄቱን መጠሪያ “ቤ/ክ ፍቅር ናት”ማለት ትችላለች ብለዋል ፡፡

መቸም ፍቅር ይዋል የደር እንጂ እንደነበር አይኖርም እና ፍቅር ፍቅር በሉ እንጂ እናት አትለወጥም በልጆቿ መከራም ቤት አትገነባም እንደማለት ይመስላል፡፡

ዕዉነት ነዉ ወደ እኛ ስናመጣዉ ከቤትም ከአገርም በላይ የሁሉ መስሰሶ እና ማገር የሆነዉ ፣ በአርያ ስላሴ የተፈጠረዉ ፣ ህዝበ አማኒያን ሲሳደዱ ፣ ሲዋረዱ ፣ ሲታረዱ ፣ ሲነዱ እንድ ተራ ነገር በተለያየ ጊዜ እና ቦታ በልዩ ልዩ ሁኔታ ሲወገዱ ለምን እና ለማን የሚል ጠፋ ፡፡

ስንሰማ ድሮ ድሮ ቤ/ከርስቲያን የድሆች መጠጊያ ፣ ማረፊያ እና ዕጉም የሚባልባት እንደነበረች አይካድም ፡፡

ዛሬ ግን ቄሱም ፣መፅሀፉም ….ሆኖ ጭራሽ  የሰዉ ልጂ ለአገርም እና ለኃይማኖትም  እርሾ እና ጭዉ መሆኑ ተረስቶ ከቤተ ከርስቲያንም ከአገሩም እንዲርቅ እና በመሆኑ እንዲጨነቅ ሲሆን ድፍን አስርተ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡

አገር ሲያለቅስ እና በስቃይ ሲመቅስ አይቶ ዝም የሚል የእምነት አባትም ሆነ ተቋም ያየንዉ ዛሬ በአገራችን በኢትዮጵያ ነዉ ፡፡

የቀደሙት አያት ቅድ አያት የዕምነት አባቶች ለአገራቸዉ እና ለህዝባቸዉ ሲሉ የሚያልፈዉን ዓለም ንቀዉ የማያልፈዉን ስም እና ተግባር ለትዉልድ ትተዉ አልፈዋል ፡፡

ዛሬ ላይ አገር እና ህዝብ በመከራ ቋያ ለዘመናት እንደ ገና ዳቦ ሲነድባቸዉ የግል እና የቡድን ምቾት እንጂ የከርስቶስ እና የክርስቶስ በጎች ምናቸዉም አለመሆኑን በሆነዉ እና እየሆነ ባለዉ ሁሉ በምንቸገረኝነት ገለልተኛነትን መርጠዉ  ሠላሳ ዓመት በላይ ሌላ ሠላሳ ዓመት መኖርን ይናፍቃሉ፡፡

ህዝብ እና ቤተ ክርስቲያን የዓምልኮት ምክነያት እንጂ የጥቅም እና የገንዘብ ምንጭ ብቻ እንደሆኑ አድርጎ ስለመከራቸዉ እና ስደታቸዉ አይቶ እንዳላዩ የሚያልፍ እርሱ ቤ/ክስቲያንም ሆኑ ህዘበ ዓማኝ መገልገያ ሆኖ የዕምነት እና ኃይማኖት መሪዎች ተገልጋይ ሆነዉ መቀጠላቸዉ ከኃይመኖታዊ አስተምሮ ዉጭ ስለሚሆን ህዝበ አማኝ የሆነ ሁሉ ከርስቶስ ደካሞችን ሊታደግ እንጂ ክፉወችን እና ኃይለኞችን ሊያበረታታ መሆኑን በማወቅ የዕምነት አባቶች በህዘብ እና አገር ጉዳይ ገለልተኛነት አስከየት ነዉ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡

በጎች በቀበሮ እያለቁ ደምወዝ የሚከፈለዉ ዕረኛ ቢኖር ኢትዮጵያ ዉስጥ እንጂ ከእኛ በቀር ይቅር ፡፡ በጎችን ከቀበሩ መታደግ ባይችል የተኩላ ተባባሪ ላለመሆን አለመትጋት  ደቀመዝሙርነት  ወይስ ጠላትነት ይሆን ፡፡

Allen

አንድነት ኃይል ነዉ !
https://amharic-zehabesha.com/archives/187344
የዕምነት ተቋማት ገለልተኛነት አስከ የት?   
በአንድ ወቅት በ17ኛዉ ክ/ዘመን የፈረንሳይ ንጉስ በዘመኑ ይታተም የነበር ወርኃዊ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መፅሄት “ቤ/ክርስቲያን እናትም ፍቅርም ናት  ”  ቅጂ  ንጉሰ መገስቱ እንዲደርሳቸዉ ይደረግ ነበር ፡፡

በዚህ የ17ኛ ክ/ዘመን ፈረንሳይ በሚያሳስብ ሁኔታ ቸነፈር እና ርኃብ ነበር ተንሰራፍቶ ህዝ ፈረንሳይ እንደ ቅጠል ሲረግፍ ቤ/ክርስቲያኗ ሠማይ ጠቀስ ፎቆችን ስታስገነባ ነበር ፡፡

ይህን የሚያዉቁት ንጉሰ ነግስት በዚያ የመከራ እና ጭለማ ዘመን ሲከነክናቸዉ የነበረዉ የዜጎች ስቃይ እና  የቤ/ክርስቲያን ዝምታ የመፅሄቷን ቅጂ በእጃቸዉ ሲቀበሉ ርዕሱን ቀይሩ ልጆቿ እያለቁ እያላት እና መድረስ ስትችል አይታ የማታይ እናት ስለማትኖር ቤተ ክርስቲያን እናትነቷን ትታለች እና የመፅሄቱን መጠሪያ “ቤ/ክ ፍቅር ናት”ማለት ትችላለች ብለዋል ፡፡

መቸም ፍቅር ይዋል የደር እንጂ እንደነበር አይኖርም እና ፍቅር ፍቅር በሉ እንጂ እናት አትለወጥም በልጆቿ መከራም ቤት አትገነባም እንደማለት ይመስላል፡፡

ዕዉነት ነዉ ወደ እኛ ስናመጣዉ ከቤትም ከአገርም በላይ የሁሉ መስሰሶ እና ማገር የሆነዉ ፣ በአርያ ስላሴ የተፈጠረዉ ፣ ህዝበ አማኒያን ሲሳደዱ ፣ ሲዋረዱ ፣ ሲታረዱ ፣ ሲነዱ እንድ ተራ ነገር በተለያየ ጊዜ እና ቦታ በልዩ ልዩ ሁኔታ ሲወገዱ ለምን እና ለማን የሚል ጠፋ ፡፡

ስንሰማ ድሮ ድሮ ቤ/ከርስቲያን የድሆች መጠጊያ ፣ ማረፊያ እና ዕጉም የሚባልባት እንደነበረች አይካድም ፡፡

ዛሬ ግን ቄሱም ፣መፅሀፉም ….ሆኖ ጭራሽ  የሰዉ ልጂ ለአገርም እና ለኃይማኖትም  እርሾ እና ጭዉ መሆኑ ተረስቶ ከቤተ ከርስቲያንም ከአገሩም እንዲርቅ እና በመሆኑ እንዲጨነቅ ሲሆን ድፍን አስርተ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡

አገር ሲያለቅስ እና በስቃይ ሲመቅስ አይቶ ዝም የሚል የእምነት አባትም ሆነ ተቋም ያየንዉ ዛሬ በአገራችን በኢትዮጵያ ነዉ ፡፡

የቀደሙት አያት ቅድ አያት የዕምነት አባቶች ለአገራቸዉ እና ለህዝባቸዉ ሲሉ የሚያልፈዉን ዓለም ንቀዉ የማያልፈዉን ስም እና ተግባር ለትዉልድ ትተዉ አልፈዋል ፡፡

ዛሬ ላይ አገር እና ህዝብ በመከራ ቋያ ለዘመናት እንደ ገና ዳቦ ሲነድባቸዉ የግል እና የቡድን ምቾት እንጂ የከርስቶስ እና የክርስቶስ በጎች ምናቸዉም አለመሆኑን በሆነዉ እና እየሆነ ባለዉ ሁሉ በምንቸገረኝነት ገለልተኛነትን መርጠዉ  ሠላሳ ዓመት በላይ ሌላ ሠላሳ ዓመት መኖርን ይናፍቃሉ፡፡

ህዝብ እና ቤተ ክርስቲያን የዓምልኮት ምክነያት እንጂ የጥቅም እና የገንዘብ ምንጭ ብቻ እንደሆኑ አድርጎ ስለመከራቸዉ እና ስደታቸዉ አይቶ እንዳላዩ የሚያልፍ እርሱ ቤ/ክስቲያንም ሆኑ ህዘበ ዓማኝ መገልገያ ሆኖ የዕምነት እና ኃይማኖት መሪዎች ተገልጋይ ሆነዉ መቀጠላቸዉ ከኃይመኖታዊ አስተምሮ ዉጭ ስለሚሆን ህዝበ አማኝ የሆነ ሁሉ ከርስቶስ ደካሞችን ሊታደግ እንጂ ክፉወችን እና ኃይለኞችን ሊያበረታታ መሆኑን በማወቅ የዕምነት አባቶች በህዘብ እና አገር ጉዳይ ገለልተኛነት አስከየት ነዉ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡

በጎች በቀበሮ እያለቁ ደምወዝ የሚከፈለዉ ዕረኛ ቢኖር ኢትዮጵያ ዉስጥ እንጂ ከእኛ በቀር ይቅር ፡፡ በጎችን ከቀበሩ መታደግ ባይችል የተኩላ ተባባሪ ላለመሆን አለመትጋት  ደቀመዝሙርነት  ወይስ ጠላትነት ይሆን ፡፡

Allen

አንድነት ኃይል ነዉ !
https://amharic-zehabesha.com/archives/187344
https://youtu.be/Z9Cu_Kgo75E?si=Z4Rkd76yOu6EQHGT

ሕዝባዊ ውይይት በአዊ ዞን | "የቀን ሥራ ሰርቼም ቢሆን ፋኖን እደግፋለሁ" | "ይዛችሁ የለቀቃችሁት ባንዳ አስጨርሶን ነበር"
https://amharic-zehabesha.com/archives/187292

Thursday, November 23, 2023

https://youtu.be/Z9Cu_Kgo75E?si=Z4Rkd76yOu6EQHGT

ሕዝባዊ ውይይት በአዊ ዞን | "የቀን ሥራ ሰርቼም ቢሆን ፋኖን እደግፋለሁ" | "ይዛችሁ የለቀቃችሁት ባንዳ አስጨርሶን ነበር"
https://amharic-zehabesha.com/archives/187292
ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትሩ እንደሚሉት አዲስ "የጋራ ትርክት" አያስፈልጋትም--የታሪክ ምሁሩ ፕሮፈሰር ሃይሌ ላሬቦ
https://youtu.be/K-iK7SugYqo?si=ZkAQU_hyBrVpPnK1

 

ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትሩ እንደሚሉት አዲስ "የጋራ ትርክት" አያስፈልጋትም--የታሪክ ምሁሩ ፕሮፈሰር ሃይሌ ላሬቦ
https://amharic-zehabesha.com/archives/187296
https://youtu.be/6fLsQJ1dN9c?si=Y83AbCvjvZrGiJQ1

 

የአማራ ህዝብ ተበድሏል። ይህ መንግስት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ ነው። እኔ ፋኖን አልወቀስኩም። ይቅርታ እጠይቃለሁ'' ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ
https://amharic-zehabesha.com/archives/187275

Wednesday, November 22, 2023

አቡነ ኤርምያስ ሆይ፣ ቤተክሲያን በክብር የደፋችልወትን ቆብ በክብር ያውልቁ! 
አቡነ ኤርምያስ ሆይ፣ ቅድስት ቤተክሲያን አቡን (ማለትም የሐይማኖት አባት) ያደረገችወት ፍርድ ጠፋ፣ ግፍ ተንሰራፋ፣ ፍትሕ ጎደለ፣ ሕዝብ ተበደለ እያሉ ለተገፉ፣ ለተበደሉና ለተጨቆኑ መዕምኖችወ እንዲጮሁ መሆኑን ለርስወ መንገር አያስፈልግም።  ርዕት ቤተክሲያን መንፈሳዊ አባት ያደረገቸወት በሂወትወ ቆርጠው፣ ለመስዋዕትነት ራስወን አዘጋጅተው፣ ለፍትሕ ርትዕ በመቆም ግፈኞችን ያለ ምንም ፍራቻ አጥበቀው እያወገዙ በመንፈሳዊ መንገድ አጥበቀው እንዲዋጓቸው ነው።

እርስወ እያደረጉ ያሉት ግን በዳይም ተበዳይም እንዳይቀየሙወት ከበዳይም ከተበዳይም ጋረ የቆሙ እያስመሰሉ፣ እንደ ሸማኔ መወርወሪያ እዛና እዚህ እያሉ፣ እርስወን በማይመጥን በሚያሳፍር ሁኔታ መለሳለስና መቅለስለስ ነው።  ልወደድ ባይነት ደግሞ የሐይማኖት አባት ሳይሆን የፖለቲከኛ ባሕሪ ነው።  ስለዚህም የርስወ ተግባር ሙሉ በሙሉ የሚመሰክርብወት የሐይማኖት አባትነት ሳይሆን የፖለቲከኛነት ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ነው።

ሙሉ ፖለቲከኛ በመሆን የሚፈልጉትን ቡድን ሙሉ በሙሉ መደገፍ ሙሉ መብትወ ነው።  የሐይማኖት ካባ ለብሰው የፖለቲካ ደባ የመፈጸም መብት ግን የለወትም።  አለበለዚያ የሐይማኖት አባት በማድረግ ያከበረችወትን ቅድስት ቤተክሲያን ማራከስ ይሆንብወታል።  ስለዚህም እያራከሷት ያሉት ቅድስት ቤተክሲያን አውግዛወት የደፋችልወትን ቆብ ሳታወልቅበወት በፊት እስወ ራስወ በገዛ እጅወ እንዲያወልቁት ይመከራሉ።  በወያኔና በኦነግ የተዋረደቸው የቅድስት ቤተክሲያን ልዕልና እርስወ ከሚገምቱት በላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተቃረበ ስለሆነ፣ ቆብወን በገዛ እጀወ አውልቀው የቀረቸወትን እንጥፍጣፊ ክብር ለመጠበቅ ያለወት ጊዜ በጣም አጭር ነው።  ሳይመሽ ገሽሽ ይበሉ።

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 
https://amharic-zehabesha.com/archives/187255

Tuesday, November 21, 2023

የፋኖ ቀበሮዎች ስብሰባ በዛምበራ!
በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ዛምበራ አፉን እንደተቆጣ አንበሳ በከፈተው የዓባይ ሸለቆ እንደ ምላስ የተዘረጋ ቆላማ ሥፍራ ነው፡፡ ዛምበራ ሽፍቶች በልጅግ፣ ምኒሽር፣ ዲሞትፌር፣ ራስማስር፣ ጓንዴና እናት አልቢን እያቀማጠሉ እንደ አንበሳ የሚጎማለሉበት አገር ነው፡፡ ዛምበራን ከሸበል፣ ከጉባያና ከደራ አፋፍ ቁልቁል ሲያዩት ሜዳ ከሱሃና ከአባይ ሽቅብ ሲመለከቱት ግን ተራራ ይመስላል፡፡ ዛምበራን የከደነው ሰማይ አድማሱን ከሸበል፣ ከየጉባያ፣ ከደራ፣ ከደጀንና ከጎሐጽዮን ዳገት ስለዘረጋ ከዛምብራ ወጥቶ ለማያውቅ የዓለም መጀመሪያም ሆነ መጨረሻ የዓባይ ሸለቆ ይመስለዋል፡፡ የዛምበራን ሰማይ እንደ ግርግዳ ቀጥ አርገው የያዙት የዓባይ ጋራዎች ከጫካውና ከገመገሙ ተዳብለው ዛምበራን ግርማና ሞገስ እንደ ብልኮ አልብሰውታል፡፡ ግርማና ሞገስን የለበሰው ዛምበራ እንደ ጦቦያ ገዳማት የሚያስፈራ ክብርን ተጎናጽፏል፡፡ አስፈሪ ክብር የተጎናጸፈው ዛምበራ ያምስቱን ዘመን ፋኖዎችና ኢፍትሐዊነትን የታገሉ  የሸበል፣ የበረንታ፣ የጉባያ፣ የጫቃታና የደራ ሽፍቶች በክብር ሲያስተናግድ ኖሯዋል፡፡

ለጀግኖች ምሽግና ለባህታውያን መጠለያ ጉድጓድ የሚቆፍሩት ቀበሮዎች የዛምበራን ታሪካዊነት ግምት ውስጥ በማስገባትና አለክላኪው ውሻም እንደ ዛምበራ ካለ ቆላ ሊያጠቃቸው እንደማይችል በመገንዘብ አመታዊ ስብሰባቸውን በዛምበራ ለማድረግ ከሞያሌ እስከ ቀይ ባህር፣ ከኦጋዴን እስከ አሶሳ፣ ከሁመራ እስከ ባሌ፣ ከአሰብ እስከ ጋምቤላ ተጠራርተው የበጋው ሙቀት የሚያከትምበትንና ወንዞች የማይሞሉበትን ወራት መርጠው ግንቦት አስራ አምስት ቀን ሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት ከተው ገብተዋል፡፡

የሁለት ሺ ሰባቱ ስብሰባ ያተኮረው በውሻና ውሻን መሳይ ሰዎች በሚፈጽሙት የቀበሮን ዘር የማጥፋት ዘመቻ ላይ ነበር፡፡ የቀበሮን ዘር ለማጥፋት ስለሚፈጸመው ዘመቻ ትምህርት ከሰጡት አያሌ የቀበሮ ምሁራን፣ የሃይማኖት መሪዎችና የጦር መኮንኖች መካከል የተከበሩ መጋቢ ብሉይ ዓይነኩሉና ክቡር ጄኔራል መከተ ደመላሽ ይገኙበታል፡፡ እንደሌሎች የስብሰባ ቀኖች ሁሉ ትምህርቱ ከመጀመሩ በፊት በውሾች የሰላ ጥርስ በመዘንቸር፣ በውሻ መሳይ ሰዎች በተተኮሰ ባሩድ በመቆላት፣ በእስር በመንገላታት፣ የሚያመክን መድኃኒት በመዋጥ፣ በቅያቸው በመፈናቀል፣ ለስደት በመዳረግ፣ ለርሃብ በመጋለጥና በበሽታ በመነደፍ ላለቁት ቀበሮች የሚደረገውን የመክፈቻ ጸሎት ለመምራት ቄስ ወልደ አማኑኤልና ሼህ ሙዴሲር ወደ መንበሩ ወጡ፡፡ እነዚህ የሃይማኖት አባቶችም "ይህንን የተባረከ ስብሰባ በጸሎት መክፈት የነበረባቸው የቀበሮ ሲኖድና መጅሊስ አባላት ነበሩ፡፡ ዳሩ ግን ለጊዜያዊ ምድራዊ ቅንጦት ሳስተው ዘላለማዊውን እግዚአብሔርን፣ እውነትን፣ ፍትህንና ሰፊውን ቀበሮ ከድተው ከውሾችና ውሻ መሳይ ሰዎች ጋር ተሰልፈዋል፡፡ ይህንን ክህደት አጢነው የሚፈርዱ አምላክና ታሪክ ስላሉ ፍርዱን ለነሱ እንተዋለን!" ብለው ስብሰባውን በጸሎት ከከፈቱ በኋላ መንበሩን ለመጋቢ ብሉይ ለቀቁ፡፡

መጋቢ ብሉይ ከአንገት እስከ እግር አንጓቸው የሚሸፍን ከጥቁር ለምድ የተሰራ በርኖስ ለብሰዋል፡፡ በትምህርት ያሳለፉትን ዘመንና የእውቀታቸውን ጥልቀት የሚያመለክት ሻሽ አውሎ ነፋስ አስመስለው ጠምጥመዋል፡፡ መጋቢ ብሉይ ማእረጋቸውን ያገኙት በካድሬ ደፍተራነት እንዲያገለግሉ ከካንቦ ተመልምለው ከድንጋይ ማምረቻው መንፈሳዊ ኮሌጅ ሰልጥነው አይደለም፡፡ መጋቢ ብሉይ ዓይነኩሉ የመጋቢ ብሉይ ማእረግ የተሰጣቸው ለማእረጋቸው የሚመጥን እውቀት ያካበቱና ሃይማኖታዊ ሥርዓትንም የጠበቁ አባት ስለሆኑ ነው፡፡ መጋቢ ብሉይ ቅኔ እንደ ዶፍ ከሚወርድባቸው ዋሸራ፣ ዲማ፣ ደብረ ወርቅ፣ ጎንጅ፣ የገወራ፣ ዋድላና ድለንታ፤ ዜማ እንደ አባይ ወንዝ ከሚፈስባቸው የጎንደር አድባራት የሃይማኖት ትምህርትና ፍልስፍናን ቀስመዋል፡፡ አእምሯቸውን በቅኔና በዜማ አስልተው የብራና መጻሕፍት ፈትሸዋል፡፡ ደብረሊባኖስ ገዳም ዘልቀውም እንደ ቀሲስ አስተርአየ አንድምታውንና መጽሔፈ ትርጓሜውን እንደ ሸንኮራ አገዳ እምሽክ አርገው በልተዋል፤ በብሉይ ኪዳንም ምርምር አድርገዋል፡፡ መጋቢ ብሉይ በመስቀላቸው ሶስት ጊዜ አማትበው "ምንትስ ምንትስ" ብለው በግዕዝ ተናገሩና መልሰው ባማርኛ "በመልካም እንዳስጀመረ በመልካም ያስጨርሰን፤ ያዝ ተሚል ሆዳም ሰውና ያዝ ሲሉት ተሚናከስ ውሻ ይጠብቀን" ብለው ማስተማሩን ጀመሩ፡፡

"የጀመርያው ፊደል ማን ይባላል?" ብለው ጠየቁ "ሀ" አለ ተሳታፊው፡፡ "የመጨረሻውስ?" ብለው ሲጠይቁ "ዜድ" አለ አንድ ከቱሪስት በርገር ሲቀበል የኖረ የባሌ ቀበሮ፡፡ "ምርቱን ተግርድ አትቀላቅል" ብለው መጋቢ ብሉይ እንደ ማንኛውም ካህን በኃይለ-ቃል ሲገስጹ ተሰብሳቢው "የእኛ ካህኖች ነገር!" አለና አፉን ይዞ መሳቅ ጀመረ፡፡ "ፐ" አለች አንድ የት እንደተቀመጠች የማትታወቅ ቀበሮ፡፡ "አዎ ፐ! የመጀመሪያውን ሳያውቁ የመጨረሻውን ማወቅ ይቻላል?" ብለው ሲጠይቁ ጥቂቱ "አይቻልም!" ሲል አብዛኛው ለምን ይህንን እንደጠየቁ ስላልገባው ማጉረምረም ጀመረ፡፡ "መሰላል ሲወጡ የመጀመሪያውን አግዳሚ ዘለው የመጨረሻውን ሊረግጡ ቢቃጡ ምን ይከተላል?" ብለው ሲጠይቁ "መንጠር!" አለ ተሳታፊው በአንድ ድምጥ፡፡ "እርግጥ ነው የመጀመሪያውን አግዳሚ ሳይረግጥ ተመጨረሻው ሊንጠለጠል እሚሞክር እንደሚነጥረው፣ ራሱን ሳያውቅ ሌላውን ለማወቅ እሚከጅልም እንደ ኳስ ነጥሮ ይንከባለላል፡፡ ስለዚህ ኦሜጋን ተማወቅ በፊት አልፋን፣ ሌላውን ተማወቅ በፊት ራስን ማወቅ ይበጃል!" እያሉ ሲያስተምሩ ብዙው ሚስጢሩ ስላልገባው ላጨበጨቡበት ቤትና ደመወዝ እንደሚሰጣቸው "የጦቢያ እንደራሴዎች" ማንቀላፋት ጀመረ፡፡

"ተገዳማትና ተዋሻዎች የመጣጭሁ እስቲ ይህንን መልሱ! የቅዱሱ መጽሐፍ አልፋ ምን ይባላል?" ብለው ሲጠይቁ እንደ አባ መላኩ ከመማር መጠምጠምን ያስቀደመ ጠብደል የቀበሮ  ካህን ከመጽሐፈ-ንዋይ!" አለ "አንተ ተዚያ...ማነው አምጡልኝ.. ጳውሎስና ያኛው በቅርቡ አምጥተው ያለሙያው የጎለቱት ጉልቻ ደሞ ማነው ማ... ማትያስ አህያውንም መጋዣውንም ተከተቱበት ሲኖድ እንጅ ተገዳም የመጣህ አይመስለኝም!" ሲሉ ሆድ ያባውን ብቅል ያዋጣዋል እንደሚባለው ተሳታፊው ሁሉ የታዘበው ጉዳይ ስለነበር "መጽሐፈ-ንዋይ ካሉት ቀበሮ በቀር ሁሉም መፋቂያ ያልነካውን ጥርሱን እያሳዬ ተንተከተከ፡፡ ሳቁ በረድ ሲል "የኔታ ቅዱሱ መጽሐፍ ተዘፍጥረት ይጀምራል!" አለ አንድ ፊቱ በፆምና በጸሎት የተሰረጎደ የላሊበላ ቀበሮ፡፡"ትክክል የመጽሐፍ ቅዱስም የዓለምም አልፋ ዘፍጥረት ነው" ሲሉ አረጋገጡ መጋቢ ብሉይ፡፡ መጋቢ ብሉይ በሶቅራጥስ የማስተማር ዘዴ የሰለጠኑ ይመስል በጥያቄ መልክ ማስተማራቸውን ቀጠሉ፡፡ "በመጀመሪያውና በሁለተኛው ቀን ምን ተፈጠረ?" ብለው ሲጠይቁ " ሰማይና ምድር፣ ብርሃንና ጨለማ " አለ ተሳታፊው፡፡ "በሶስተኛው ቀንስ?" " አትክልት"  "በአራተኛው ቀንስ? "ከዋክብት" "በአምስተኛው ቀንስ? "ወፎችና ሌሎችም ፍጥረታት፡፡" አለ ተሳታፊው፡፡ "በስድተኛው ቀንስ?" ብለው ሲጠይቁ "በስድስተኛው ቀን መናጢው ሰው ተፈጠረ!" ብሎ ተሳታፊው ሲመልስ "የእንሽርት ውኃ ሆኖ በቀረ ኖሮ!" ስትል ጮኸች ሁለት ልጆቿን ሰው ያዝ ብሎ በውሻ ያስበላባት ቀበሮ፡፡

"እንግዲህ ቀበሮ የተፈጠረው በስንተኛው ቀን መሆኑ ነው?" ብለው መጋቢ ብሉይ ከፊት ከተቀመጡት አንዱን ሲጠይቁ አእምሮው እንደ ዘመኑ ወመኔና ከሀዲ ገዥዎች አንጎል የሐሳብ -ሰንሰለት (ሎጅክ) እማይቀበል ስለነበር "በስድስተኛው ቀን" ሲል መለሰ፡፡ "በስድስተኛው ቀን መፈጠርህን በሁለት እግርህ ቆመህ ሁለት እጆችና አስር ጣቶችህን አሳዬና!" ብለው መጋቢ ብሉይ ተሳለቁበት፡፡ "ቀበሮ በአምስተኛው ቀን ተፈጠረ!" ሲሉ መለሱ ብዙ ቀበሮዎች ባንድነት፡፡ "አዎን እኛ ቀበሮዎች የተፈጠርነው በአምስተኛው ቀን ነው፡፡ እሚያሳዝነው አለክላኪው ውሻም የተፈጠረው በዚሁ ቀን ነው" አሉና መሬቱን እያዩ በመተከዝ "እንግዲህ ባፈጣጠር ተሰውና ተቀበሮ ማን ይቀድማል?" ሲሉ ጠየቁ፡፡ "ቀበሮ" አለ ተሳታፊው፡፡ "በዚች ምድር ቀድሞ የታዬው ቀበሮ ወይስ ሰው? "ቀበሮ" ብሎ አብዛኛው ተሰብሳቢ ሲመልስ በቱሪስቶች ሲጎበኝ የኖረ የሰሜን ቀበሮ "ተመራማሪዎች ቀበሮም ሰውም ባዝጋሚ ለውጥ ከትላትል ተፈጠሩ ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡" ሲል አስተያየት ሰጠ፡፡ "እና አንተም የትል ልጅ እንደሆንክ ታምናለህ ማለት ነው? እስቲ ትሉን አንተን አርግና አሳዬን! አያችሁ! ራሱን ሳያውቅ ሌላውን ለማወቅ እሚሻ መጨረሻው ውድቀት ነው ያልነው ለዚህ ነው! የራስን ብራና ሳይገልጡ የሌሎቹን ወረቀት ማነብነብ መጨረሻው ውድቀት ነው! ለማንኛውም እኛ በምናምንበት በፈጣኑም ሆነ ሌሎች በሚያምኑበት አዝጋሚ ለውጥ ብታስበው በዚች ምድር ቀበሮ ከሰው በፊት ታይቷል! አራት ነጥብ!፡፡" አሉ መጋቢ ብሉይ ያራት ነጥብ ምልክት አየሩ ላይ እየሳሉ፡፡

"እንግዲህ በፈጣኑም ሆነ በአዝጋሚው መንገድ ሰው ከምድር የደረሰው በመጨረሻ ተሆነ ምድር ለማን ትገባ ነበር? ቀድሞ ወይስ መጨረሻ ለደረሰው?" ብለው ሲጠይቁ ፡፡ "ቀድሞ ለደረሰው" አለ አብዛኛው ቀበሮ፡፡ "አዎን ምድር ቀድሞ ለደረሰ ትገባ ነበር፡፡ ነገር ግን በኋላ የመጣ አይን አወጣ እንደሚባለው  ሰው በኋላ መጥቶ እኛንም ሆነ ሌላውን ፍጡር እያጠፋ ምድርን ተቆጣጠረ" እያሉ መጋቢ ብሉይ  ሲያስተምሩ አንድ የቀበሮ ካህን ብድግ አለና "ሰው ዓለምን እንዲገዛ ተፈቅዶለታል እኮ" ብሎ ዘሌዋውያን ውስጥ የተጻፈውን እየጠቀሰ ተከራከረ፡፡ "ሰው ዓለምን እንዲገዛ የተፈቀደለት ፈጣሪ ለእውነትና ለፍትህ ይቆማል ብሎ በአምሳሉ በሰራው ጊዜ ነበር፡፡ ሰው ይህንን የተሰጠውን ፀጋ አውልቆ ከሳጥናኤል ጉያ ሲገባ የዓለምን መግዣ ፈቃዱን እንደ ሰካራም መቺና ነጂ ተነጥቋል፡፡ ስለዚህ ሰው እንኳን ዓለምን እንዲገዛ ሊፈቀድለት በጥፋት ውኃና በእሳተ ገሞራ እንዲጠፋ ተደርጓል፡፡ ታጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል እንደሚባለውም የጥፋቱ ውኃምና እሳተ ገሞራው ለኛም ደርሷል፡፡" ሲሉ ሌላ የቀበሮ ሊቅ ተከራከሩ፡፡ በክርክሩ የረኩት መጋቢ ብሉይ "ትክክል መልሰሃል!" ብለው ለሁለተኛው ተናጋሪ አጋርነታቸውን ገለጡና "ለመሆኑ ሰው ወደ ምድር እንዴት እንደወረደ እሚያውቅ አለ?" ብለው ሲጠይቁ "ወገቡን ተጠርንፎ በመሰላል!" አለች አንድ የቀበሮ ወይዘሮ እንደ ዘመኑ ቄሶችና መነኩሴዎች መጋቢ ብሉይን ልታሳስት ተውረግራጊ ሽንጧን እያሳየችና እየተሽኮረመመች፡፡ "ጥሩ ጠላ ጠማቂ ሳትሆኝ አትቀሪም፤ እንደ ብቅል በመሰላል ወረደ ማለትሽ ነው?" ብለው ቀለዱና ፈገግ አሉ፡፡ "ጠላዬን ቢቀምሱማ ሥስት ጊዜ አፍርሶ እንደ ቆመሰው ቄስ ታደሰ ሌላም ያምርዎ ነበር" አለች ወይዘሮዋ በልቧ፡፡ "ሰው ወደ ምድር የተላከው ለልማት ነው!" አለ እንደ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ በቴክኒክ ምክንያት ተነስቶ መናገር ያቃተው ቀበሮ ባለመነሳቱ ይቅርታ ጠየቀና፡፡ መጋቢ ብሉይም "ምንትስ ምንትስ ብለው ግርማ ወልደ ጊዮርጊስን በሚመስለው ቀበሮ ለተራ ቀበሮ እማይገባ እንደ አዋዜ የታሸ ቅኔ ከተቀኙ በኋላ "ይህ የካድሬዎች ስብሰባ ሳይሆን የምሁራን ስብሰባ መሆኑን አትዘንጉ! ጥርነፋ፣ ልማት ቅብጥሶ ቅብጥሶ የሚሉ የኮር አባል ቃላት እያመጣችሁ ውይይታችንን አታቆርፍዱ" ሲሉ ገሰጹ፡፡

"ጥያቄውን አሁንም እደግመዋለሁ! ሰው ለምን ተገነት ወደ ምድር እንደ ቁልቢጥ ተወረወረ?" ሲሉ ጠየቁ፡፡ "ሰው በእባብ አመካኝቶ ከእግዚአብሔር ሆዱን መርጦ አትብላ የተባለውን ፍሬ ስለበላ በእርግማን እንደ ቁልቢጥ ተወረወረ!" አሉ አንድ ኩርምት ብለው የተቀመጡ ቀበሮ በሰነነ ድምጽ፡፡ መጋቢ ብሉይ "ሆዱን ሳይሆን ጭንቅላቱን ሲመግብ የኖረ እንደዚህ የመጽሐፉን ቃል ይናገራል!" ብለው መላሹን ቀበሮ ሲያደንቁ ተሳታፊው አይኑን ጥያቄውን ከመለሱት ኮስማና ቀበሮ አሳረፈው፡፡ "እኒህ ሊቅ እንዳሉት ሰው ወደ ምድር የተወረወረው በእርግማን ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ሰው የተረገመ ፍጡር ነው፡፡ ሌላውን እርኩስ እያለ ይጠራል እንጅ እርኩስ ራሱ ነው፡፡ እርሱ በመረገሙና በመርከሱም ምድር በእሾህና በእንቅፋት ተሞላች፤ በብርድ ተኮማተረች፣ በሐሩርም ነደደች፡፡ ገነት ውስጥ የሰራው ስህተቱ ሳያንሰው ክፋቱን በምድርም ስላበዛው መጀመሪያ በጎርፍ  አጠፋው፡፡ የእርሱ ኃጥያት ለእኛም ደርሶ አብረን ጠፋን፡፡ ኖህ በሚባል ብሩክ ሰው ምክንያት ዘራችን ተርፎ እንደገና አቆጠቆጥን፡፡ የሰው ክፋት ግን ከጥፋት ውኃ በኋላም በመቀጠሉ በገሞራና በእሳት አጋዬው፡፡ በገሞራና በእሳት ጋይቶም ስላልተማረ ኑሮን እንዲያስተምር ልጁን የሰው ሥጋ አልብሶ ወደ ምድር ላከው፡፡ አትብላ የተባለውን ፍሬ በልቶ ወደ ምድር የተወረወረው፤ ስካርን፣ ዝሙትን፣ ውሸትን፣ ክህደትን፣ ስግብግብነት በማብዛቱ በጎርፍ የተጠረገው፤ ከዝሙትም አልፎ ግብረ ሰዶም በመፈጠው በገሞራና በእሳት የጋዬው ሰው ይባስ ብሎ የእግዚአብሔርን ልጅ በሐሰት ከሶ፣ በሐሰት መስክሮና በሐሰት ፈርዶ በእሾህ ከጨቀጨቀ በኋላ በምስማር ከርችሞ ሰቅሎ በጦር ወጋው! እንግዲህ ሰውን በአምሳሉ የሰራውን ክርስቶስን አሰቃይቶ የገደለ ሰው ለቀበሮ ያዝናል ተብሎ ይጠበቃል?" "ከጉረሮ እየሞለቀቀ ህጻናትን በርሃብ የሚጨርስ፣ ቀለሙ ያላማረውን ሰው በኮረንንቲ የሚጠብስ፣ በፈላ ውኃ እሚቀቅል ውሻ መሳይ ሰው ውሻን ያዝ እያለ ቀበሮን ከማስፈጀት ይቆጠባል ተብሎ ይጠበቃል? ብለው ሲጠይቁ "አይጠበቅም" አሉ አይኖቻቸው በእንባ የረጠቡ ተሳታፊዎች በጎረነነ ድምጽ፡፡ መጋቢ ብሉይ እየተንጎራደዱ "እንግዲህ መታገል ያለብንን የእርጉሙን ሰው ተፈጥሮ የተገዘባችሁ ይመስለኛል፡፡ የራሱን ሥጋ እየቆረጠ ከመብላት ከማይመለሰው ውሻ መሳይ ሰውና ውሻ ለመዳን ልባዊ ጸሎትንና የመንፈስ ጽናትን ይጠይቃል፡፡ የመንፈስ ጽናቱን ይስጠን፡፡" ብለው ንግግራቸውን ሲጨርሱ እንደ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ በቴክኒክ ምክንያት መነሳት ካልቻሉት በስተቀር ሁሉም ቀበሮዎች ከመቀመጫው ተነስተው ከሐዘንና እልህ በመነጨ እንባ ተራጩ፡፡

መጋቢ ብሉይ ማስተማራቸውን እንደጨረሱ ተሰብሳቢዎች ነፋስ ተቀብለውና ከስንቃቸው ተቃምሰው ወደ ስብሰባው ሥፍራ ተመለሱ፡፡ ጀኔራል መከተ ደመላሽ በደረታቸውና በትክሻዎቻቸው ኒሻናቸውን እንደ ግርግዳ ፎቶ ሰድረው እየተጀነኑ ከመድረኩ ሲወጡ ተሰብሳቢው ተነስቶ በተደጋጋሚ "በቃ ተቀመጡ! በቃ! በቃ! ተቀመጡ!" እንስከሚባል ድረስ  "ጩዋ..ጩዋ..." እያደረገ ጭብጨባውን አቀለጠው፡፡ ጄኔራል መከተ የቀበሮን ግዛት ለማስከበርና ቀበሮን ለማዳን ብዙ ጀብዱ የሰሩ ሥመጥር ጀኔራል ናቸው፡፡ ጀኔራል መከተ የጀኔራልነት ማእረግ ያገኙት አቶ ኤርሚያስ ፊደል አስቆጥሮ ከአራተኛ ክፍል እንዳስመረቃቸው ተገዳላዮች ያስፈጁትና ያሰቃዩት ሕዝብ ተገምቶ አይደለም፡፡ ጀኔራል መከተ በታወቀ የቀበሮ የጦር አካዳሚ የስድስት ዓመት ትምህርትን በከፍተኛ ማእረግ ያጠናቀቁ፤ በቀበሮ፣ በሰው፣ በውሻ ታሪክና ሥነ-ልቡና በቂ ትምህርት ወስደው ምርምር ያኪያሄዱ፤ በአያሌ የጦር ሜዳዎች የቀበሮ ጠላቶችን ተፋልመው የቀበሮን ግዛት ያስጠበቁ ወታደራዊ መሪ ናቸው፡፡ ጀኔራል መከተ በተለያዬ ጊዜ ቀበሮን ሊያንቁ የመጡ ውሾችን አይኖች በጥፍራቸው አፍሰውና በአቀንጣጤአቸው የደም ሥራቸውን በጥሰው ደማቸውን ያፈሰሱ ታሪክ በብራና የጣፋቸው መኮንን ናቸው፡፡ ጄኔራል መከተ ውሻን አስከትለው ሊያጠቁ የመጡ ሰዎችን  ባቀንጣጤ ወግተው ሬቢስ በሚባለው የጀርም መሳሪያ የረፈረፉ ጀግና ናቸው፡፡ በዚህ አስደናቂ ታሪካቸው የተደመመው የስብሰባ ተሳታፊ ጀኔራሉ የሚናገሩትን ለመስማት እንኳን ጆሮውን አፉን፣ አፍንጫውንና አይኑንም ከፍቶ የመርፌ ኮሽታ በሚሰማበት ጸጥታ ጠበቃቸው፡፡

ጀኔራል መከተ እንደ አንበሳ ትክሻቸውን ከምረውና ደረታቸውን እንደ ጋሻ ለጥጠው የቀኝ የፊት እግራቸውን ወደ ቀኙ የራስ ቅላቸው ወስደው ወታደራዊ ሰላምታ ለተሰብሳቢው አቀረቡ፡፡ ጄኔራል እንደ ታምራት በነፍጠኛ ወቢ እማይተፉ እንደ ስዬም ጦርነት ፈጣሪ ብለው እማይደነፉ የበሰሉ ጀግና ናቸው፡፡ በዚህ የበሰለና የሰከነ አንደበታቸውም መጋቢ ብሉይ ያሉትን ጠቅሰው ንግግራቸውን ጀመሩ፡፡ "አባታችን መጋቢ ብሉይ ሥለ ሰው፣ ሥለ እኛና ሌሎችም ፍጡራና አፈጣጠር ሲያስተምሩ መሰላል ሲወጡ የመጀመሪያውን አግዳሚ መርገጥ እንደሚያስፈልግ መክረው ነበር፡፡ የአባታችንን ምክር በመከተል ሌሎች ቦታዎችን ከመርገጣችን በፊት በዚቺ ሰዓት የቆምንባትን ዛምበራን እንቃኛለን፡፡ ከገዥዎች ጋዜጣ ወሬ እየለቀሙ ታሪክ ጻፍን እሚሉ 'ታሪክ ጸሐፊዎች' ችላ ቢሉትም ዛምበራ ታሪካዊ ቦታ ነው፡፡ ለመሆኑ ዛምበራ ለምን ታሪካዊ እንደሆነ እሚያውቅ አለ?" ብለው ሲጠይቁ አንድ ወጠጤ ቀበሮ ዛምበራን ደራ ከሚለው ስም አምታቶ "ሰዎች የሚዳሩበት ቦታ ስለሆነ?" ብሎ ሲመልስ እንኳን ጥርስ ያለው የሌለውም ተሰብሳቢ የተጋጠ ቆረቆንዳ የመሰለ ድዱን እያሳዬ ከዳር እስከ ዳር ሳቀ፡፡ ከዚያም አንድ በመልሱ ያልተደሰቱ ተሰብሳቢ "የነቀዘ ትውልድ! አንተ ያልከውን ለማድረግ የክትፎ መጎስጎሻና የመሸታ መጨለጫ ካሞቦውን ትቶ እዚህ ለምን ይመጣል?" የሚል አስተያዬት ሰጥተው ሳይጨርሱ አንድ ዛምበራ ያደገ ቀበሮ ዛምበራን የመዳሪያ ቦታ ባለው ወጠጤ አይኑን አጉረጥርጦ "ልክስክስ! አንተ እንዳልከው ሳይሆን ዛምበራ የአምስቱ ዘመን ፋኖዎችንና ሽፍቶችን በመጠለል ቅኝ አገዛዝና ኢፍትሐዊትነት ድባቅ ለመምታት በተደረገው የሞት የሽረት ፍልሚያ ትልቅ አስተዋፅዖ ያደረገ የአገር ደጀን ነው" አለ፡፡ "ትክክል የዛምበራ ታሪክ ይህ ጎበዝ እንዳለው ነው! በአምስቱ ዘመን የጎጃም፣ የሸዋ፣ የወሎና የጎንደር ጀግኖች ጣሊያንን ያርበደበዱት በዛንበራ በኩል ያባይን በረሃ እያቋረጡ መረጃ በመቀባበል ነበር፡፡ ጣሊያን ከላይ በመነጥር እያዬ በቦንብ ሲያጋያቸው እሚያመልጡት እንደ ዛምብራ ባሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችና የእኛ ቅድመ አያቶች በቆፈሯቸው ጉድጓዶች በመመሸግ ነበር፡፡ ይህም ማለት እኛ ቀበሮዎችም እንደ ዛምበራ ቅኝ አገዛዝንና ኢፍትሐዊነትን ለመታገል ትልቅ አስተዋጽዖ አድርገናል ማለት ነው! አይደለም እንዴ?" እያሉ ጀኔራል የጀግንነት ታሪክ ሲያስተምሩ ተሳታፊው "ትክክል!" እያለ ጭብጨባውን አቀለጠው፡፡

የጋለው ጭብጨባ እየቀነሰ ሄዶ ሲቆምም "እርግጥ ነው እኛ ከጀግና ሰዎች የትግል አጋሮች ነን፡፡ ለፋኖዎችና ለሽፍቶች እንደዚሁም ለባህታውያን ጉድጓዶቻችን ለምሽግነትና ለመጠለያ ስናበርክት ኖረናል፡፡ ሽፍቶችም ስለቀበሮ ጉድጓድ አንጎራጉረዋል፡፡ ከጀግና ሰዎች ጋር የነበረን የትግል አጋርነት እስራኤላዊያንን ከፈርኦን መንጋጋ ካላቀቀው ሙሴና ኢትዮጵያን ከጣሊያን ወረራ ካዳኗት ያምስቱ ዘመን ተናዳፊ ጀግኖች ጋር ባሳዬነው ትብብር ተረጋግጧል፡፡" ሲሉ "ትክክለኛ ታሪክ ነው!" አለ የስብሰባው ተሳታፊ፡፡ "ልብ በሉ! ጀግና ሰዎች ጥቂት እንደሆኑት ሁሉ ጀግና ቀበሮዎችም ጥቂት ናቸው፡፡ ባምስቱ ዘመን የሰውም ሆነ የቀበሮ ጀግኖች ጥቂቶች ነበሩ፡፡ ብዙው ወገኑን ክዶ ለጣሊያን እንቁላል ሲገዛና መንገድ ሲያያሳይ ይውል አለዚያም ጎመን በጤናን እየተረተ በላይም በታችም እያገሳ ተኝቶ ያድር ነበር" ብለው ጀኔራሉ ሳይጨርሱ " ባንዳውና ሰላቶው ዛሬ ብሷል ጀኔራል!" አለ ተሰብሳቢው፡፡ "አዎ! ዛሬ ብሷል! አብዛኛው በሆዱ እየተገዛ ነፍሰ ገዳዮችን እያገለገለ አለዚያም ጎመን በጤናን እየተረተ የውርደት ሞቱን ይጠብቃል፡፡ ሆዳም እንኳን ጎረቢትና ጓደኛውን ልጁንና ወላጁንም ይሸጣል" አሉ ጀኔራል የተኮሳተረው ግንባራቸው ለከሀዲ ያላቸውን ጥላቻ እያሳዬ፡፡ "ስለዚህ የእኛ ችግር ከጀግኖች ጋር ሳይሆን ከውሻና ከውሻ መሳይ ሆዳምች ጋር ነው!" ሲሉ ከውሻ አምልጠው የተረፉት ተነስተው ጭብጨባውን አቀለጡት፡፡ "አዎ ዛሬም በውሻ መሳይ ሆዳሞች ቀበሮና ሰው አንድ ላምስት ተጠርንፈው እርስ በርስ እንዲበላሉ እየተደረገ ነው፡፡ መጋቢ ብሉይ እንዳሉት ይህ እርስ በርሱ እሚበላላ ሰው በእኛ ውሻ ከመልቀቅ ይቆጠባል ብሎ የሚያስብ አለ?" ብለው ጀኔራል ሲጠይቁ "ማንም የለም! ሰውም እንደ ውሻ ጠላታችን ነው!" አለ ተሳታፊው በአንድነት፡፡

በቀረበላቸው ውኃ ጉረሯቸውን አረጠቡና ጀኔራል አሁንም ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡ "ቀደም ሲል እንደተወያየነው የፋኖ ምሽጉ የቀበሮ ጉድጓድ ነው፡፡ ምግቡም ድኩላ ነው፡፡ በሌላ በኩል ግን ሆዳም ሰው መኝታው የጥጥ ፍራሽ ምግቡም በሬና በግ ነው፡፡ ልብ በሉ! ጀግና ድኩላን አድኖ ሲበላ ሆዳም በግን ከእነአጥንቱ እየቆረጠመ ቀበሮን ያባርራል፡፡ "መጋቢ ብሉይ እንዳስተማሩት ቀበሮና በግ የሚተዋወቁት ሰው ከመፈጠሩ በፊት ነበር፡፡ ይህ የሚያረጋግጠውም በግ ለቀበሮ ምግብነት የተፈቀደው ለሰው ከመፈቀዱ በፊት መሆኑን ነው፡፡ አይደለም እንዴ?" ብለው ሲጠይቁ  "ይበል ብለናል ጀኔራል!!" አሉ መጋቢ ብሉይ፡፡ አንዳንዶቻችሁ "ቀበሮስ ለምን በግን ይበላል ብላችሁ ትጠይቁ ይሆናል፡፡ ቀበሮ በግን እንዲበላ የሚያስገድደው ተፈጥሮው ነው፡፡ የሥነ-ህይወት ጠበብቶች በሙያችን ገባህ አይበሉኝ እንጅ የቀበሮ ጥርስ የተሰራው ሥጋን ለመብላት ብቻ ነው" ብለው አቀንጣጢአቸውን ለማስረጃነት አሳዩ፡፡ "በሥነ-ህይወት ጠበብቶች ፊት ስለ አካል ክፍሎች ማውራት እንደሚከብደው መጋቢ ብሉይ ባሉበት ስለብሉይ ኪዳን መናገር ይከብዳል እንጅ ሰው ደም ያለው ፍጡር እንዳይበላ በዘሌዋውያን ሕግ ተከልክሎ ነበር፡፡ ሰው ግን እንኳን አምላክ የደነገገውን ራሱ የሞነጫጨረውን ሕግም እንደማያከብር በወመኔው አገዛዝ እያየነው ነው፡፡ ሕግ አፍራሹ ሰው ሕግን ጥሶ እንኳን በግን አህያውንና አይጡንም እየበላ ነው፡፡ አህያውና አይጡ ሲነጥፍ እኛንም መብላቱ እማይቀር ነው፡፡ ቢጫ አይነ-ገናዎች ወመኔዎችን እያጎረሱ ኢትዮጵያን ከወረሩበት ጊዜ ጀምሮ ያህያና የአይጥ ቁጥር መቀነሱ እሙን ነው፡፡ ቢጫዎችንና ነጮቹን መምሰል መሰልጠን እሚመስላቸው አሻንጉሊት አበሾችም አህያና አይጥ መብላት እንደሚጀምሩ አትጠራጠሩ፡፡ አህያውና አይጡ ሲጠፋም እነዚህ አሻንጉሊቶች ወደ እኛ እንደሚዞሩ አትዘንጉ!" ሲሉ ሴት ቀበሮች ሆድ ባሳቸውና አፋቸውንና አፍንጫቸውን በጥፍሮቻቸው ይዘው ሰቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡ "በምናወጣው ወታደራዊ ስልት ሽንጥን ገትሮ መፋለም እንጅ ማልቀስ መፍትሔ አይሆንም! ቀይ ቀበሮ፣ የሰሜን ቀበሮ፣ የባሌ ቀበሮ ጂኒ ጃንካ የሚባሉትን ክልሎች ደርምሰን ቀበሮ በሚል ጃንጥላ ተሰባስበን በጥፍር፣ በጥርስና በድድ መፋለም ይኖርብናል" ሲሉ ታሳታፊው ምክራቸውን መቀበሉን በደማቅ ጭብጨባ አረጋገጠ፡፡

"ሰው በሆዱ ብቻ ሳይሆን በክህደቱም ውሻን ይመስላል፡፡ መጋቢ ብሉይ እንዳሉት ውሻ በአካሉም ሆነ በአፈጣጠር ዘመኑ እሚመደበው ከኛ ጋር ነው፡፡ ዳሩ ግን በአራት እግሩ እየሄደ በሁለት እግሩ ከሚሄደው መናጢ ሰው ወግኖ እኛን እየፈጀ ነው፡፡ ከሀዲውን ውሻም መናጢው ሰው በአገልጋይነቱ የመጀመሪያው ለማዳ፣ ታማኝ ጓደኛ፣ የተደበቀን ፈላጊ፣ ቅብጥሶ ቅብጥሶ እያለ ያሞካሸዋል፡፡ ይህ ሙከሻም ምእራባውያን እንደ ባርያ የሚያገለግሏቸውን ወመኔ ገዥዎች ዲሞክራቶችና ምጣኔ ሐብት አሳዳጊዎች እንደሚሉት ማታለያ ነው፡፡ ወመኔዎች ለሚያሞካሿቸው ምእራባውያን አቤት ወዴት እያሉ እንደ አሽከር በላኳቸው ግዛት ሁሉ እንደሚዘምቱት ውሾችም ጅራታቸውን እየቆሉ ሰው ያዝ  ብሎ በላካቸው የቀበሮ ግዛት ሁሉ እየዘመቱ ነው" እያሉ ጀኔራል ሲያስተምሩ አንድ በጀኔራሉ ቁመና፣ ጀግንነትና ምሁርነት የተማረከች ቆንጆ ቀበሮ በደንብ እንድትታይ በኋላ እግር ጥፍሮቿ ቆማ መቃ አንገቷን እየሰበቀችና ችቦ ወገቧን እንደ እዝርት አሹራ ዳሌዋን እያሳዬች "የሁለት ሺ ስድስቱ ቆጠራ እንደሚያመለክተው የቀበሮ ቁጥር እጅግ ቀንሷል፡፡ እንዲያውም ሴቶች በርትተው እያከታተሉ ወልደው ባያሳድጉ እንደ ወንዶቹ ጡርቂነትማ ጨርሰን እንጠፋ ነበር" ብላ ለወንዶች ያላትን ንቀትና ለሴቶች ያላትን አድናቆት ገልፃ ሳትጨርስ ከግዕዝና ከቅኔ መምህሯ ከእማሆይ ገላነሽ ሰፈር የመጣች አንድ ወጣት ቀበሮ "ምንት ምንትስ.." ብላ በግእዝ ተቀኝታ ለቆንጆዋ ቀበሮ መልስ ስትሰጥ ቅኔው የገባቸው ጥቂቶች ሽንታቸው እስኪመጣ ሲስቁ ሌሎችም ካልገረማቸው አልሳቁም በሚል ተራ በተራ ፈገግ ማለት ጀመሩ፡፡ "ጨለማን ተገን አድርገው ወንዶች በርትተው ጉድጓድ ባይቆፍሩ ልጆች ከየት ይመጡ የትስ ያድጉ ነበር! ይላል ቅኔው ሲተረጎም" ይበል ብለናል! አሉ አንድ የግዕዝ ሊቅ፡፡ ሞኝ ሁለት ጊዜ ይስቃል መጀመሪያ ሌሎች ሲስቁ ዳግመኛም ነገሩ ሲገባው እንደሚባለው ጠቅላላ ተስብሳቢው በሐይል ሲስቅ የገደል ማሚቶው ድፍን ዛምበራን አናጋው፡፡

ተሳታፊዎች ሊቋ በተቀኙት ቅኔ እየተንፈራፈሩ ሲስቁ ከቀበሮዎች ኪስ የሾለኩ ሁለት የእጅ ስልኮች ከመሬት ተገኙ፡፡ ጸጥታ አስከባሪ ኮማንዶዎች ስልኮቹን አንስተው ሲፈትሹ ሰርገው የገቡ ሰላዮች ስብሰባውን እየቀዱ መሆኑን ተረዱ፡፡ ስብሰባውን ሊቀዱ የገቡትን ሰላይዎች ኮማንዶዎች አንቀው ሲያወጧቸው ግርግር ተፈጠረ፡፡ ሰላይ መሆናቸውን የተረዳው ተሰብሳቢ እየተረባረበ ሲረግጣቸውና በጥፍር ሲሞነጭራቸው ከሰላዮቹ አንዱ የቀበሮ ለምድ የለበሰ ውሻ ሆኖ ተገኘ፡፡ ይህንን ውሻ ያዬ ሁሉ አፉን እንደ ዓባይ ሸለቆ ከፍቶና አይኑን እንደ ልቅ አንጎልጉሎ እንደ ስልክ እንጨት ደርቆ ቀረ፡፡ ተሰብሳቢው ከድንጋጤና ከግርምት አለም ሲመለስ "አሁኑኑ እርምጃ ይወሰድባቸው!!" ሲል ጀኔራል መከተን ጠየቀ፡፡ ጄኔራል መከተም "ክቡራትና ክቡራን ቀበሮዎች ሆይ! አንዴ! አንዴ! አዳምጡኝ! እንደማመጥ! እንደማመጥ!" ብለው ሲጠይቁ ጀኔራሉ የሚሉትን ለመስማት ሁሉም እረጭ አለ፡፡ "ከስሜታዊነትና ግብታዊነት እንላቀቅ፡፡ እኛ ቀበሮች እንደ ወመኔ ገዥዎች ከእጃችን የገባን እስረኛ የምናሰቃይና የምንገድል እርጉሞች አይደለንም፡፡ እንደምታዩት በባንዳ ቀበሮዎች እርዳታ የእኛን መልክ ለብሶ የመጣውን ውሻ በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ ነገር ግን ሌሎችም ሰላዮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ስብሰባውን እዚህ ላይ እናቆምና ጸጥታ ማስከበሩ ላይ እናተኩራለን፡፡ ከጸጥታ አስከባሪዎች በስተቀር ሁላችሁም ከተመደበላችሁ ጉድጓድ እንድትገቡ እንጠይቃለን፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድ ነገ ከጧቱ በሁለት ሰዓት እዚሁ ቦታ እንገኛለን" ብለው ስብሰባውን በተኑ፡፡

ጀኔራልና ኮማንደሮቻቸው እንደ ወመኔ ገዥዎች እየገረፉና ጥፍር እያወለቁ ሳይሆን እያበሉና እያጠጡ እጅ ከፈንጅ ከተያዙት ሰላዮች መረጃ ሲሰበስቡ አደሩ፡፡ ከተያዙት በስተቀር ሌላ ሰላይ እንደሌለና አደጋም እንደማይፈጠር ካረጋገጡ በኋላ ሰብሰባውን በሁለት ሰዓት ጀመሩ፡፡ ተሰብሳቢው ቦታ ቦታውን ከያዘ በኋላ ኮማንደሮቹ ሰላዮቹን እግር ለእግር አስተሳስረው ከተሰብሳቢው ፊት አቀረቡ፡፡ አንደኛው ኮማንደርም ሰላዮቹ ለጀኔራልና ለኮማንደሮች የተናዘዙትን በራሳቸው አንደበት ለሰፊው ቀበሮ እንዲናዘዙ አዘዟቸው፡፡ የቀበሮ ለምድ ለብሶ የገባው ሰላይ ውሻ ጆሮውንና ጅራቱን ወትፎ "በመጀመሪያ ከሰው ልጅ ያላየሁትን ርህራሄ ከቀበሮ በተለይም ከእኒህ ጀኔራል በማግኜቴ ለመላው ቀበሮዎች ምስጋናዬንና አድናቆቴን አቀርባለሁ፡፡" ብሎ ጭብጨባ ከተሰብሳቢው ለመለመን ቀና አለ፡፡ ተሰብሳቢው ግን ጥርሱን ነክሶ "የምታታልለውን አታል!" በሚል ስሜት አፈጠጠበት፡፡ ምህረት የተነፈገ የመሰለው ሰላዩ ውሻ በፍርሃት ተውጦ ኑዛዜውን እንዲህ ሲል ቀጠለ፡፡ "እንደምታዩኝ ውሻ ነኝ፡፡ ነገር ግን ቀበሮ በማባረር የምኖር ውሻ አይደለሁም፡፡ እውነቱን ለመናገር ከትናንትናው በቀር ቀበሮን አስደንግጬ አላውቅም፡፡ ከአካሌ መረዳት እንደምትችሉትም ክልስ ነኝ፡፡ እናቴ አበሻ ብትሆንም አባቴ ጣሊያናዊ ውሻ ስለሆነ ያደኩት ሮም ከተማ የተቀመመ ምግብ እየበላሁ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የመጣሁትም በሁለቱ የኢትዮጵያና የጣሊያን ጦርነቶች አበሻ ቀበሮዎች ምሽግ እየቆፈሩ ፋኖዎችን ስለረዱ ቀበሮዎችን በቀለም፣ በዘር፣ በክልልና በሃይማኖት ከፋፍሎ እርስ በርሳቸው እንዲፋጁ የሚያደርገውን የቆዬ ያውሮጳ እቅድ ለማስፈጸም ነው፡፡ ይህንን ተልኮዬን ለማሳካትም እዚህ አብረውኝ እንደቆሙት ያሉትን ቀበሮች በጥቅማጥቅም ደልያለሁ፡፡ በስህተቴ ተጸጽቼ ከእግራችሁ ተንበርክኬ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ብሎ ባፍንጫው ተደፉ፡፡ ባንዳዎቹ ቀበሮዎችም በሐፍረትና በፍርሃት ተሸማቀው መሬት መሬቱን እያዩ በተወካያቸው አማካኝነት ኑዛዜአቸውን እንደሚያቀርቡ ገለጡ፡፡ የተወከለው ባንዳ አይኑን ከመሬት ተክሎ "እኛን ያሳሳተን ይህ ክልሱ ውሻ ነው፡፡ ሰው ያዝ ሲለው ውሻ እያባረረ ከሚደፋችሁ ሮም ወስጄ የተቀመመ ምግብ እየበላችሁ ከአልጋ እንድትተኙ እድሉን አመቻችላችኋለሁ ብሎ አታለለን" ብሎ ሳይጨርስ አንድ ጎረምሳ ቀበሮ እንደ ምኒሊክ ብምርህ ማሪያም አትማረኝ በሚል መንፈስ ቡጢ ሊያቀምሰው ሲቃጣ ኮማንደሮቹ አዳኑት፡፡ ኑዛዜአቸውን ሲጨርሱ ከፊሉ "ይቅርታ ይደረግላቸው' ሲል የቀረው "እንዴት ለሰይጣን ይቅርታ ይደረጋል?" ሲል ተቃወመ፡፡

በዚህ ግርግር መካከል አንድ አዛውንት ቀበሮ ብድግ አሉና እንደ ቄስ አማረ አንገታችውን አንዴ ወደ ግራ ሌላ ጊዜ ወደቀኝ እያቅለሰለሱ "አያችሁ ይሉኝታ ቢሱ ሰው የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ ቀበሮዎች ተጠንቀቁ እያለ ይተርታል፡፡ የቀበሮ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ውሾች ወይም ውሻን የበግ ለድ አልብሰው ያዝ ከሚሉ ሰዎች ተጠንቀቁ ብሎ ሲተርት ግን ተሰምቶ አይታወቅም፡፡ ፈቃዳችሁ ተሆነ በአይናችሁ ያያችሁትን የቀበሮ ለምድ የለበሰ ውሻ ልዝለልና ሰው የበግ ለምድ አልብሶ ወደ ቀበሮ ስለላከው ውሻ ላውጋችሁ፡፡ መቼም የቀበሮ ጆሮ ቀጥ ስላለና ደፍቶ ስለሚያይ እንደ ተንኮለኛ ይቆጠራል እንጅ እንደ ቀበሮ ደግና ታማኝ ፍጡር የለም፡፡ ከእለታት አንድ ቀን ቀበሮ የበግ መንጋን ሲጠብቅ፤ ለአገልግሎቱም አንድ ጠቦት ሊያገኝ ከሰው ጋር ተዋዋለ፡፡ እንደምታውቁት ቃል በቀበሮ ዘንድ እንደዚያ... አምጡልኝ ለሕዝብ ሲል ራሱን እንደ ክርስቶስ አሳልፎ እንደሰጠው ..." ብለው ሳይጨርሱ አብዛኛው ተሰብሳቢ በአንድነት "እስክንድር ነጋ!" አለ፡፡ አዛውንቱ ቀበሮም " እስክ ጥንቱ የጦቢያ ግዛት እስተ እስክንድርያ ይንጋላችሁ" ብለው መርቀው  ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡  " አዎ ቀበሮ እንደ ብሩኩ እስክንደር ነጋ እምነት ጥኑና ቃል አክባሪ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ቀበሮ በቃል-ኪዳኑ ጠንቶ አንዲት ግልገል ሳያጎል የበጎችን መንጋ ለሰውየው አስረከበ፡፡ ሰውየውም ቀበሮን በምስጋና ሸንግሎ ጦቦቱን እስታመጣልህ እዚህ ጠብቀኝ አለው፡፡ ቃል አክባሪው ቀበሮ አሁንም የገባውን ቃል አክብሮ ጠበቀው፡፡ ይህ ቃሉን እንደቀበኛ የበላ ሰው ግን የበግ ለምድ አልብሶ ውሻውን አመጣና ያዝ ብሎ ወደ ቀበሮው ለቀቀው፡፡ ቀበሮውም ለሰው ሞት አነሰውን ተርቶ ውሻውን አመለጠው፡፡ ለሰው ሞት አነሰው እሚለው ዜማ የቀበሮ ብሔራዊ መዝሙር የሆነው ተያን ጊዜ ጀምሮ ነው" ብለው ሲተርኩ አንድ ካዲሳባ የመጣ ቀበሮ "ይህ ታሪክ በደንብ እማውቀውን ቃል በላ አስታወሰኝ" አለና "የቀበኛው የልጅነት ስም አብዮት ነበር? ብሎ አዛውንቱን ጠየቀና ተሰብሳቢውን አውካካው፡፡

ሁካታው በረድ ሲል ጀኔራል ተነሱና " ለዚህ አቢይ የቀበሮ ታሪክ አባታችንን እናመሰግናለን፡፡ ይህ አባታችን የነገሩን ታሪክ የተፈጸመውና ብሔራዊ መዝሙር መዘመር የጀመርነው ከሀዲዎች እንደሚሉት ከመቶ አመት ወዲህ ሳይሆን ከአራት ሺህ ዓመታት በፊት ነበር፡፡ እንደምታውቁት ውሾችና ውሻ መሳይ ሰዎች ታሪክ እንዲወራ አይወዱም፤ ከታሪካቸውም መማር አይፈልጉም፡፡ እነዚህ እፊታችሁ የቆሙት ሰላዮችም የሚማሩና የሚታረሙ አይመስለኝም፡፡ ይህንን ስል እንደነሱ ክፉ ሆነን እናሰቃያቸው ወይም እንግደላቸው ማለቴ አይደለም፡፡ በሽተኛ በእግዚአብሔር እጅ እንደሆነው ሁሉ እጅና እግሩ የታሰር እስረኛም በእግዚአብሐር እጅ ነው፡፡ ስለዚህ እስረኛን ማሰቃዬት በእግዚአብሔር ሕግ ያስጠይቃል፤ ምድራዊ ሕግ ባለበት አገር በምድራዊ ሕግም ያስጠይቃል፡፡ ስለዚህ ለእስረኛ እሚደረገው እንክብካቤ እየተደረገላቸው በሕግ ውሳኔ እስከሚያገኙ ማረሚያ ቤት ይቆያሉ፡፡ ውሾችና ውሻ መሳይ ሰዎች በሆዳቸው እየተገዙ በዶላር፣ በዩሮና በፓውንድ ከጠነቡ የቀበሮ መንግስታት ጋር የሚሸርቡትን ሸር ማጣራቱን እንቀጥላለን፡፡ ሆዳምና ውሻ መቼውንም ስለማይጠፋ ከመጥፋት የሚያድነን የራሳችን ጥንካሬ ነው፡፡ ሆዳምንና ውሻን አንድ ሆነን በስልት መዋጋት አለብን!" ሲሉ አንድ ሰበብ የሚያበዛ ቀበሮ ብድግ አለና "ሰው ብዙ መሳሪያ አለው፤ ውሻም በተኩስ ሰልጥኗል ይባላል፡፡ እኛ እጅ እንኳን የለንም፤ በምን ልንዋጋ እንችላለን?" ብሎ ሲጠይቅ አንድ ቆፍጣና ኮማንደር ተቆጣና "ያምስቱ ዘመን ጀግኖች  እስታፍንጫው ታጥቆና መርዝ በአውሮፕላን ጭኖ የመጣውን ጣሊያን ያሸነፉት በጦርና በጎራዴ ነው፡፡ አሸናፊው መሳሪያ ሳይሆን ልብ ነው፡፡ ልብ ሲኖር ሜዳው ገደል ነው! ልብ ሲኖር ከተማው ጫካ ነው! ልብ ታለህ እጅ ባይኖርህም በጥርስህ ንከስ፣ መሳሪያ ባይኖርህ በጥፍርህ ቧጭር!  አዎ እንደ ክቡር ጄኔራል በጥፍርህ ቧጭረህ አይን አፍስስ፣ በጥርስህ ነክሰህ በበሽታ ረፍርፍ! ቀበሮ በበላበት በሚለምድ ሆዳም ውሻና ተኋላው በመጣ ውሻ መሳይ ሰው ርስቱን ተንጥቆ እየተባረ በጭራሽ አይኖርም! የቀበሮ ፋኖ ወደፊት ይገሰግሳል! ተወደቀም ፎክሮ ይነሳል! የቀበሮ ፋኖ ክብሩን እርስቱን ጥሎ ተመኖር መሞትን ይመርጣል፡፡ ታጠቅ! ተነስ! አለዚያ ፈሪ ለናቱ ያገለግላል፤ ምጣዱ ሲጣድ ሙግድ ያቀብላል እንደሚባለው ከቤትህ ዋልና ለሚስትህ ሙግድ አቀብል! ሰበበኛ!" ሲል አንዳንድ የሚልመጠመጡ ባሎች ያሏቸው ሴቶች ሙግድ አቀባይ ባሎቻቸውን እያዩ በሳቅ ፈነዱ፡፡ ጀግና ቀበሮዎች በጀኔራሉ ፊት ፎከሩ፡፡ ሙግድ አቀባይ ባሎችም በምንተ እፍረት ከጀግናዎች  ጀርባ ቆመው ዘራፍ ማለት ጀመሩ፡፡

ፉከራውና ሽለላው ሲያበቃም ጄኔራል መከተ የኮማንደሩን ቆምጫጫ አስተያየትና የፎከሩትን አድንቀው "ወንድማችን እንዳለው አሸናፊው ልብ ነው፡፡ ቀበሮ ከመጥፋት እሚድነው ክብሩን፣ ታሪክና ባህሉን በልቡና በቃል ኪዳኑ ሲጠብቅ ብቻ ነው፡፡ አለዚያማ ክብሩን የተገፈፈ ቀበሮ ቅርቀብ ተጭኖ በዱላ ከሚነረት አህያ በምን ይሻላል? እንደ አህያና እንደ ውሻ ሆድን እየቆዘሩ ክብርን ተራቁቶ ከመኖር በርሃብ ሞቶ በክብር ተከፍኖና በማእረግ ተገንዞ መቀበር ይሻላል፡፡ ስለዚህ ነፃነት ወይም ሞት ብለናል! ከዛሬ ጀምሮ ሜዳው፣ ተራራው፣ ሸንተረሩ፣ ሐይቁ፣ ወንዙና ጅረቱ በዋሽንት፣ በመሰንቆ፣ በክራር፣ በበገናና በእምቢልታ ወኔያማ  ዜማዎች ያሸብርቅ፡፡ ጋራው፣ ሸለቆውና ጫካውም ቀረርቶና ፉከራን ያስተጋባ፡፡ የዋሽንት፣ የመሰንቆ፣ የክራርና የበገና እንጉርጉሮዎች፣ የወይዛዝርት ዘፈኖች፣ የካህናት ወረቦችና ቅኔዎች፣ የጎበዝ ቀረርቶዎችና ፉከራዎች የጀግና መብቀያ ለም መሬቶች ናቸው፡፡ እነዚህን የጀግና መብቀያ ለም መሬቶች ሱሪና ቀሚስ በሚያስወልቁ ምዕራባውያን የሚዚቃና የዳንስ አረሞች መበከል የሚያበቅለው ቀበቶውን ከቂጡ ታጥቆ መዥገር እንደያዛት የድርቅ ላም እሚሽመደመድ ትውልድ ነው፡፡ ስለዚህ ስልጡን ለመምሰልና ገንዘብ ለማካበት በማንነቱ አፍሮ ቆዳውን የለወጠውን ማይክልንና የጳውሎስን ወዳጅ ቦያንሲን እየኮረጀ ጀግና እሚያበቅለውን ባህላችንን እሚያጠፋም ከባንዳ እሚመደብ ነው፡፡ ባንዳ እግራችንን እየነከሰን ብዙ መራመድም ስለማንችል በላይ ዘለቀ፣ አበበ አረጋይና ሌሎችም ጀግኖች እንዳደረጉት የመጀመሪያው እርምጃችን ባንዳን ማጽዳት ይሆናል፡፡ ባንዳን አጽድተን በአንድ አላማና በአንድ ባንዲራ ከተሰለፍን የመሳሪያ ጋጋታም ሆነ የውሻ መሰልጠን ከድል አይገታንም፡፡ ውሻንና ውሻን መሳይ ሰው ድል እንደምንነሳ ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡" ብለው ኳስ በሚያህለው ቡጢያቸው ጠረጴዛውን ሲያቦኑት ተሳታፊው እየዘለለ ጭብጨባውን ለሁለት ደቂቃ አቀለጠው፡፡ ጭብጨባው በረድ ሲልም ጀኔራል "በምስጢር የምናስተላልፋቸውን ወታደራዊ የትግል ስልቶች እየተከተላችሁ ቀበሮን ከመጥፋት ለማዳን  በሚደረገው መራር ትግል በንቃት ተሳተፉ፡፡ አመስግናለሁ፡፡" ብለው ስብሰባውን በጸሎት እንዲዘጉ ቄስ ወልደ አማኑኤልንና ሼህ ሙዴስርን ጋበዙ፡፡

ቄስ ወልደ አማኑኤልና ሼህ ሙዴስር በስብሰባው መደሰታቸውን ከገለጡ በኋላ እውነትና ፍትህ  የእግዚአብሔር ባህርያት እንደሆኑ አስረድተው፤ ለእውነትና ለፍትህ የሚደረግ ትግልም ለእግዚአብሔር የሚደረግ ትግል መሆኑን አስተምረው፤ ለእግዚአብሔር ለሚደረገው ትግልም የቤተ-ክርስቲያንና የመስጊድ አገልጋዮች ከፊት እንዲሰለፉ በአፅንኦት ጠይቀው የመዝጊያውን ጸሎት አደረሱ፡፡ ከጾለቱ በኋላ "ለሰው ሞት አነሰው" እሚለው የቀበሮ ብሔራዊ መዝሙር ተዘምሮ ተሳታፊዎች "ፋኖ ተሰማራ" እሚለውን የነፃነት ተጋድሎ ዜማ እያዜሙ ወደ እያገራቸው ተመልሰው የህልውና ፍልሚያውን ቀጠሉ፡፡

 

መጀመርያ ህዳር ሁለት ሺ ስምንት ዓ..ም.

እንደገና ህዳር ሁለት ሺ አስራ ስድስት ዓ.ም.
https://amharic-zehabesha.com/archives/187228

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...