Thursday, February 29, 2024

መንግስቱ ሙሴ (ዶ/ር) ከዳላስ

 

መግቢያ

ታዋቂው ጣሊያናዊ ፈላስፋ፣ ዲፕሎማት እና የህዳሴ ዘመን ፀሐፊ ኒኮሎ ማቺያቬሊ ፍልስፍናው “The Prince” ከሚለው የሴሚናል ሥራው ጋር ይያያዛል። በ16ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የተጻፈው ይህ ድርሰት የስልጣን ምንነት፣ አስተዳደር እና ገዥዎች ተገዥወችን ለመቆጣጠር ስለሚጠቀሙባቸው ስልቶች ጥልቅ ግንዛቤዎችን ይሰጣል። መጽሐፉ በዝርዝርም ያስረዳል።ለዚህም ነው ማኪያቬሊ ከሞተ በኋላ ብዙ መቶ ዓመታት ቢያልፉም የማኪቢሌ የፍልስፍና አስተሳሰቦቹ በተለይም በፈላጭ ቆራጭ መሪዎች ዘንድ እያስተጋባ  እና እያደገ ህያው ሆኖ ቀጥሏል። ይህ ጽሑፍ የማኪያቬሊ ፍልስፍና በዘመናችን አምባገነኖች ላይ ያለውን ዘላቂ ተጽእኖ የሚዳስሰው በኢትዮጵያው የአብይ አህመድ ባህርያትን በመቃኘት ሲሆን አይን ያወጣው ዘረኛ አብይ አህመድ የማኪያቬሊያን መርሆች በአስተዳደር ስልታቸው ውስጥ የሚገለጡባቸውን መንገዶች አንባቢም እንዲያይ ይረዳ ዘንድ ለመዳሰስ ይሞከራል።

የማኪያቬሊያን ፍልስፍና፡ አጭር አጠቃላይ እይታ

በዚህ ዘመን በሚኖሩ አምባገነን መንግስታት ውስጥ ያለውን የማኪያቬሊያን ፍልስፍና ልዩ አተገባበር ከማሳየቴ በፊት፣ የማኪያቬሊ የፖለቲካ አስተሳሰብ መሰረታዊ መርሆችን መረዳት አስፈላጊ ስለሆነ ወደማኪቪሊ መርህ አስተሳሰቦች አጭር እይታ ላጋራ። በ"The Prince" መጽሐፉ ማኪያቬሊ አንባ ገነን ገዥወች ስልጣናቸውን እንዴት ማግኘት፣ ማቆየት እና ማስፋፋት እንደሚችሉ ተግባራዊ ምክሮችን ይሰጣል። በፍልስፍናው ውስጥ ዋና ፅንሰ-ሀሳቦች እንደ ሥነ-ምግባር ፣ ከሥነ ምግባራዊ ጉዳዮች ይልቅ የመንግሥትን ጥቅም ማስቀደም እና ርዕሰ ጉዳዮችን ለመቆጣጠር ፍርሃትን እና ማጭበርበርን የመሳሰሉ ፅንሰ-ሀሳቦች ከ ስነመግባር አውጥቶ በስራ ማዋል ለመንግስት ጠቀሜታ አላቸው ይላል።

ማኪያቬሊ ፍርሃትን በተገዥው ሕዝብ ውስጥ ማስረጽ ታዛዥነትን እና መረጋጋትን ስለሚያረጋግጥ አንድ ገዥ ከመወደድ ይልቅ መፍራት የተሻለ አማራጭ ነው ብሎ ይሟገታል። ሌላው በማኪቪሊ ፍልስፍና የፖለቲካ ግቦችን ለማሳካት አንድ ገዥ አስፈላጊ የሆነውን ማንኛውንም ዘዴ መጠቀም ለምሳሌ መግደል፤ ማሰር፤ ቶርቸር ማድረግ ወዘተ እና ተንኮልን መጠቀምም (Convince & Confuse) የፖለቲካ ትርፉን እና ክሳራውን በማስላት ይህዝብን ግንዛቤ ማጭበርበርን ማሳሳትን እንደስልት ይደግፋል። የማኪያቬሊ ፕራግማቲዝም ፖለቲካ ባህላዊ ሀይማኖታዊ እና ስነምግባራዊ የሞራል ገደቦችን ውድቅ ያደርጋል፣ ምክንያቱም እነዚህ የሞራል ጫፎቹ ስልጣንን ለማሳደድ እና ለመጠበቅ መንገዶችን ያጠብባሉ በሚል ስሌት ነው።

አብይ አህመድ እና የማኪያቬሊያን አስተዳደር በኢትዮጵያ

የኢትዮጵያው አረመኔ አንባገነን መሪ አብይ አህመድ የማኪያቬሊያን አስተዳደር በተግባር አሳይቷል። አብይ ወደ ስልጣን ሲመጣ ሕዝብን በማጭበርበር ተወዳጅነትን በማትረፍ ሲሆን፣ ብዙ ሳይቆይ ከዳር እስከዳር ያመነውን እና ፍቅር እና ሞገስ ያሳየውን ሕዝብ እና ደጋፊወቹን ሆን ብሎ ለማስቀየም ተግቶ ሰርቷል። ይህን አስመልክቶ የዘረኛዋ የህወሓትን የንስሐ አባት ስብሀት ነጋን ሲፈታ ቁጥረ ብዙ የሆኑ ደግ አሳቢ እና ለሐግር እድገት የሚታትሩ ዜጎችን በማሰር ሕዝብን አሳዝኗል። በእራሱ የፕሮፖጋንዳ ሚዲያ ለቀረበለት ጥያቄ “የነስብሐት ነጋ በነጻ መለቀቅ እኛንም አስደንግጦናል በሚል ተሳልቋል”።

ከዚህ ግዜ በኋላ በሌላው እንደድሮው ሕዝብ እንዲወደው እንዲያምነው እና እንዲያከብረው ሳይሆን በጀመረው የእስትራቴጅ ማኬቪላዊ ለውጥ እንዲፈራው እና እሱን ሲያይ እንዲሸማቀቅ ኃይል መጠቀምን አካሂዷል እያካሄደ ነው።ለዚህ ማሳያው እስክንድር ነጋ ያነሳቸው የዋና ከተማይቱን አደጋ ላይ መውደቅን አስመልክቶ በአዳራሽ የተናገረው በጀሮ ለሰማው፤ ገጽታውን በቴሌቪዥን ለተከታተለው እጅግ አስፈራሪ የሆነውን የቀይሽብርን ንፅርብ በመጥቀስ ከቀይ ሽብሩ በእጥፍ በቀን መቶሺሆችን እንጨርሳለን የሚለው የምር ማንነቱን የገለጠ ማኪቪላዊ ንግግር በሐገሪቱ ያንዣበበውን አደጋ ፍንትው አርጎ ያሳየ ነበር።በቀጣይ  ጥያቄወች ሲነሱበት የተቃዋሚዎችን ጭካኔ ተግባራዊ በማድረግ ለእርሱ ወደስልጣን መምጣት ምክንያት የነበሩትን ዘረኛ አጋሮችን እና በየመድረኩ ያወድሳቸው የነበሩትን ጃዋር መሐመድን አይነቱን ከበቀለ ገርባ ጋር ዘብጥያ አወረዳቸው፤ የጠቅላይ ሚኒስቴርነቱን ቦታ ለቆ ለሱ የሰጠውን ለማ መገርሳን አሽቀንጥሮ ጣለው፤ ከሁሉም በላይ በወለጋ፤ በመተከል፤ በሻሸመኔ፤ በአዲስ አበባ ዙሪያ መጠነ ሰፊ የሕዝብ መፈናቀል፤ የግድያ እና ዘረፋ ወንጀል መንግስታዊ በሆነ የግልጽ እና የስውር መዋቅር መካሄድ ጀመረ። ከሁሉም አስደማሚው እና ። አረመኔው አብይ አህመድ አገዛዙን እና ማእከላዊ ስልጣኑ አደጋ ገጠመው ብሎ ባሰበ ግዜ የጥንካሬ እና የማይሸነፍ ምስልን ከዚህ በፊት ከነበሩን ገዥወች ባልታየ ጭካኔን በማሳየት ለዜጎች ሞት እና ስደት ፍጹም ግድ የለሽነቱን በተለይ ለሽሆች ሞት እና ስደት አንድም ቀን ሀዘኔታ ያለማሳየቱ የእርሳሱ የብልጽግና አባላቱ ሳይቀር አረመኔ እስኪሉት ያደረሰ ባህርይውን አሳየ ይህም ማኪያቬሌ እንደሚለው ስብእናው ተፈሪ እንዲሆን አድርጎታል። ለዚህ መፈራት፤ እና ፍጹም ማኬቪላዊ አስተሳሰብን ከግብ ለማድረስ ቀድሞ ወደስልጣን ሲመጣ ያሰበበትን ስለነበር ስልጣን በያዘ ማግስት የስውር መንግስት እንደመሰረተ በሰሞኑ በ ርዮተር የተጋለጠውን የስውር ኮሚቴ መስርቶ መጠነ ሰፊ አፈና እና የድብቅ ግድያወች ተካሄደ።

አብይ አህመድ የዘመናችን የማኪቬሌ ፍልስፍናን The Prince በስራ የተረጎመ ለዚያ ዘመን እንዲመጥን በሚል የጻፈውን ከ 500 አመታት በኋላ በኢትዮጵያን እና ሕዝቧ ቤተ ሙከራነት የተጠቀመበት በትጋት በሕዝብ ላይ መሸማቀቅን ለመፍጠር የተጠቀመበት አንዱ ዘዴ በሰሞኑ በ Reuters News Magazine የአምስት አመት ክትትል ጽናት እንደተገለጸው ስውር ባለሙሉ ስልጣን ያለው መንግስት በቀጥታ ለእርሱ ሪፖርት የሚያደርግ አፋኝ፤ ገዳይ እና ወሳኝ መንግስት ገና ስልጣን ከያዘ ቀን ጀምሮ በመመስረት እየተገለገለበት ይገኛል።

የ አብይ አህመድ አገዛዝ የበርካታ የማኪያቬሊያን መርሆችን በምሳሌነት ያሳያል፡ ከነዚህም ውስጥ የመንግስትን ጥቅም ከግለሰብ መብት ማስቀደም፡ ፍርሃትን በህዝብ ለማስፈን ስልታዊ አጠቃቀም እና የህዝብን አመለካከት ለመቆጣጠር ቁጥጥር የተለያዩ ስልቶችን መጠቀምን ጨምሮ። የሱን መንግስት እንደ ባለራዕይ መሪ ለማሳየት መደመር የሚለውን ባዶ ሰነድ እና የተራቀቁ የፕሮፓጋንዳ ቴክኒኮችን ይጠቀማል፣በተመሳሳይ ጊዜ ተቺዎችን ዝም በማሰኘት እና በትንሽ የታማኞች ክበብ ውስጥ ስልጣንን ያጠናክራል።

አብይ አህመድ ከተጠቀሙባቸው ቁልፍ ስልቶች ውስጥ አንዱ የፍርሃት እና የጥርጣሬ አየር በሀገሪቱ እና በህዝቧ ማስፈን ነው።ከእርሱ ሀሳብ ጋር የተቃረኑ ወይም በሀሳብ የተለዩ የቅርትብ ሰወቹን ጨምሮ በፍጥነት ይገደላሉ ወይንም በአሰቃቂ ሁኔታ ይታፈናሉ፣ ተቃዋሚዎች ብዙውን ጊዜ ለእስር፣ ለእንግልት እና ለሞት ይዳረጋሉ። ይህ የተፈጠረው ማኬቪላዊ የፍርሀት ድባብ ተቃዋሚዎችን ለመግታት እና የስልጣን ይዞታ ለማጠናከር እያገለገለው ነው።

በተጨማሪም የአህመድ አገዛዝ የማኪያቬሊ የማጭበርበር እና የማታለል ስትራቴጂያዊ አጠቃቀም ላይ ያለውን ትኩረት በምሳሌነት ያሳያል። መንግስት የመረጃ ፍሰትን የሚቆጣጠረው በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ ሚዲያዎች እና ፕሮፓጋንዳዎች ሲሆን ይህም የህዝብን ግንዛቤ ከትረካው ጋር በማጣጣም ነው። አህመድ እራሱን እንደ በጎ አድራጎት እና ለሀገር ደህንነት የሚተጋ መሪ አድርጎ በተመሳሳይ ጊዜ በሙስና እና በሰብአዊ መብት ረገጣ እየተሳተፈ ነው።

የአህመድ መንግስት ከሀገር ውስጥ ቁጥጥር በተጨማሪ የውጭ ፖሊሲውን የማኪያቬሊያን ስልቶችንም ይጠቀማል። መንግስት በዲያስፖራ ማህበረሰቦች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመጨፍለቅ እና ተቀናቃኝ ወገኖችን ለማዳከም ስውር ስራዎችን ሲሰራ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ፊት ለፊት ይይዛል። አህመድ የማኪያቬሊ የመንግስት ስራ መርሆዎችን በመጠቀም በአገር ውስጥም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ ስልጣኑን ለማጠናከር እና የአገዛዙን ረጅም እድሜ ለማረጋገጥ ይፈልጋል።

የማኪያቬሊያን አስተዳደር ዓለም አቀፍ ተጽእኖ

በኢትዮጵያ ያለው የአብይ አህመድ አገዛዝ ስለ ማኪያቬሊያን አስተዳደር አሳማኝ የሆነ ጥናት ቢያቀርብም፣ ስልቶቹ ግን በአስተዳደሩ ብቻ እንዳልሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል። በመላው አለም፣ አምባገነን መሪዎች ተግባራቸውን ለማፅደቅ እና በስልጣን ላይ እንዲቆዩ ለማድረግ ከማኪያቬሊ ፍልስፍና መነሳሻን አግኝተዋል።

እንደ ሰሜን ኮሪያ፣ ሩሲያ እና ቬንዙዌላ ባሉ ሀገራት መሪዎች ህዝቦቻቸውን ለመቆጣጠር ተመሳሳይ የማታለል፣ የመፍራት እና የተቃውሞ ስልቶችን ይጠቀማሉ። እነዚህ አገዛዞች ከምንም ነገር በላይ ለስልጣን መጠናከር ቅድሚያ የሚሰጡት ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ለሰብአዊ መብት፣ ለዲሞክራሲ እና ለሕግ የበላይነት መጥፋት ነው። የማኪያቬሊያን መርሆች ለእንደዚህ አይነት መሪዎች የዘመናዊ አስተዳደርን ውስብስብ ሁኔታዎች እንዲዳስሱ እና እርስ በርስ በሚተሳሰር እና ተለዋዋጭ በሆነ አለም ውስጥ ቁጥጥርን እንዲቀጥሉ ያስችላቸዋል።

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189024
ከ አስር በላይ ከተሞች በፋኖ ዕጅ ገብተዋል !| ፋኖ የባህር ዳር ቀበሌ 14 ገብቶ ሰራዊቱን አናወጠ | ም/ ጎጃም ከባድ ትንቅንቅ ጦሩ እጅ ሰጠ|
https://youtu.be/sFF2D7Bd-WA?si=NGMk2ITYoHcreTON

 

https://youtu.be/A2q3ZefEd8A?si=u2UGWOZqbffRCb4Z

የመንግስት ሰራዊትን ከድተው በምንጃር ከሰም ብርጌድ ፋኖን የተቀላቀሉ

 

https://youtu.be/FMvD4p2UkW8?si=2qIdbMXPg17Vd44h

ፋኖ የባህር ዳር ቀበሌ 14 ገብቶ ሰራዊቱን አናወጠ | ም/ ጎጃም ከባድ ትንቅንቅ ጦሩ እጅ ሰጠ|

https://youtu.be/8I076bGo3Zg?si=5j1aKdXm6NGbMZ2N

https://youtu.be/YKXRbQ1dm6A?si=gqPIN2KbyocRBGJS
https://amharic.zehabesha.com/archives/189049

Wednesday, February 28, 2024

‹‹ዳይኖሰርስ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብትል ሰላም ከሌለ ማንም ሊጎበኝ አይመጣም›› 5ቱ ገዳዬች ኮሬ ነጌኛ!!! ከኖቬል ሽልማት ወደ ሄግ ፍርድ ቤት!!!
(ክፍል ሁለት)                               ሚሊዮን ዘአማኑኤል (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

The Koree Nageenyaa:-In Ethiopia, a secret committee orders killings and arrests to crash rebels

የኦሮሙማ ‹‹ኮሬ ነጌኛ›› ዳይኖሰርስ በኦሮሞ ህዝብ ላይ በፀጥታና ደህንነት ኮሚቴ ሽፋን የተቆቆመው የገዳዬች ቡድን ዶክተር አብይ አህመድ ሥልጣን እንደያዘ ያቆቆመው ስውር ቡድን ሲሆን ከዋና መሥራቾቹ  ውስጥ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዜዳንት፤ ፍቃዱ ተሰማ፣የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዜዳንት፤ አወሉ አብዲ፣የኦሮሚያ የብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ፤ አራርሳ መርዳሳ፣ የኦሮሚያ ሠላምና ደህንነት ኃላፊ ስውር ቡድን በአደባባይ አሰራአምስት የከረዩ አባገዳዎች ገድለዋል፡፡ የአባገዳዎች  የጂምላ ግድያውና የመካነ-መቃብራቸው ኃውልት ከላይ በፎቶግራፍ ይስተዋላል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የ‹‹ኮሬ ነጌኛ›› የገዳዬች ቡድን በሰብዓዊ መብቶች ጥስት፣ በህግ ውጪ ግድያና ህገወጥ እስራት በመፈፀም በህብረተሰቡ ውስጥ ይታወቃል፡፡ ‹‹ኮሬ ነጌኛ›› ዋነኛ ዓላማዎቹ ውስጥ ‹‹የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት›› ማጥፋትና በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ተከታይ እንዳይኖረውና የጸጥታና ደህንነት ሥጋት እንዳይሆን ማድረግ ነው፡፡ የሮይተርስ የምርመራ ቡድን ጥናት መሠረት በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ህዝባዊ እንቢተኛነትና አመፅ እንዳይነሳ በህቡዕ የሚንቀሳቀሰው ገዳይ ቡድን ህገወጥ ግድያና እስራት  በመፈፀም የኦሮሞ ህዝብ በፍርሃትና በስጋት ውስጥ እንዲኖርና የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊትን እንዳይደግፍ አድርገውታል፡፡ የሮይተርስ የምርመራ ቡድን ሠላሳ የሚሆኑ የፌዴራልና የክልል ኃላፊዎችን፣ ዳኞችን፣ የጥቃቱ ሠለባ የሆኑ ሰዎችን ቃለ-መሠይቅ እንዳደረገላቸውና የፖለቲካና የህግ ዶሴዎችን እንደመረመረ ገልፆል፡፡ ቀሪውን ከድረገፁ ያንብቡ፡፡ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የደረሰውን የስብአዊ መብቶች ጥሰት፣ ግድያና አስገድዶ መሰወር ወንጀሎች በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (International Criminal court) ኮነሬል አብይ ከነገዳዬቻቸው መቅረባቸው አይቀርም በህብረት እንታገል፡፡“The Koree Nageenyaa committee in Ethiopia's Oromiya region, operating under Prime Minister Abiy Ahmed's government, has been implicated in human rights violations, including extra-judicial killings and illegal detentions. The committee aims to suppress the Oromo Liberation Army and address security challenges in Oromiya. A secretive committee of senior officials in Ethiopia's largest and most populous region, Oromiya, has ordered extra-judicial killings and illegal detentions to crush an insurgency there, a Reuters investigation has found. Reuters interviewed more than 30 federal and local officials, judges, lawyers and victims of abuses by authorities. The agency also reviewed documents drafted by local political and judicial authorities.”…………………………(1)

የኮነሬል አብይ ሲሶ መንግሥት!!! ፓርኮቹንና የጫካው ቤተ-መንግሥትን ብቻ ያስተዳድራል!!!

ትግራይ፣ አማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላ፣ኦሮሚያ፣ሶማሊያ፣ማዕከላዊ፣ደቡብ፣ ሲዳማና የደቡብ ምስራቅ ክልልና፣

ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልሎች ከፋሽስቱ አገዛዝ ሥርዓት ቁጥጥር ውጪ ሆኖል፡፡

የውጭ የጉዞ ምክር ወደ ኢትዮጵያ (Foreign travel advice Ethiopia) ፌብሪዋሪ 22 ቀን 2024እኤአ

!Warning FCDO advises against all travel to parts of Ethiopia……………….(2)

ጠቅላላ የሃገሪቱ ሁኔታ፡-የአሜሪካ፣ የእንግሊዝ፣ ጀርመን፣ የአውሮፓ ህብረት አገሮች፣ የካናዳ፣ አውስትራሊያ መንግሥቶች  ለመንገደኛ ዜጎቻቸው የሠጡት ማሳሰቢያ ይመለከታል፡፡  ወደ ኢትዮጵያ ለሚጎዙ ቱሪስቶች ማወቅ የሚገባቸው ጠቅላላ የሃገሪቱ ሁኔታ በተመለከተ፣ ድንገተኛ ህዝባዊ አመፅና ግጭት፣ ህዝባዊ አለመረጋጋት፣ ወንጀል፣ የመገናኛ አገልግሎት መቆረጥ፣ ሽብርተኛነትና የሰዎች እገታ በጠረፍማና በተለያዩ አካባቢዎች ሊከሰት ስለሚችም ተጎዦችን ያስጠነቅቃሉ፡፡ Reconsider travel to Ethiopia due to sporadic violent conflict, civil unrest, crime, communications disruptions, terrorism and kidnapping in border areas.Jul 31, 2023

- በኢትዮጵያ ካርታው ላይ የሚታየው ቀላ ያላ ቀለም ቱሪስቶች መጎዝ የሌለባቸው  ከባቢዎች ናቸው (Advise against all travel)

- በካርታው ላይ የሚታየው ቢጫ  ቀለም ቱሪስቶች መጎዝ የሌለባቸውና ዋነኛ የጉዞ   ከባቢዎች ናቸው( Advise against all but essential travel)

- በካርታው ላይ የሚታየው ፈዘዝ ያለ ቢጫ  ቀለም ቱሪስቶች ከመጎዛቸው በፊት ምክረ-ሃሳብ መስማት የሚጠበቅባቸው ከባቢዎች ናቸው( See our travel advise before  travelling)

የውጭ ጉዳይ ኮመንዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ The Foreign, Commonwealth & Development Office (FCDO) provides advice about risks of travel to help British nationals make informed decisions.

የዓለም አቀፍ ድንበር አካባቢዎች ለተጎዦች የተከለከለ ማሳሰቢያ  International border areas/ FCDO advises against all travel within:

- ከሱዳን ድንበር ሃያ ኪሎሜትር አካባቢ (20km of the border with Sudan)

- ከደቡብ ሱዳን ድንበር አስር ኪሎሜትር አካባቢ (10km of the border with South Sudan)

- ከኢትዮጵያ ድንበር መቶ ኪሎሜትር ርቀት ከሱማሌና ኬንያ  አንዲሁም ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ውስጥና አካባቢ(100km of the Ethiopian border with Somalia and Kenya in Ethiopia’s Somali region, and within

- ከኢትዮጵያ ድንበር ሠላሳ ኪሎሜትር ርቀት ከሱማሌ ውስጥ በፋፋን ዞን ከድንበር ከተሞች በስተቀርና ከዋጃሌ ባሻገር እና ከዋናው መንገድ መኃል ከጂጂጋና ዋጃሌ (30km of the Ethiopian border with Somalia in Fafan zone, except the border town and crossing at Wajale, and the principal road between Jijiga and Wajale)

- ከኬንያ ድንበር አስር ኪሎሜትር አካባቢ እንዲሁም ከዋናው መንገድና ከተሞች በስተቀር (10km of the border with Kenya, except for principal roads and towns )

- ከኤርትራ ድንበር አስር ኪሎሜትር አካባቢ (10km of the border with Eritrea)

(1) የትግራይ ክልል Tigray region የውጭ ጉዳይ ኮመንዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ ወደ ትግራይ ክልል የሚደረግ ጉዞን ሲያግዱ ከመቐለ ከተማና አገናኝ መንገዶች በስተቀር፣ ከማይጨው በስተ ደቡብ አቅጣጫ በኩል፣ ከአዲግራት በስተ ሰሜን አቅጣጫ በኩል፣ ከአቢ አዲ፣ አድዋና ሽሬ ምስራቅና ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በኩል፣ ከአባላ በስተ ምዕራብ በትግራይ አፋር ድንበር በኩል ለተጎዞች እግድ ተጥሎል፡፡(FCDO advises against all travel to Tigray region except the towns and connecting roads of Mekelle southward to Maychew  northwards to Adigrat west and north-westward to Abiy Addi, Adwa and Shire eastward to Abala on the Tigray-Afar border.

(2) አማራ ክልል Amhara region የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ ወደ አማራ ክልል የሚደረግ ሁሉንም ጉዞ አግዶል፡፡ FCDO advises against all travel to Amhara region.

(3) አፋር ክልል Afar region የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ  መቶ ኪሎሜትር ከትግራይ ድንበር  በስተ ሰሜን አንሰባ ከተማ አቅጣጫ በኩል፣ ሠላሳ ኪሎሜትር ከትግራይ ድንበር  በስተ ደቡብ አንሰባ ከተማ አቅጣጫ በኩል እንዲሁም አስር ኪሎሜትር በኤርትራ ድንበር በኩል ያለውን ሥፍራ የጉዞ እገዳ ያካትታል፡፡ FCDO advises against all travel to areas of Afar region within:   100km of the border with Tigray to the north of Anseba town  30km of the border with Tigray to the south of Anseba town  10km of the border with Eritrea

(4) ጋምቤላ ክልል Gambella region የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ ወደ ጋምቤላ ክልል የሚደረግ ሁሉንም ጉዞ አግዶል፡፡ FCDO advises against all travel to Gambella region.

(5) ኦሮሚያ ክልል Oromia region የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ ወደ ኦሮሚያ ክልል የሚደረግ የተለያዩ ቦታዎችን ጉዞ አግዶል፡፡ ከኬንያ ድንበር ከሚያዋስነው አስር ኪሎሜትር ርቀት ያለው ስፍራ፣ ከዋናው መንገድና ከተማ በስተቀር፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን መስቀለኛ መንገድ ደቡብና ምስራቅ አካባቢ እንዲሁም ሰሜን ሸዋ ዞን ኤ ስሪ መንገድ ፣ ምስራቅ ወለጋ ዞን ከአዲስ አበባ እስከ ጋምቤላ የመወስደው መንገድ፤ ምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ቄለም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ፣ የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ ምስራቅ ጉጂ እና ጉጂ ዞን አስር ኪሎሜትር ርቀት፣ ኦሮሚያ ክልለዊ መንግስት በምዕራብ ሸዋ ዞን በሁለቱም በኩል ያለ መንገድ መኃል ወለንጪቲ እና መታህራ በኩል ለቱሪስት መንገደኞች የተከለከለ መንገድ ነው፡፡  FCDO advises against all travel to these areas of Oromia region: within 10km of the border with Kenya, except for principal roads and towns north of (but not including) the A4 road in West Shewa zone south and west of (but not including) the A3 road in North Shewa zone West Wollega zone (including the main Addis Ababa to Gambella road), East Wollega zone, Kellem Wollega and Horo Gudru Wollega FCDO advises against all but essential travel to: West Guji and Guji zones the road and 10km either side of the road between Welenchiti and Metehara on the A1 in East Shewa zone of Oromia regional state.

(6) ሶማሊያ ክልል Somali Regional State የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ  ከኢትዮጵያ ድንበር መቶ ኪሎሜትር በኩል ሱማሊያና ኬንያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል መንግሥት፣  ከኢትዮጵያ ድንበር ሠላሳ ኪሎሜትር በኩል ሱማሊያ በፈፋን ዞን በኩል በሁለቱም በኩል ያለ መንገድና ከተሞች መኃል  በጂግጂጋ  እና ዋጃል በኩል፣  በሲቲ ዞን በኩል፣ በኖጎብ (የቀድሞው ፊቅ) በኩል፣ በጃራር (የቀድሞው ደጋሃቡር) በኩል፣ በሸበሌ (የቀድሞው ጎዴ) በኩል፣ ቆራሔ እና ዶሎ (የቀድሞው ዋርዴር) በኩል፣ ሊበን እና አፍዴር ዞን መቶ ኪሎሜትር ከሱማሌና ኬንያ ድንበር በኩል ያሉት መንገዶች ለቱሪስቶች የተከለከሉ ናቸው፡፡FCDO advises against all travel to within:  100km of the Ethiopian border with Somalia and Kenya in Ethiopia’s Somali region  30km of the Ethiopian border with Somalia in Fafan zone, except the border town and crossing at Wajale, and the principal road between Jijiga and Wajale. FCDO advises against all but essential travel to:   the Siti zone the Nogob (previously Fik)  Jarar (previously Degehabur)  Shabelle (previously Gode)  Korahe and Dollo (previously Warder) areas of Liben and Afder zones more than 100km from the Somalia and Kenya borders

(7) ማዕከላዊ፣ ደቡብ፣ ሲዳማና የደቡብ ምስራቅ ክልል Central, Southern, Sidama and South West regions (formerly SNNPR) የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ  የጉዞ እገዳ ማስጠንቀቂያ በማድረግ  በኮንሶ ልዩ ዞን የደቡብ ኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ድንበር አስር ኪሎሜትር ርቀት ከደቡብ ሱዳንና ኬንያ ድንበር በኩል ተጎዦች አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡ FCDO advises against all but essential travel: to the Konso Special Woreda of the Southern Nations, Nationalities, and Peoples’ Region (SNNPR) within 10km of the borders with South Sudan and Kenya

(8) ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል Benishangul-Gumuz region የውጭ ጉዳይ ኮመን ዌልዝና ዲቨሎፕመንት ኦፊስ  የጉዞ ማሳሰቢያ መሰረት በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ድንበር በኩል ሃያ ኪሎሜትር ርቀት ከሱዳን ወሰን በኩል መተከል ዞን እና ማኦኮሞ ልዩ ዞን እግዱ  ያካትታል፡፡ FCDO  advises against all travel to these areas of Benishangul-Gumuz region: within 20km of the border with Sudan the Metekel zone and Maokomo special zone. FCDO advises against all but essential travel to the rest of Benishangul-Gumuz region.

በህብረ ብሔር ኃይሎች ግንባር በማቆቆም የሽግግር መንግሥት በመመሥረት የብልጽግና መንግሥትን እናውርድ!!!

ምንጭ

(1)In Ethiopia, a secret committee orders killings and arrests to crush rebels/Reuters/Feb 23, 2024,

(2) (Foreign travel advice Ethiopia) !Warning FCDO advises against all travel to parts of Ethiopia. Warnings and insurance/ Still current at: 22 February 2024/Updated: 26 January 2024
https://amharic.zehabesha.com/archives/188998
ከመቅዳላ የተዘረፈውና ለጨረታ የቀረበው ቅርሳችን…!! ለጨረታው ቀረበው የመቅደላ ቅርሳችን ወደ ሀገሩ፣ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ድምፃችንን በአንድነት እናሰማ!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)

የኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ባለውለታ የሆኑት የነፍሰ ኄር ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስት ልጅ የሆኑት ዶ/ር አሉላ ፓንክረስት፤ በውጪ ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶች አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ በመሆን እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታትም በተለይ በመቅደላ ዘመቻ ወቅት በእንግሊዝና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ተዘርፈው የተወሰዱ ቅርሶቻችንን በማስመለስ ረገድ ትልቅ ሥራ እየሠሩ ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም የሠራ ባልደረባ ነበርኩበት ጊዜ እንደማስታውሰውም፤ ወላጅ፣ አባታቸው ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስት (ባለቤታቸው ሪታ ፓንክረስት)፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የነበሩት ፕ/ር አነድርያስ እሸቴ፣ የታሪክና የቅርስ ጥበቃ ምሁራን፣ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ወዳጆች ማኅበር፤ በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር በሚገኙ የኢትዮጵያ ታሪክና ቅርስ ተቆራቋሪ በሆኑ ወዳጆች በተቋቋመው AFROMET በተባለ ድርጅት አማካኝነት- የዐፄ ቴዎድርስ ክታብ፣ የጸሎት መጽሐፋቸው፣ ጎራዴያቸውና ሌሎች ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው ነበር፡፡

እነዚህ በመቅደላው ዘመቻ ተዘርፈው ወደ እንግሊዝ ተወስደው የነበሩና የተመለሱ ብርቅዬና ውድ የሆኑ ቅርሶቻችንም በአንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፤ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ቤተ-መዘክር ውስጥ ለሕዝብ ቀርበው እንደነበርም አስታውሳለሁ፡፡

ይህ የእነ ነፍሰ ኄር ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስትና በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር ያሉ የኢትዮጵያ ታሪክና ቅርስ ተቆርቋሪዎች ጥረት ዛሬም ሳይቋረጥ- በፕ/ር ሪቻርድ ፓንከረስት ልጅ በሆኑት በዶ/ር አሉላ ፓንክረስት ቀጥሎ ባለፉት ጥቂት ወራትም በመቅደላ ዘመቻ የተዘረፉ ታቦታትን ጨምሮ የተለያዩ ቅርሶቻን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡

ታቦታቱ በእንግሊዝ፣ የለንደን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በተደረገ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ለቤተክርስቲያኒቱ እንዲመለስም ተደርጓል፡፡

ሌሎች ቅርሶቻችንም በኢትዮጵያ እንግሊዝ አምባሳደር በሆኑት አምባሳደር ተፈሪ፤ ለቅርስ ጥበቃ ባለ ሥልጣን በአካል ተገኝተው ማስረከባቸውን ከመገናኛ ብዙኃን ተከታትለናል፡፡ ይህ ብዙዎቻችንን ከልብ ያስደሰተ፤ ይበል የሚያሰኝ ሥራ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ከሰሞኑን ደግሞ፤ ከመቅደላ የተዘረፈ እጅግ የተዋበና በልዩ ጥበብ የተሠራ ጋሻ በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ለጨረታ መቅረቡን ዶ/ር አሉላ ገልጸውልኛል፡፡

ይህ የኢትዮጵያ ቅርስ የሆነ ጋሻ ወደ ሀገሩ እንዲመለስም የቅርስ ተቆርቋሪ የሆኑ ሁሉ በቲወተር (በኤክስ) እና በሌሎች ሶሻል ሚዲያ የትስስር ገጾች ድማፃችንን እንድናሰማ የቪዲዮ መልእከት አስተላልፈዋል፡፡

ይህ ቅርስ፣ ጋሻ የኢትዮጵያውያን፣ የአፍሪካና የመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተጋድሎ ትልቅ ትእምርት/ተምሳሌት ነው፡፡ ይህ ለጨረታ የቀረበውና ከ150 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ቅርስ ‹ጋሻ› በክብር ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ለታሪካችንና ለቅርሶቻችን የምንቆረቆር ኢትዮጵያውን ሁሉ ድምፃችንን በአንድነት ሆነን ልናሰማ ይገባናል፡፡

ይህ የኢትዮጵያውያን ጥበብ የፈሰሰበትና እጅግ የተዋበ ቅርሳችን፤ ‹ጋሻ› የኢትዮጵያውያን፣ የአፍሪካና የመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተጋድሎ ትልቅ ትእምርት/ተምሳሌት ነው ስልም በምክንያት ነው፡፡

አውሮፓውያን ቅኝ ገዢ ኃይላት ጥቁር ሕዝብ ከእንሰሳ ያነሰ ስብእና ያለው፤ የራሱ ታሪክ፣ ሥልጣኔ፣ ዕድገት፣ ባህል… ወዘተ. የሌለው ብለው ድመድመው አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ተቀራምተው ሕዝቦቿን በባርነት ሲያግዙ በነበረበት ዘመን- አንድ የጥቁር ምድር/የሐበሻ ንጉሥ፤ የቋራው አንበሳ/ዐፄ ቴዎድሮስ የእንግሊዝንና የአውሮፓውያንን መልእክተኞች እግረ ሙቅ ውስጥ አስገብቶ ራሷን ታላቋ ብሪታንያ እያለች ከምትጠራውና የዓለም 1/3 በቅኝ ከምትገዛው ሀገር ጋር እኩል መደራደሪያ እድርገዋቸው ነበር፡፡

መላው አፍሪካና ጥቁር ሕዝብ በባርነትና በቅኝ ግዛት ቀምበር ስር ወድቆ ሲማቅቅ ነበረበት ወቅት የሐበሻው ጥቁር ንጉሥ፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ሁላችንም በፈጣሪ ፊት እኩል ነን፤ በሚል መርሕ ራሳቸውን ከሁሉም በላይ ነን ብለው የሚያስቡትን አውሮፓውያንን/ነጮችን- በኢትዮጵያውያን የነጻነት እሳቤና ከፍ ባለ የመንፈስ ልእልና ድል በማድረግ ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነትና የጀግንነት ኩራት ሆነዋል፡፡

ይህ ከመቅዳላ ተዘርፎ ለጨረታ የቀረበው ቅርሳችን- ‹ጋሻ› የዚህ ኢትዮጵያዊነት የነጻነት እሳቤ፣ የሰው ልጆች እኩልነት መገለጫና የመንፈስ ልእልና ትእምርት/ምልክት ነውና ቅርሳችን ወደ ሀገሩ፤ ኢትዮጵያ እንዲመለስ፤ ከዶ/ር አሉላ ፓንክረስትና ኬሎች ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጋር በአንድነት ሆነን ድምፃችንን እናሰማ!!

የዶ/ር አሉላ ፓንክረስት ከመቅዳላ ተዘርፎ የነበረና ለጨረታ የቀረበውን ቅርሳችንን/ጋሻ  ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ሁላችንም በጋራ ድምፃችንን እንድናሰማ የቪዲዮ መልእክት ያስተላለፉበት ሊንክ እንሆ!!

ሰላም ለኢትዮጵያ!!

 

https://youtu.be/kCNUOPwOKHE?si=asxKpqiewbFxtCR7
https://amharic.zehabesha.com/archives/189001

Tuesday, February 27, 2024

ጎጃም ተጋድሎው ተቀጣጥሏል | በአማራ በበርካታ ቦታዎች ውጊያዎች እየተደረጉ ነው፥ ትልልቅ ከተሞች በፋኖ እጅ ገብተዋል፥ የአምኒስቲ ሪፖርት፥ ኮሬ ነጌኛ፥ ሀዋሳ ሀዘን ላይ ናት
https://youtu.be/aiLIE6XPpWg?si=FlJBn5Chp1pAl852

https://youtu.be/8M7uD-YSrzI?si=LUP8bTyGnsr1cGUt

 በአማራ በበርካታ ቦታዎች ውጊያዎች እየተደረጉ ነው፥ ትልልቅ ከተሞች በፋኖ እጅ ገብተዋል፥ የአምኒስቲ ሪፖርት፥ ኮሬ ነጌኛ፥ ሀዋሳ ሀዘን ላይ ናት
https://amharic.zehabesha.com/archives/188982
በአማራ በበርካታ ቦታዎች ውጊያዎች እየተደረጉ ነው፥ ትልልቅ ከተሞች በፋኖ እጅ ገብተዋል፥ የአምኒስቲ ሪፖርት፥ ኮሬ ነጌኛ፥ ሀዋሳ ሀዘን ላይ ናት
 

https://youtu.be/8M7uD-YSrzI?si=LUP8bTyGnsr1cGUt

 በአማራ በበርካታ ቦታዎች ውጊያዎች እየተደረጉ ነው፥ ትልልቅ ከተሞች በፋኖ እጅ ገብተዋል፥ የአምኒስቲ ሪፖርት፥ ኮሬ ነጌኛ፥ ሀዋሳ ሀዘን ላይ ናት
https://amharic.zehabesha.com/archives/188982

Monday, February 26, 2024

ቆሬ ነጌኛ ወይም የፀጥታ ኮሚቴ የተባለው አፋኝ ቡድን የገደላቸው high profile ሰዎች መካከል
1. ኢንጂነር ስመኘው በቀለ

2. ጀነራል አሳምነው ፅጌ

3. ዶ/ር አምባቸው መኮንን

4. ጀነራል ሰአረ መኮንን

5. ጀነራል ገዛኢ አበራ

6. አቶ ምግባሩ ከበደ

7. አቶ እዘዝ ዋሴ

8. አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ

9. አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ

10. ቴዲ ቡናማው

ከነ ጀነራል አሳምነውግድያ ጋር በተያያዘ የተረሸኑ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በልዮ ሁኔታ የሰለጠኑ ጀግናዎች የአማራ ልዮ ሀይል አባላት (ብዛት850)  ቁጥራቸው ያልታወቀ የኦህዴድ ፓርቲ ተቀናቃኝ ናቸው የተባሉ የአማራ የኦሮሞና የሌሎች ብሄር ወጣቶችና ጎልማሶች ፖለቲከኞች ጋዜጠኞች አክቲቪስቶች ወዘተ

በወለጋ በሻሸመኔ በሀረር በአርሲ በተለያዮ ግዜያት ማንነታቸው አማራ በሆኑ ሰላማዊ ሰዎች ላይ በተደጋጋሚ የተፈፀሙት የዘር ማጥፋት ወንጀሎች በአዲስ አበባ ከተማ የባልደራስ የአብን ወዘተ ፖለቲካ ፓርቲ ደጋፊ ናችሁ ተብለው የተፈረጁ እንዲሁም በዚሁ አዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይና አማራ ብሄር ተወላጆችን ያለፍርድ ቤት ትዛዝ አፍሶ ወደ ማጎሪያ ስፍራ በመውሰድ ማሰቃየት መግደል ማሸበር

እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን ግድያዎች የፈፀመው ቡድን የሚያሰማራው አብይ አህመድ የፈጠረው informal ስውር ገዳይ ቡድን መሆኑን International Community ስለደረሱበትና መረጃና ማስረጃ ስላላቸው በReuters ሚድያ ላይ publish አድርገውታል:: ቀጣዮ እነዚህ ወንጀለኞች በአለም አቀፍ ፍርድ ቤት (international criminal court) እደሚከሰሱ ምንም ጥያቄ የለውም:: የአለም አቀፍ ማህበረስቡ አብይ አህመድንና ቡድኑን ተጠያቂ ለማድረግ ሁኔታዎች እያመቻቸ ለመሆኑ ጥያቄ የለውም::

Dagmawi M. Belay
https://amharic.zehabesha.com/archives/188978
በዝቋላ ገዳም አራት መነኮሳት መገደላቸውንየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክስርቲያን አስታወቀች
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ውስጥ የሚኖሩ አራት የገዳሙ መነኮሳት በታጣቂዎች መግደላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክስርቲያን አስታውቃለች።

ቤተክርስቲያኒቱ የህዝብ ግንጙነት መምሪያ ባወጣው መረጃ መሰረት ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ/ም ታጣቂዎቹ አባቶችን አግተው ወደ በረሃ ወስደዋል። የታገቱትን ለማስለቀቅ ገዳሙ ጥረት እያደረገ በነበረበት ወቅትም የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ/ም የገዳሙን መጋቢ አባተክለማርያም አስራትን፣ ጨምሮ አራት መነኮሳት መገደላቸውን እና አብረው ከነበሩት ውስጥ አንድ አባት ብቻ በህይወት መትረፋቸው ተገልጿል፡፡

የቤተ ክርስቲያኗ የህዝብ ግንጙነት መምሪያ ባወጣው መረጃ መነኮሳቱ የተገደሉት መንግስት «ኦነግ ሸኔ» እያለ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን ነው። በአሁኑ ወቅትም መነኮሳቱ እና የገዳሙ ቅርሶች አደጋ ላይ በመሆናቸው የፌደራል እና የክልሉ የፀጥታ አካላት ጥበቃ እንዲያደርጉ ቤተክርስቲያኒቱ ጥሪ አቅርባለች። በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ የሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በርካታ መነኮሳት እንዲሁም ቅርሶች የሚገኙበት ጥንታዊያን እና ታሪካዊ ገዳም ሲሆን፤ በተለያዩ ጊዜያት ዘረፋ፣ ቃጠሎ እና ከባድ ጉዳቶችን እንደደረሰበትም ቤተ ክርስቲያኗ ያወጣችው መግለጫ ያመለክታል።

DW
https://amharic.zehabesha.com/archives/188955
የኮሬ ነጌኛ: በኦሮሚያ ክልል ለሚፈፀም ከሕግ ውጭ ግድያ
በኦሮሚያ ክልል ለሚፈፀም ከሕግ ውጭ ግድያ እና እስራት አንድ ከፍተና የባለስልጣናት ሚስጥራዊ ኮሚቴ ትዕዛዝ ሲሰጥ መቆየቱን ሮይተርስ የዜና ወኪል ገለፀ

በኢትዮጵያ የከፍተኛ ባለሥልጣ

ናት የሚስጥራዊ ኮሚቴ፣ብዙ ህዝብ በሚኖርበት የኦሮሚያ ክልል፤ አማጽያንን ለመደምሰስ በሚል ከሕግ አግባብ ውጭ ግድያ እና ሕገወጥ እስራት እንዲፈፀም ትዕዛዝ ማስተላለፉን የሮይተርስ የምርመራ ግኝት አመልክቷል።

ሮይተርስ በዚህ ምርመራው ከ30 በላይ የፌደራል እና የአካባቢ ባለስልጣናትን ፣ዳኞችን፣ጠበቆችን፣በባለሥልጣናት እና በደል የሚደርስባቸውን ሰለባዎች ማነጋገሩን ጠቁሟል።

የዜና ምንጩ በሀገር ውስጥ ፖለቲካ እና የፍትህ ባለስልጣናት የተነደፉ ሰነዶችንም መገምገሙንም አስታውቋል።ከእነዚህ ቃለ መጠይቆች እና ሰነዶችም በኦሮምኛ ቋንቋ «ኮሬ ነጌኛ»ወይም የደህንነት ኮሚቴ የሚባለውን አካል አሠራርን ይፋ የሚያደርግ መረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መገኘቱን የዜና ምንጩ ገልጿል።

-

እንደ ሮይተርስ የፀጥታ ኮሚቴው በኦሮምኛ ቋንቋ ፤«ኮሬ ነጌኛ» ሥራ የጀመረው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ ከወራት በኋላ ሲሆን፤ከጎርጎሪያኑ 2018. ዓ/ም በፊት ግን ኮሚቴው አለመኖሩን ዘግቧል።

አምስት የአሁን እና የቀድሞ የመንግስት ባለስልጣናት ነገሩኝ ብሎ ሮይተርስ እንዳሰፈረው፤ ይህ ኮሚቴ ዓላማው የራስን እድል በራስ ለመወሰን ለዓመታት የዘለቀውን የኦሮሞ ነፃ አውጪ ጦር የሽምቅ ውጊያ እንዲያበቃ ማድረግ ነው።

ከሮይተርስ ከአምስቱ ምንጮች አንዱ የቀድሞ የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሚልኬሳ ገመቹ ሲሆኑ፤ እሳቸውን ጨምሮ አምስቱ ባለስልጣናት እንዳሉት ፤ በጎርጎሪያኑ 2019 ዓ/ም አዲስ የኦሮሞ ህዝብ አመፅ ሲቀሰቀስ ጠንከር ያለ እርምጃ በመውሰድ ይህ ኮሚቴ የመሪነት ሚና ነበረው።

የኮሬ ነጌኛ እንቅስቃሴዎችን የሚያውቁ ሰዎች በኮሚቴው ትዕዛዝ በርካታ ግድያዎች ተፈጽመዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እስር ተካሂዷል ሲል ሮይተርስ ባወጣው ዝርዝር የምርመራ ዘገባ አመልክቷል።

Dq
https://amharic.zehabesha.com/archives/188963
በዝቋላ ገዳም አራት መነኮሳት መገደላቸውንየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክስርቲያን አስታወቀች
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ውስጥ የሚኖሩ አራት የገዳሙ መነኮሳት በታጣቂዎች መግደላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክስርቲያን አስታውቃለች።

ቤተክርስቲያኒቱ የህዝብ ግንጙነት መምሪያ ባወጣው መረጃ መሰረት ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ/ም ታጣቂዎቹ አባቶችን አግተው ወደ በረሃ ወስደዋል። የታገቱትን ለማስለቀቅ ገዳሙ ጥረት እያደረገ በነበረበት ወቅትም የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ/ም የገዳሙን መጋቢ አባተክለማርያም አስራትን፣ ጨምሮ አራት መነኮሳት መገደላቸውን እና አብረው ከነበሩት ውስጥ አንድ አባት ብቻ በህይወት መትረፋቸው ተገልጿል፡፡

የቤተ ክርስቲያኗ የህዝብ ግንጙነት መምሪያ ባወጣው መረጃ መነኮሳቱ የተገደሉት መንግስት «ኦነግ ሸኔ» እያለ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን ነው። በአሁኑ ወቅትም መነኮሳቱ እና የገዳሙ ቅርሶች አደጋ ላይ በመሆናቸው የፌደራል እና የክልሉ የፀጥታ አካላት ጥበቃ እንዲያደርጉ ቤተክርስቲያኒቱ ጥሪ አቅርባለች። በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ የሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በርካታ መነኮሳት እንዲሁም ቅርሶች የሚገኙበት ጥንታዊያን እና ታሪካዊ ገዳም ሲሆን፤ በተለያዩ ጊዜያት ዘረፋ፣ ቃጠሎ እና ከባድ ጉዳቶችን እንደደረሰበትም ቤተ ክርስቲያኗ ያወጣችው መግለጫ ያመለክታል።

DW
https://amharic.zehabesha.com/archives/188955

Sunday, February 25, 2024

በአባይ ማዶና በሸዋ መጣ | 5ቱ የደም ነጋዴዎች | ህዝቡ ሆ ብሎ ወጣ መንገዶች ተዘጋጉ
https://youtu.be/QqpglM1kK9E?si=BHnSjDfDMdpmcIOb

 

https://youtu.be/8bcr4xvYfQ0?si=4W1Phb1Km7ghD2yL

 

ታየ ደንደአ ስለነዚህ ሰዎች የሚያውቀው ሚስጥር | የተገደለው ሰላይ የተመስገን ጥሩነህ የቅርብ ዘመድ

https://youtu.be/D_zCiDBFmQ4?si=iMny6xUl1Ob-YzUk

ህዝቡ ሆ ብሎ ወጣ መንገዶች ተዘጋጉ
https://amharic.zehabesha.com/archives/188945
በአባይ ማዶና በሸዋ መጣ | 5ቱ የደም ነጋዴዎች | ህዝቡ ሆ ብሎ ወጣ መንገዶች ተዘጋጉ
https://youtu.be/QqpglM1kK9E?si=BHnSjDfDMdpmcIOb

 

https://youtu.be/8bcr4xvYfQ0?si=4W1Phb1Km7ghD2yL

 

ታየ ደንደአ ስለነዚህ ሰዎች የሚያውቀው ሚስጥር | የተገደለው ሰላይ የተመስገን ጥሩነህ የቅርብ ዘመድ

https://youtu.be/D_zCiDBFmQ4?si=iMny6xUl1Ob-YzUk

ህዝቡ ሆ ብሎ ወጣ መንገዶች ተዘጋጉ
https://amharic.zehabesha.com/archives/188945

Saturday, February 24, 2024

በኦሮሞ እልፍኝ የተደበቁ ሳጥናኤል አብይ እና ጥቂት እፉኞች ፥ የጨነቀለት መከራዉን ሲያሳዩት የነበረውን ኦሮሞ አድነን እያሉ ነው
ካሌብ ታደሰ

የካቲት 10, 2016

በኦሮሞ እልፍኝ የተደበቁ ሳጥናኤል አብይ እና ጥቂት እፉኞች ፥ የጨነቀለት መከራዉን ሲያሳዩት የነበረውን ኦሮሞ አድነን እያሉ ነው:: ሲጀምር ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ ከህዝብ ጋር ችግር የለብትም ኖሮበትም አያውቅም!!

በአዳማ (ናዝሬት) ጨፌ በተባለው ምክር መሰብሰቢያ አዳራሽ በቅርቡ በነበረው ስብስባ ላይ ሺመልስ አብዲሳ፣ አሁን ያለውን ዘረኛ ስርዓት፣ የኦሮሞ ህዝብ እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል፡፡ "ኦሮሞ የሆነ ሁሉ ፋኖን መዋጋት አለበት፣ ፋኖ ኦሮሞን ሊያጠፋ ነው " በሚል፡፡

 

ይህን ያለው ፣ በአዳማ (ናዝሬት) ጨፌ በተባለው ምክር መሰብሰቢያ አዳራሽ ነው፡፡ በአዳማ (ናዝሬት)  ከ75% በላይ ነዋሪ ኦሮምኛ የማይናገር ነው፡፡ ግን በአዳማ ጨፌው ሲሰበሰብ ሙሉ በሙሉ በኦሮምኛ ብቻ ስለሆነ፣ አብዛኛው የናዝሬት ነዋሪ አይከታተለውም፡፡ እርግጠኛ ነኝ ከጨፌ አባላት ውስጥም የአዳማ (ናዝሬት) ልጆች የሉበትም፡፡ በአዳማ (ናዝሬት) የተወለዱና ያደጉ፡፡ ይህም ምን ያህል የኦሮሞ ክልል የሚባለው ዘረኛና አፓርታይዳዊ መሆኑን አመላካች ነው፡፡

ኦሮሞ ባለፉት 30 አመታት፣ በተለይም ደግሞ ላለፉት 6 አመታት ምን ተጠቅሞ ነው:: በእነዚህ ጥቂት አመታት ውስጥ ከብልጽግና ይልቅ ከፍተኛ ውድመትና ጥፋት ደርሷል ስለሆነም አሁን ያለውን ስርዓት ለማስጠበቅ የሚነሳው ? አዎን በአዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ በኦሮሞ ስም የዘረፉ፣ የተጠቀሙ የተወሰኑ ከኦሮሞ ማህበረሰብ የሆኑ ሰዎች አሉ፡፡ ግን ከ98 በመቶ የሚሆነው ኦሮሞ፣ ምን ያገኘው ነገር አለ ?

የኦሮሞ ስቃይ በአብይ አህመድ እና በሺመልስ አብዲሳ፣  የስልጣን ዘመን ኦሮሞ፣ ምን ያገኘው ነገር አለ ? ዛሬ አርብ  የካቲት 15, 2016 ለንባብ የበቃው የሮይተርስ ዘገባ ባደረገው ምርመራ “በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ያቀፈ ሚስጥራዊ ወይንም የህቡዕ አደረጃጀት አለው የተባለው ኮሚቴው ስያሜው “ኮሬ ነጌኛ” ወይንም የጸጥታ ኮሚቴ መሆኑን እና አብይ አህመድ ጠ/ሚኒስትር ሁነው በተሾሙ ወራት ውስጥ የተቋቋመ መሆኑን የዜና አውታሩ በሪፖርቱ ጠቁሟል። የተቋቋመበትም ዋነኛ አላማ በክልሉ ከሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ሀይል ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር በተገናኘ በኦሮምያ ክልል የተነሳውን ተቃውሞ  ለመቆጣጠር መሆኑን አመላክቷል። ይህ የህቡዕ አደረጃጀት ከህግ አግባብ ውጭ ግድያ እና ህገ ወጥ እስራት ትእዛዝ ያስተላልፋል ተፋጻሚነቱን ይከታተላል” ሲል ተናግሯል። ይህ ሚስጥራዊው አካል “ኮሬ ናጌንያ” “Koree Nageenyaa” የሚል መጠሪያ ያለው ሲሆን አብይ አህመድ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣን ከያዙ ከጥቂት ወራት በኋላ ወደ ስራ መገባቱን አመልክቷል።

የዜና አውታሩ አክሎም " ኮሬ ናጌንያ በአቢይ ብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቢሮዎች ውስጥ የሚገናኙ ሲሆን ኮሚቴው የሚመራው በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ መሆኑንም አክለውም የኮሚቴ አባላት በሙሉ ኦሮሞ ናቸው።  በአባልነት የክልሉ ከፍተኛ የጸጥታ እና የፖለቲካ ባለሥልጣናት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል. ከነሱም ወስጥ የኦሮሚያ የብልጽግና ፓርቲ መሪ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ተሰማ በኮሚቴው ውስጥ ተቀምጠዋል፣ የኦሮሚያ የጸጥታ ኃላፊ የሆኑት አራርሳ መርዳሳ እና ሌሎች ግማሽ ደርዘን የሚሆኑ ሌሎች የሀገር ውስጥ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሃላፊዎች በኮሚቴው ውስጥ ተቀምጠዋል ብለዋል ምንጮች።  ይህ ሚስጥራዊው አካል “ኮሬ ናጌንያ” committee is little known beyond a tight official circle” ጥብቅ ከሆነው ኦፊሴላዊ ክበብ በዘለለ ብዙም አይታወቅም።

“ According to a Reuters report “the Koree Nageenyaa – Security Committee in the Oromo language - which began operating in the months after Prime Minister Abiy Ahmed came to power in 2018. The committee’s existence has not been previously reported.” ሮይተርስ የምርመራ ሪፖርቱን ለማጠናከር  “ከ30 በላይ የፌደራል እና የአካባቢ ባለስልጣናትን፣ ዳኞችን፣ ጠበቆችን እና በባለስልጣናት በደል ሰለባዎችን ቃለ መጠይቅ አድርጓል” ብሏል። በተጨማሪም በክልሉ የሚገኘውን “የኮሬ ናጌንያ” ስራዎችን ያውቃሉ የተባሉ ግለሰቦችን አነጋግሯል - አንዳንዶቹ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀዋል። ሚስጥራዊው አካል በክልሉ ውስጥ ግድያዎች እና እስራት ጋር የተያያዘ ነው:: ሮይተርስ በተጨማሪም የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩትን ሚልኬሳ ​​ገመቹን ጠቅሶ ስለ ኮሬ ናጌንያ ከመጋቢት 2019 ጀምሮ እንደሚያውቅ ዘግቧል።

የዚህ ቡድን ተግባር የሚፈልጋቸው ሰዎች እያሳደደ መግደል እና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጪ  ማሰር መሆኑም ተጠቁሟል. “The people familiar with Koree Nageenyaa's activities attributed dozens of killings to the committee's orders and hundreds of arrests. Among the killings, they said, was a massacre of 14 shepherds in Oromiya in 2021 that the government has previously blamed on OLA fighters.”

በኮሚቴው በተላለፈ ትእዛዝ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች፣ “የጸጥታ ስጋቶች” ናቸው በሚል የተፈጸሙ ጅምላ እስሮች በዜና አውታሩ ሪፖርት ተካተዋል። በ2014 ዓ.ም በከረዩ አባገዳዎች አባላት ግድያ ላይ በሰበሰባቸው እና ባገናዘባቸው ማስረጃዎች መሰረት 14 የከረዩ የሚችሌ ገዳ አባላት በመንግሥት የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በግዳጅ ወደ ጫካ ቦታ ተወስደውና የአካባቢ አስተዳደር ሰዎች ባሉበት ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በጥይት ተመተው የተገድለዋል ብሏል።  እስቲ ጉጂ ያላችሁ ተናገሩ ? ወለጋ ያላችሁ ኦሮሞዎች ተናገሩ፣ ሰሜን ሸዋ ያላችሁ ተናገሩ ? እኔ ባለኝ መረጃ ፣  ኦሮሞ ነን የሚሉ ኦነጋዊ ገዢዎች ስልጣን እንደያዙበት ዘመን፣ ኦሮሞ በታሪኩ ተሰቃይቶ አያውቅም፡፡ በ 2014 th 2015 አመተ ምህረት በምስራቅ ወለጋ የተለያዩ ወረዳዎች በኦሮሚያ ልዩ ኃይል እና በመከላከያ የተገደሉ የአማራ ተወላጆች በመቶዎች የሚቆጠሩ ናቸው:: በእስር ላይ የሚገኙትም ተገርፈዋል፣ እንዲሰቃዩ ተደርገዋል ያለው ሮይተርስ ጣልቃ ለመግባት እና ለመገዳደር የሞከሩ ዳኞች እና ጠበቆች ማስፈራራት ደርሶባቸዋል ሲል ገልጿል።

ብዙ ኦሮሞዎች አሁን የፋኖን ዓላማ እየተረዱ የመጡ ይመስላል፡፡ በሺሆች የሚቆጠሩ እነ ብርሃኑ ጁላ የላኳቸው የኦሮሞ ተዋጊዎች አልቀዋል፡፡ ሞተዋል፡፡ ቁስለኞች ሆነዋል፡፡ ይህ በኦሮሞ እናቶችና አባቶች ዘንድ ፣"ለምንድን ነው ልጆቻችን የሞቱት ?" የሚል ጥያቄዎች እየተነሱ፡፡ ይህ አሁን ያለው አገዛዝ ልጆቻችን አታሎ፣ አፍሶ አስፈጃቸው እያሉ ነው፡፡ በሺሆች የሚቆጠሩም ተማርከው በሰላም ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመልሰዋል፡፡ ለህዝቡ እየተናገሩ ነው፡፡ ያዩትን፣ የሆነውን ሁሉ፡፡ አገዛዙ የርሱ ጭፍሮችን፣ ይዞ ንጹሃንን በማንነታቸው ፣ አማራ ስለሆኑ ብቻ ሲጨፈጭፍ፣ ፋኖዎች ተመሳሳይ የበቀል እርምጃዎች በመውሰድ ፣ ኦሮሞን በኦሮሞነቱ አላጠቁም፡፡ ይሄንን ደግሞ በአማራ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ያሉ ኦሮሞዎች ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ፋኖዎች ሺመልስ አብዲሳ እንዳለው ቢሆኑ ኖሮ፣ በፍቼ፣ በወለንጭቲ፣ በገብረ ጉራቻ፣ በመኪጡሪ፣ በኢጄሬ ሰሜን ሸዋና በኢጀሬ ምስራቅ ሸዋ፣ በሞጆ፣ በከሚሴ፣ በሸኖ፣ በመንዲዳ፣ በመተሃራ ወዘተ ባሉ አካባቢዎች እልቂት ይፈጠር ነበር፡፡ ፋኖ ሃላፊነት ሚሰማው፣ በዘር ጥላቻ ላይ ያልተመሰረተ እንደሆነ ብዙ ኦሮሞዎች እያወቁ ነው፡፡

ፋኖ ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ማንም ኢትዮጵያዊ ባህሉን፣ ቋንቋዎች፣ ቅርሱን ጠብቆ፣ በቋንቋዉ መንግስታዊ አገልግሎት እያገኘ፣ በወደደው ቦታ መኖር የሚችልንበት ስርዓት እንዲኖር ነው የሚታግለው፡፡  ሺመልስ አብዲሳ፣ አዳነች አበቤ፣ አብይ አህመድ መቀመጫቸው አዲስ አበባ ነው፡፡ የኦሮሞ ክልል ጨፌ ደግሞ ናዝሬት ነው፡፡ ፋኖዎች የብልጽግና ዘረኛውን አገዛዝ ለመገርሰስ፣ ወታደራዊ ዘመቻዎች ባሌ ዲንሾ፣ ወይንም ምእራብ ወለጋ ጉሊሶ ወይም አርሲ ኮፈሌ አይደለም የሚንቀሳቀሱት፡፡ ከ90% በላይ ኦሮሞ ባለበት አካባቢ፡፡ ሺመልስ አብዲሳ፣ አዳነች አበቤ፣ አብይ አህመድ መቀመጫቸው አዲስ አበባ ነው፡፡ አዲስ አበባንና አዲስ አበባን አካባቢ፣ እነ ናዝሬትን ከተቆጣጠሩ፣ የኦሮሞ ብልጽግና አገዛዝ ሙሉ ለሙሉ ያከትምለታል፡፡ በነዚህ አካባቢዎች ደግሞ ፣ በአዲስ አበባ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ፣ በናዝሬት፣ በደብረ ዘይት፣ በአጠቃላይ በምስራቅ ሸዋ ዞን የሚኖረው ማህበረሰብ አብዛኛው ኦሮሞ ያልሆነ፣ ፋኖን የሚደገፍ ነው፡፡ ያሉት ኦሮሞዎች ቢሆኑ፣ ሚኒሊካዊ ኦሮሞዎች እንጂ ጽንፈኞች አይደሉም፡፡ ስለዚህ የኦሮሞ ህዝብ ጠብቁን ብለው ቢጮሁ እነ ሺመልስ አብዲሳ፣ የሚሰማቸው ማንም የለም፡፡

አብይ አህመድ ወጥቶ ያወራል፡፡ ሺመልስ አብዲሳ ወጥቶ ይደነፋል፡፡ እነዚህ ሰዎች የስልጣን እድምያቸው ማለቂያ ላይ ነው፡፡ ኃይላቸው እየተሸመደመደ፣ ጦራቸው እየተሸነፈና እየተፍረከረከ ነው፡፡ ያላቸውን ሁሉ አሰማሩ፡፡ አልቻሉም፡፡ ፋኖን በሶስት ሳምንት እንደመስሳለን አሉ፡፡ እነርሱ ራሳቸው እየተደመሰሱ ነው፡፡ ፋኖ ክብዙ አደረጀጀቶች፣ ወደ ሻለቃዎች፣ ከሻለቃዎች ወደ ብርጌዶች፣ ከብርጌዶች ወደ ክፍለ ሮችር፣ ከክፍ፤እ ጦሮችን ወደ እዞች እየተሸጋገረ ነው፡፡ ከኢመደበኛ አደረጃጀት ወደ መደበኛ አደረጃጀት እየመጣ ነው፡፡ መከላከያ የሚባለው ቢፈርስ፣ ፋኖ የአገር መከላከያ ሆኖ የመቀጠል አቅም እንዲኖረው እየሰራ ነው፡፡

ከዚህ ቀደም ሽመልስ አብዲሳ  ፖለቲካ ቁማር እንደሆነ በግልፅ ተነግሮናል:: ካሁን ቀደም ከኦሮሞ አንፃር ቁማሩ ሁለት ጉዳዮችን ያካትታል:: አንደኛዉ ውስጣዊ አንድነቱን መናድ ላይ አተኩሯል::  በኦሮሞ ህዝብ መካከል የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ (ባሌ፣ ወለጋ፣ አርሲ፣ ቦረና፣ ወሎ፣ ሸዋ፣ ሀረርጌ፣ ጅማ ወዘተ) በሀይማኖትና በጎሳ (ክርስቲያኖች፣ ሙስሊሞች፣ ዋቄፋና ወዘተ) እና በሶሺዮ ኢኮኖሚ ተግባራቶቻቸው ላይ ሳይቀር መከፋፈል መፍጠር ወይም ማበረታታት ተከፋፍሎ እንዲያንስ ታስቦ ነጣጥሎ ለምግዛት ይሰራ ነበር አሁን የጭንቅ ቀን  “ኦሮሞ ተንሰ::”የኦሮሞ ሕዝብና መንግሥት የመጀመሪያውም ኾነ የመጨረሻው ተልዕኮው ይህን መንግሥታዊ ሥርዓት መጠበቅ ነው”

የቅርብ ጊዜውን ብልጽግና ስልጣን ከያዘበት ጊዜ አንስቶ በመስኪድ ፈረሳ ምክንያት የቱለማ ኦሮሞን ከሙስሊም ወንድሞቹ ጋር ለማጋጨት የተሰራዉ ተንኮል ይታወሳል:: በመዋቅር ስም በደቡብ ኦሮሚያ የተፈጠረዉ ውዥንብርም ወንድማማቾችን ነጣጥሎ ለማዳካም ከተሸረበዉ ሴራ ይመነጫል:: እንዲህ ዓይነት ተንኮል በዞን... በወረዳ... በቀበሌና በጎጥ ደረጃም ተተግብሯል:: ለማንኛዉም ሴራዉ በተደጋጋሚ ተሞክሮ እንደከሸፈ ቁማርተኛዉም ያዉቃል! ደስ የሚልው ህዝቡ ከሴረኛዉ ቀድሟል!

ኦሮሞን በወንድሞቹ ዘንድ ለማስጠላት የተወጠነዉ ሌላኛው ቁማር አሁን በመጨረሻ ሰኣት የጭንቀት ሰኣት የመዘዟት:: በአንድ በኩል ከሌሎች ኢትዮጲያዊ ወገኖቹ ጋር በመከራ እሳት እየተቃጠለ ያለዉን ንፁህ ህዝብ የተለየ ተጠቃሚ ለማስመሰል የሀሰት ሪፖርት ይቀርባል:: የፎቶና የቪድዮ ድራማ ይሰራል:: በሌላ በኩል ደግሞ ልክ በዘር ፖለቲካ ካጠመቃቸው አባታቸው ወያኔ የውድቀት ፖለቲካ መማር ያልቻሉ ድንዙዛን ያንኑ መልሰው አሳፋሪ ተግባራት ተፈፅሞ በኦሮሞነት ካባ ይፎከራል ያደንቁሩናል::

ሀይማኖትና ብሔር በአደባባይ ይዘለፋል:: ያለሀፍረት "ፖለቲካ በማታለል የታጀበ ቁማር ነዉ" ይባላል:: ቁማሩን የሚጫወቱትም ለኦሮሞ ተብሎ እንደሆነ ይመሰላል:: ጫወታዉን ለማሳመር በቁማርተኛዉ ስብዕና ፈፅሞ የሌለዉ ኦሮሙማ በየመድረኩ ይደጋገማል::

በዘመድ አዝማድ ተደራጅቶ ሀገር ይጋጥና በተጎጂዉ ህዝብ ስም ለመሸፈን ይሞከራል:: በህዝቡ ዘላቂ ኪሳራ ሴረኛና ዘራፊ ጊዜያዊ ርካሽ ጥቅሙን ያካብታል:: ህዝቡ ግን በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን በረሃብ ሲሞት ሁሉም አይቷል:: የሌሎችን እርዳታ እንኳን እንዳያገኝ ለገፅታ ጥራት ተብሎ መከራዉ ይደበቃል:: በአጋጣሚ የህዝቡ መከራ ከተሰማ መልሶ ለመሸፈን ዶክመንተሪ ይሰራል:: አሁን በኦሮሚያ ስለህዝቡ ሞትና መፈናቀል መረጃ ማግኘት ከሰማይ ይርቃል! የክልሉ ህዝብ በኢህእዴግ ዘመን የነበረዉን ነፃነትን እንኳን አጥቷል:: በሌቦች ዉሳኔ ምርቱን ከገበያ ዋጋ በታች ለቁመርተኛዉ ደላሎች ለመሸጥ ይገደዳል:: ማህበራዊ ግልጋሎት ከናካቴዉ ተረስቷል::  በተለያዬ ቦታ ሰዉ በዘፈቀደ ይገደላል::

አብይ አህመድ ሰልጣን እንደያዜ ስለማዐከላዊው የስቃይ ምርመራ ሲደስኩር አሁን እንደ  እንጉዳይ በየቦታው በየባለስልታኖች ቤት ሳይቀር ለመስማት እንኳን የሚቀፍ ግፍ ፣ለህዝብ የቆሙ ንፁሃንን ከልጆቻቸው ነጥሎ፣ በቶርቼር (torure) ገላቸውን መበጣጥስ፣  ሰቃዩና ጥፍር ነቀላውን በማሳለጥ እንደትላንቱ ዜጎችን በምርመራ ስም ማኮላሸት ከአባትችሁ ወያኔ በከፋ መልኩ ቀጥላጭችሁበታል! በናንተ ሌብነት ምክንያት በታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥላችሁ ዉሃ ሲጠይቁት ወተት የሚሰጥ የዋው ህዝብ ገፊና አፈናቃይ እንዲመስል ተደርጏል:: ከነባራዊዉ ትርክት አንፃር ይህ እዉነት ለማመን ሊቸግርም ይችላል:: ግና መራራ ሀቁን መግለፅ አሁን ግድ ይላል:: የቁማርተኛ ሌባ ወንጀል ፈፅሞ ኦሮሞን አይመለከትም:: በመሰረቱ ሌባ ሆድ እንጂ ብሔር .. ሀይማኖት ወይም ሰፈር የለዉም:: እዉነቱን ለምናገር ግን የኦሮሞ ህዝብ የአማራና የሌሎች ኢትዮጵያዊያን የወንድሞቹ ደስታና ሀዘን ተጋሪ እንጂ ለቁማርተኛ ሌቦች ወንጀል አባሪ አይደለም::  ቁማርተኛ ሌቦች በህዝብ ኪሳራ ለመጠቀም ኦሮሞን ልዩ ተጠቃሚ ለማስመሰል ብዙ ደክሟል:: በተጨባጭ ግን ምስኪኑ የኦሮሞ ህዝብ የቁማሩ ልዩ ሰለባ ሆኖ ይገኛል:: ከሁሉም ለከፋ መካራ መጋለጡ አንሶት በወንድሞቹ ዘንድ ባልተገባ መንገድ ይታያል:: እዛው  እራሳች ሁን ቻሉ የጨነቀለት አለ ስፋኙ እውነት ነው የጨነቀለት ስት ሰርቅ ስትገድለው ስታኮላሸው ኑሮን ምድራዊ ሲኦል ስታደርግበት ት ዝ ያላለህ ህዝብ አሁን የጨነቀለት ፈልከው ብዙ አይደንቅም የዘረኞች የዘራፊዎች የጨቋኞች በመውደቂያቸው ዋዜማ የሚያሰሙት ጣር ስለሁነ የኦሮሞ ህዝብም እዛው እራሳችሁን ቻሉ በሎ በስብሰባችሁ ላይ ነግሮዋችዋል! ….ይሰማል በኦሮሞ እልፍኝ የተደበቃችሁ ሳጥናኤል አብይ እና ጥቂት እፉኞች እዛው እራሳችሁን ቻሉ!! ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ ከህዝብ ጋር ችግር የለብትም ኖሮበትም አያውቅም!!

*****የጨነቀለት አለ ዘፋኙ ገና ብዙ እናያለን*****
https://amharic.zehabesha.com/archives/188922
የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አባቶች ግድያ
https://youtu.be/hoKunbPmTmw?si=QC-Ie2PclXa4aVdw

 የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አባቶች ግድያ
https://amharic.zehabesha.com/archives/188936
በኦሮሞ እልፍኝ የተደበቁ ሳጥናኤል አብይ እና ጥቂት እፉኞች ፥ የጨነቀለት መከራዉን ሲያሳዩት የነበረውን ኦሮሞ አድነን እያሉ ነው
ካሌብ ታደሰ

የካቲት 10, 2016

በኦሮሞ እልፍኝ የተደበቁ ሳጥናኤል አብይ እና ጥቂት እፉኞች ፥ የጨነቀለት መከራዉን ሲያሳዩት የነበረውን ኦሮሞ አድነን እያሉ ነው:: ሲጀምር ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ ከህዝብ ጋር ችግር የለብትም ኖሮበትም አያውቅም!!

በአዳማ (ናዝሬት) ጨፌ በተባለው ምክር መሰብሰቢያ አዳራሽ በቅርቡ በነበረው ስብስባ ላይ ሺመልስ አብዲሳ፣ አሁን ያለውን ዘረኛ ስርዓት፣ የኦሮሞ ህዝብ እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል፡፡ "ኦሮሞ የሆነ ሁሉ ፋኖን መዋጋት አለበት፣ ፋኖ ኦሮሞን ሊያጠፋ ነው " በሚል፡፡

 

ይህን ያለው ፣ በአዳማ (ናዝሬት) ጨፌ በተባለው ምክር መሰብሰቢያ አዳራሽ ነው፡፡ በአዳማ (ናዝሬት)  ከ75% በላይ ነዋሪ ኦሮምኛ የማይናገር ነው፡፡ ግን በአዳማ ጨፌው ሲሰበሰብ ሙሉ በሙሉ በኦሮምኛ ብቻ ስለሆነ፣ አብዛኛው የናዝሬት ነዋሪ አይከታተለውም፡፡ እርግጠኛ ነኝ ከጨፌ አባላት ውስጥም የአዳማ (ናዝሬት) ልጆች የሉበትም፡፡ በአዳማ (ናዝሬት) የተወለዱና ያደጉ፡፡ ይህም ምን ያህል የኦሮሞ ክልል የሚባለው ዘረኛና አፓርታይዳዊ መሆኑን አመላካች ነው፡፡

ኦሮሞ ባለፉት 30 አመታት፣ በተለይም ደግሞ ላለፉት 6 አመታት ምን ተጠቅሞ ነው:: በእነዚህ ጥቂት አመታት ውስጥ ከብልጽግና ይልቅ ከፍተኛ ውድመትና ጥፋት ደርሷል ስለሆነም አሁን ያለውን ስርዓት ለማስጠበቅ የሚነሳው ? አዎን በአዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ በኦሮሞ ስም የዘረፉ፣ የተጠቀሙ የተወሰኑ ከኦሮሞ ማህበረሰብ የሆኑ ሰዎች አሉ፡፡ ግን ከ98 በመቶ የሚሆነው ኦሮሞ፣ ምን ያገኘው ነገር አለ ?

የኦሮሞ ስቃይ በአብይ አህመድ እና በሺመልስ አብዲሳ፣  የስልጣን ዘመን ኦሮሞ፣ ምን ያገኘው ነገር አለ ? ዛሬ አርብ  የካቲት 15, 2016 ለንባብ የበቃው የሮይተርስ ዘገባ ባደረገው ምርመራ “በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ያቀፈ ሚስጥራዊ ወይንም የህቡዕ አደረጃጀት አለው የተባለው ኮሚቴው ስያሜው “ኮሬ ነጌኛ” ወይንም የጸጥታ ኮሚቴ መሆኑን እና አብይ አህመድ ጠ/ሚኒስትር ሁነው በተሾሙ ወራት ውስጥ የተቋቋመ መሆኑን የዜና አውታሩ በሪፖርቱ ጠቁሟል። የተቋቋመበትም ዋነኛ አላማ በክልሉ ከሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ሀይል ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር በተገናኘ በኦሮምያ ክልል የተነሳውን ተቃውሞ  ለመቆጣጠር መሆኑን አመላክቷል። ይህ የህቡዕ አደረጃጀት ከህግ አግባብ ውጭ ግድያ እና ህገ ወጥ እስራት ትእዛዝ ያስተላልፋል ተፋጻሚነቱን ይከታተላል” ሲል ተናግሯል። ይህ ሚስጥራዊው አካል “ኮሬ ናጌንያ” “Koree Nageenyaa” የሚል መጠሪያ ያለው ሲሆን አብይ አህመድ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣን ከያዙ ከጥቂት ወራት በኋላ ወደ ስራ መገባቱን አመልክቷል።

የዜና አውታሩ አክሎም " ኮሬ ናጌንያ በአቢይ ብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቢሮዎች ውስጥ የሚገናኙ ሲሆን ኮሚቴው የሚመራው በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ መሆኑንም አክለውም የኮሚቴ አባላት በሙሉ ኦሮሞ ናቸው።  በአባልነት የክልሉ ከፍተኛ የጸጥታ እና የፖለቲካ ባለሥልጣናት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል. ከነሱም ወስጥ የኦሮሚያ የብልጽግና ፓርቲ መሪ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ተሰማ በኮሚቴው ውስጥ ተቀምጠዋል፣ የኦሮሚያ የጸጥታ ኃላፊ የሆኑት አራርሳ መርዳሳ እና ሌሎች ግማሽ ደርዘን የሚሆኑ ሌሎች የሀገር ውስጥ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሃላፊዎች በኮሚቴው ውስጥ ተቀምጠዋል ብለዋል ምንጮች።  ይህ ሚስጥራዊው አካል “ኮሬ ናጌንያ” committee is little known beyond a tight official circle” ጥብቅ ከሆነው ኦፊሴላዊ ክበብ በዘለለ ብዙም አይታወቅም።

“ According to a Reuters report “the Koree Nageenyaa – Security Committee in the Oromo language - which began operating in the months after Prime Minister Abiy Ahmed came to power in 2018. The committee’s existence has not been previously reported.” ሮይተርስ የምርመራ ሪፖርቱን ለማጠናከር  “ከ30 በላይ የፌደራል እና የአካባቢ ባለስልጣናትን፣ ዳኞችን፣ ጠበቆችን እና በባለስልጣናት በደል ሰለባዎችን ቃለ መጠይቅ አድርጓል” ብሏል። በተጨማሪም በክልሉ የሚገኘውን “የኮሬ ናጌንያ” ስራዎችን ያውቃሉ የተባሉ ግለሰቦችን አነጋግሯል - አንዳንዶቹ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀዋል። ሚስጥራዊው አካል በክልሉ ውስጥ ግድያዎች እና እስራት ጋር የተያያዘ ነው:: ሮይተርስ በተጨማሪም የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩትን ሚልኬሳ ​​ገመቹን ጠቅሶ ስለ ኮሬ ናጌንያ ከመጋቢት 2019 ጀምሮ እንደሚያውቅ ዘግቧል።

የዚህ ቡድን ተግባር የሚፈልጋቸው ሰዎች እያሳደደ መግደል እና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጪ  ማሰር መሆኑም ተጠቁሟል. “The people familiar with Koree Nageenyaa's activities attributed dozens of killings to the committee's orders and hundreds of arrests. Among the killings, they said, was a massacre of 14 shepherds in Oromiya in 2021 that the government has previously blamed on OLA fighters.”

በኮሚቴው በተላለፈ ትእዛዝ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች፣ “የጸጥታ ስጋቶች” ናቸው በሚል የተፈጸሙ ጅምላ እስሮች በዜና አውታሩ ሪፖርት ተካተዋል። በ2014 ዓ.ም በከረዩ አባገዳዎች አባላት ግድያ ላይ በሰበሰባቸው እና ባገናዘባቸው ማስረጃዎች መሰረት 14 የከረዩ የሚችሌ ገዳ አባላት በመንግሥት የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በግዳጅ ወደ ጫካ ቦታ ተወስደውና የአካባቢ አስተዳደር ሰዎች ባሉበት ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በጥይት ተመተው የተገድለዋል ብሏል።  እስቲ ጉጂ ያላችሁ ተናገሩ ? ወለጋ ያላችሁ ኦሮሞዎች ተናገሩ፣ ሰሜን ሸዋ ያላችሁ ተናገሩ ? እኔ ባለኝ መረጃ ፣  ኦሮሞ ነን የሚሉ ኦነጋዊ ገዢዎች ስልጣን እንደያዙበት ዘመን፣ ኦሮሞ በታሪኩ ተሰቃይቶ አያውቅም፡፡ በ 2014 th 2015 አመተ ምህረት በምስራቅ ወለጋ የተለያዩ ወረዳዎች በኦሮሚያ ልዩ ኃይል እና በመከላከያ የተገደሉ የአማራ ተወላጆች በመቶዎች የሚቆጠሩ ናቸው:: በእስር ላይ የሚገኙትም ተገርፈዋል፣ እንዲሰቃዩ ተደርገዋል ያለው ሮይተርስ ጣልቃ ለመግባት እና ለመገዳደር የሞከሩ ዳኞች እና ጠበቆች ማስፈራራት ደርሶባቸዋል ሲል ገልጿል።

ብዙ ኦሮሞዎች አሁን የፋኖን ዓላማ እየተረዱ የመጡ ይመስላል፡፡ በሺሆች የሚቆጠሩ እነ ብርሃኑ ጁላ የላኳቸው የኦሮሞ ተዋጊዎች አልቀዋል፡፡ ሞተዋል፡፡ ቁስለኞች ሆነዋል፡፡ ይህ በኦሮሞ እናቶችና አባቶች ዘንድ ፣"ለምንድን ነው ልጆቻችን የሞቱት ?" የሚል ጥያቄዎች እየተነሱ፡፡ ይህ አሁን ያለው አገዛዝ ልጆቻችን አታሎ፣ አፍሶ አስፈጃቸው እያሉ ነው፡፡ በሺሆች የሚቆጠሩም ተማርከው በሰላም ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመልሰዋል፡፡ ለህዝቡ እየተናገሩ ነው፡፡ ያዩትን፣ የሆነውን ሁሉ፡፡ አገዛዙ የርሱ ጭፍሮችን፣ ይዞ ንጹሃንን በማንነታቸው ፣ አማራ ስለሆኑ ብቻ ሲጨፈጭፍ፣ ፋኖዎች ተመሳሳይ የበቀል እርምጃዎች በመውሰድ ፣ ኦሮሞን በኦሮሞነቱ አላጠቁም፡፡ ይሄንን ደግሞ በአማራ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ያሉ ኦሮሞዎች ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ፋኖዎች ሺመልስ አብዲሳ እንዳለው ቢሆኑ ኖሮ፣ በፍቼ፣ በወለንጭቲ፣ በገብረ ጉራቻ፣ በመኪጡሪ፣ በኢጄሬ ሰሜን ሸዋና በኢጀሬ ምስራቅ ሸዋ፣ በሞጆ፣ በከሚሴ፣ በሸኖ፣ በመንዲዳ፣ በመተሃራ ወዘተ ባሉ አካባቢዎች እልቂት ይፈጠር ነበር፡፡ ፋኖ ሃላፊነት ሚሰማው፣ በዘር ጥላቻ ላይ ያልተመሰረተ እንደሆነ ብዙ ኦሮሞዎች እያወቁ ነው፡፡

ፋኖ ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ማንም ኢትዮጵያዊ ባህሉን፣ ቋንቋዎች፣ ቅርሱን ጠብቆ፣ በቋንቋዉ መንግስታዊ አገልግሎት እያገኘ፣ በወደደው ቦታ መኖር የሚችልንበት ስርዓት እንዲኖር ነው የሚታግለው፡፡  ሺመልስ አብዲሳ፣ አዳነች አበቤ፣ አብይ አህመድ መቀመጫቸው አዲስ አበባ ነው፡፡ የኦሮሞ ክልል ጨፌ ደግሞ ናዝሬት ነው፡፡ ፋኖዎች የብልጽግና ዘረኛውን አገዛዝ ለመገርሰስ፣ ወታደራዊ ዘመቻዎች ባሌ ዲንሾ፣ ወይንም ምእራብ ወለጋ ጉሊሶ ወይም አርሲ ኮፈሌ አይደለም የሚንቀሳቀሱት፡፡ ከ90% በላይ ኦሮሞ ባለበት አካባቢ፡፡ ሺመልስ አብዲሳ፣ አዳነች አበቤ፣ አብይ አህመድ መቀመጫቸው አዲስ አበባ ነው፡፡ አዲስ አበባንና አዲስ አበባን አካባቢ፣ እነ ናዝሬትን ከተቆጣጠሩ፣ የኦሮሞ ብልጽግና አገዛዝ ሙሉ ለሙሉ ያከትምለታል፡፡ በነዚህ አካባቢዎች ደግሞ ፣ በአዲስ አበባ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ፣ በናዝሬት፣ በደብረ ዘይት፣ በአጠቃላይ በምስራቅ ሸዋ ዞን የሚኖረው ማህበረሰብ አብዛኛው ኦሮሞ ያልሆነ፣ ፋኖን የሚደገፍ ነው፡፡ ያሉት ኦሮሞዎች ቢሆኑ፣ ሚኒሊካዊ ኦሮሞዎች እንጂ ጽንፈኞች አይደሉም፡፡ ስለዚህ የኦሮሞ ህዝብ ጠብቁን ብለው ቢጮሁ እነ ሺመልስ አብዲሳ፣ የሚሰማቸው ማንም የለም፡፡

አብይ አህመድ ወጥቶ ያወራል፡፡ ሺመልስ አብዲሳ ወጥቶ ይደነፋል፡፡ እነዚህ ሰዎች የስልጣን እድምያቸው ማለቂያ ላይ ነው፡፡ ኃይላቸው እየተሸመደመደ፣ ጦራቸው እየተሸነፈና እየተፍረከረከ ነው፡፡ ያላቸውን ሁሉ አሰማሩ፡፡ አልቻሉም፡፡ ፋኖን በሶስት ሳምንት እንደመስሳለን አሉ፡፡ እነርሱ ራሳቸው እየተደመሰሱ ነው፡፡ ፋኖ ክብዙ አደረጀጀቶች፣ ወደ ሻለቃዎች፣ ከሻለቃዎች ወደ ብርጌዶች፣ ከብርጌዶች ወደ ክፍለ ሮችር፣ ከክፍ፤እ ጦሮችን ወደ እዞች እየተሸጋገረ ነው፡፡ ከኢመደበኛ አደረጃጀት ወደ መደበኛ አደረጃጀት እየመጣ ነው፡፡ መከላከያ የሚባለው ቢፈርስ፣ ፋኖ የአገር መከላከያ ሆኖ የመቀጠል አቅም እንዲኖረው እየሰራ ነው፡፡

ከዚህ ቀደም ሽመልስ አብዲሳ  ፖለቲካ ቁማር እንደሆነ በግልፅ ተነግሮናል:: ካሁን ቀደም ከኦሮሞ አንፃር ቁማሩ ሁለት ጉዳዮችን ያካትታል:: አንደኛዉ ውስጣዊ አንድነቱን መናድ ላይ አተኩሯል::  በኦሮሞ ህዝብ መካከል የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ (ባሌ፣ ወለጋ፣ አርሲ፣ ቦረና፣ ወሎ፣ ሸዋ፣ ሀረርጌ፣ ጅማ ወዘተ) በሀይማኖትና በጎሳ (ክርስቲያኖች፣ ሙስሊሞች፣ ዋቄፋና ወዘተ) እና በሶሺዮ ኢኮኖሚ ተግባራቶቻቸው ላይ ሳይቀር መከፋፈል መፍጠር ወይም ማበረታታት ተከፋፍሎ እንዲያንስ ታስቦ ነጣጥሎ ለምግዛት ይሰራ ነበር አሁን የጭንቅ ቀን  “ኦሮሞ ተንሰ::”የኦሮሞ ሕዝብና መንግሥት የመጀመሪያውም ኾነ የመጨረሻው ተልዕኮው ይህን መንግሥታዊ ሥርዓት መጠበቅ ነው”

የቅርብ ጊዜውን ብልጽግና ስልጣን ከያዘበት ጊዜ አንስቶ በመስኪድ ፈረሳ ምክንያት የቱለማ ኦሮሞን ከሙስሊም ወንድሞቹ ጋር ለማጋጨት የተሰራዉ ተንኮል ይታወሳል:: በመዋቅር ስም በደቡብ ኦሮሚያ የተፈጠረዉ ውዥንብርም ወንድማማቾችን ነጣጥሎ ለማዳካም ከተሸረበዉ ሴራ ይመነጫል:: እንዲህ ዓይነት ተንኮል በዞን... በወረዳ... በቀበሌና በጎጥ ደረጃም ተተግብሯል:: ለማንኛዉም ሴራዉ በተደጋጋሚ ተሞክሮ እንደከሸፈ ቁማርተኛዉም ያዉቃል! ደስ የሚልው ህዝቡ ከሴረኛዉ ቀድሟል!

ኦሮሞን በወንድሞቹ ዘንድ ለማስጠላት የተወጠነዉ ሌላኛው ቁማር አሁን በመጨረሻ ሰኣት የጭንቀት ሰኣት የመዘዟት:: በአንድ በኩል ከሌሎች ኢትዮጲያዊ ወገኖቹ ጋር በመከራ እሳት እየተቃጠለ ያለዉን ንፁህ ህዝብ የተለየ ተጠቃሚ ለማስመሰል የሀሰት ሪፖርት ይቀርባል:: የፎቶና የቪድዮ ድራማ ይሰራል:: በሌላ በኩል ደግሞ ልክ በዘር ፖለቲካ ካጠመቃቸው አባታቸው ወያኔ የውድቀት ፖለቲካ መማር ያልቻሉ ድንዙዛን ያንኑ መልሰው አሳፋሪ ተግባራት ተፈፅሞ በኦሮሞነት ካባ ይፎከራል ያደንቁሩናል::

ሀይማኖትና ብሔር በአደባባይ ይዘለፋል:: ያለሀፍረት "ፖለቲካ በማታለል የታጀበ ቁማር ነዉ" ይባላል:: ቁማሩን የሚጫወቱትም ለኦሮሞ ተብሎ እንደሆነ ይመሰላል:: ጫወታዉን ለማሳመር በቁማርተኛዉ ስብዕና ፈፅሞ የሌለዉ ኦሮሙማ በየመድረኩ ይደጋገማል::

በዘመድ አዝማድ ተደራጅቶ ሀገር ይጋጥና በተጎጂዉ ህዝብ ስም ለመሸፈን ይሞከራል:: በህዝቡ ዘላቂ ኪሳራ ሴረኛና ዘራፊ ጊዜያዊ ርካሽ ጥቅሙን ያካብታል:: ህዝቡ ግን በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን በረሃብ ሲሞት ሁሉም አይቷል:: የሌሎችን እርዳታ እንኳን እንዳያገኝ ለገፅታ ጥራት ተብሎ መከራዉ ይደበቃል:: በአጋጣሚ የህዝቡ መከራ ከተሰማ መልሶ ለመሸፈን ዶክመንተሪ ይሰራል:: አሁን በኦሮሚያ ስለህዝቡ ሞትና መፈናቀል መረጃ ማግኘት ከሰማይ ይርቃል! የክልሉ ህዝብ በኢህእዴግ ዘመን የነበረዉን ነፃነትን እንኳን አጥቷል:: በሌቦች ዉሳኔ ምርቱን ከገበያ ዋጋ በታች ለቁመርተኛዉ ደላሎች ለመሸጥ ይገደዳል:: ማህበራዊ ግልጋሎት ከናካቴዉ ተረስቷል::  በተለያዬ ቦታ ሰዉ በዘፈቀደ ይገደላል::

አብይ አህመድ ሰልጣን እንደያዜ ስለማዐከላዊው የስቃይ ምርመራ ሲደስኩር አሁን እንደ  እንጉዳይ በየቦታው በየባለስልታኖች ቤት ሳይቀር ለመስማት እንኳን የሚቀፍ ግፍ ፣ለህዝብ የቆሙ ንፁሃንን ከልጆቻቸው ነጥሎ፣ በቶርቼር (torure) ገላቸውን መበጣጥስ፣  ሰቃዩና ጥፍር ነቀላውን በማሳለጥ እንደትላንቱ ዜጎችን በምርመራ ስም ማኮላሸት ከአባትችሁ ወያኔ በከፋ መልኩ ቀጥላጭችሁበታል! በናንተ ሌብነት ምክንያት በታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥላችሁ ዉሃ ሲጠይቁት ወተት የሚሰጥ የዋው ህዝብ ገፊና አፈናቃይ እንዲመስል ተደርጏል:: ከነባራዊዉ ትርክት አንፃር ይህ እዉነት ለማመን ሊቸግርም ይችላል:: ግና መራራ ሀቁን መግለፅ አሁን ግድ ይላል:: የቁማርተኛ ሌባ ወንጀል ፈፅሞ ኦሮሞን አይመለከትም:: በመሰረቱ ሌባ ሆድ እንጂ ብሔር .. ሀይማኖት ወይም ሰፈር የለዉም:: እዉነቱን ለምናገር ግን የኦሮሞ ህዝብ የአማራና የሌሎች ኢትዮጵያዊያን የወንድሞቹ ደስታና ሀዘን ተጋሪ እንጂ ለቁማርተኛ ሌቦች ወንጀል አባሪ አይደለም::  ቁማርተኛ ሌቦች በህዝብ ኪሳራ ለመጠቀም ኦሮሞን ልዩ ተጠቃሚ ለማስመሰል ብዙ ደክሟል:: በተጨባጭ ግን ምስኪኑ የኦሮሞ ህዝብ የቁማሩ ልዩ ሰለባ ሆኖ ይገኛል:: ከሁሉም ለከፋ መካራ መጋለጡ አንሶት በወንድሞቹ ዘንድ ባልተገባ መንገድ ይታያል:: እዛው  እራሳች ሁን ቻሉ የጨነቀለት አለ ስፋኙ እውነት ነው የጨነቀለት ስት ሰርቅ ስትገድለው ስታኮላሸው ኑሮን ምድራዊ ሲኦል ስታደርግበት ት ዝ ያላለህ ህዝብ አሁን የጨነቀለት ፈልከው ብዙ አይደንቅም የዘረኞች የዘራፊዎች የጨቋኞች በመውደቂያቸው ዋዜማ የሚያሰሙት ጣር ስለሁነ የኦሮሞ ህዝብም እዛው እራሳችሁን ቻሉ በሎ በስብሰባችሁ ላይ ነግሮዋችዋል! ….ይሰማል በኦሮሞ እልፍኝ የተደበቃችሁ ሳጥናኤል አብይ እና ጥቂት እፉኞች እዛው እራሳችሁን ቻሉ!! ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ ከህዝብ ጋር ችግር የለብትም ኖሮበትም አያውቅም!!

*****የጨነቀለት አለ ዘፋኙ ገና ብዙ እናያለን*****
https://amharic.zehabesha.com/archives/188922

Friday, February 23, 2024

የሉባ ገዳ፡  የጨፍጫፊወች ዕድር
‹‹አራተኛው ሉባ ቢፎሌ ይባላል፡፡  ደዋሮን ሙሉ በሙሉ አጥፍቶ ፈጠጋርን መውጋት የጀመረው እሱ ነው፡፡  ምርኮኞችን እያጋዘ አገልጋዮች በማድረግ ገርባ አላቸው፡፡››

አባ ባሕርይ፣ ዜናሁ ለጋላ፣ ክፍል 8

መንደርደርያ

የሉባ ገዳ ማለት ማነነታቸውን በውሸት ትርክት ላይ ሙሉ በሙሉ የመሠረቱ የኦሮሞ ፅንፈኞች እንደሚሉት አቃፊ፣ ደጋፊ ሳይሆን ዘራፊ፣ ጨፍጫፊ መሆኑን ከነዚህ ፅንፈኞች ውስጥ ሀቁ እየተገለጠላቸው የመጣው ጥቂቶቹ (እነ ዮናስ ብሩ) በግልፅ መመስከር ጀምረዋል።  መመስከር የጀመሩት እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሎ መላዋን ጦቢያን ለማንቦግቦግ እያስገመገመ ያለው ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል ዓይናቸው ሸፍኖት የነበረውን የኦሮሙማን ሞራ በትንሹም ቢሆን ስለገፈፈላቸው ነው።  በዚህ ጦማር ላይ ደግሞ የሉባ ገዳ ማለት ሌላ ምንም ማለት ሳይሆን የሉባ ጨፍጨፊ ሠራዊት ጭፍጨፋውን ለማሳለጥ የግድ ስለሚያስፈልገው ብቻ የመሠረተው የጨፍጫፊወች ዕድር መሆኑን እንመለከታልለን።

 

የጨፍጫፊወች ዕድር

ሌቦች ሲካፍሉ እንጅ ሲሰርቁ አይጣሉም፣ እንደውም በጣም ይዋደዳሉ፣ ካልተዋደዱ ስርቆታቸው አይሳካምና።  ጨፍጫፊወች ደግሞ ድርጊታቸው ከሌቦች እጅግ የከበደ ስለሆነ፣ ጭፍጭፋቸውን ሲያከናውኑ ከሌቦች እጅግ የበለጠ መዋደድ ወዴታቸው ሳይሆን ግዴታቸው ነው።  ዓይናቸውን የሚጥሉት በጭፍጨፋው ቱርፋቶች ላይ እንጅ በጭፍጨፋው ላይ ስላልሆነ፣ ጭፍጨፋውን ለማሳካት ማድረግ /የሚገባቸውን/ ሁሉ በሙሉ ስምምነት፣ ቅንብርና ትብብር ያደርጋሉ፡፡  የጭፍጨፋውን አመራሮች የሚመርጡት ደግሞ የጭፍጨፋውን ቱርፋቶች በተቻላቸው መጠን አመርቂ ለማድረግ በተቻላቸው መጠን ሌት ተቀን ይተጋሉ ብለው ሙሉ በሙሉ የሚያምኑባቸውን ግለሰቦች ብቻና ብቻ ስለሆን፣ አመራረጡ ሙሉ በሙሉ ዲሞክራሲያዊ ነው፡፡  ማናቸውም የጭፍጨፋው አመራር ደግሞ የጭፍጨፋ ሚናውን በሚገባ ካልተወጣ /የሚጎዳው/ እሱ ራሱ በመሆኑ፣ ቦታውን ከሱ ለተሻለ ግለሰብ ለመልቀቅ ሙሉ ደስተኛ ነው፡፡  ማናቸውም የጭፍጨፋው ዐባል ደግሞ ጭፍጨፋውን አመርቂ ለማድረግ ይበጃሉ የሚላቸውን ሐሳቦች የመግለጽ ሙሉ ነጻነት እንዲኖረው ብቻ ሳይሆን፣ እንዲገልጽም በእጅጉ ስለሚበረታታ የጭፍጨፋው አባሎች ነጻነት ገደብ የለውም።

ሌቦች ስርቆታቸውን ከጨረሱ በኋላ በስርቆቱ ክፍፍል እንደሚጣሉ፣ ጭፍጨፊወችም ጭፍጨፋቸውን ከጨረሱ በኋላ በጭፍጨፋው ቱርፋቶች ክፍፍል ይጣላሉ።  በጭፍጨፋው ወቅት የነበረው ከፍትኛ ፍቅር ወደ ከፍትኛ መናቆር ይለወጣል፡፡  በጭፍጨፋው ወቅት የነበረው በሙሉ ስምምነት ላይ የተመሰረት ቅንብርና ትብብርም፣ ተግባሩን ስለፈፀም ጭፍጨፋው እንደቆመ ወዲያውኑ ይከስማል።

ጭፍጭፋን ላማሳለጥ የግድ ስለሚያስፈልግ ብቻ በጊዜያዊነት የሚያገለግል፣ ጭፍጨፋው ሲቆም የሚከስም፣ ለጨፍጫፊወች ሙሉ ነፃነት የሚሰጥና፣ የጨፍጭፋው አመራሮቸ በሙሉ ነፃነት የሚመረጡበት የጨፍጫፊወች ቅንብርና ትብብር የጨፍጫፊወች ዕድር ይባላል፡፡  የኦሮሞ ጽንፈኞች ገዳ ዲሞክራሲ ነው የሚሉት ለኦሮሞ ጨፍጫፊወች ሙሉ ነፃነት የሚሰጥና የጨፍጭፋው አመራሮቸ በሙሉ ነፃነት የሚመረጡበት የኦሮሞ ጨፍጫፊወች ዕድር ስለነበረ ነበር።

 

የሉባ ገዳ

ኦሮሞ ከመነሻው ፈልሶ፣ በጦቢያ ላይ ተስፋፍቶ፣ ግብርና ተምሮ በቋሚነት ከመስፈሩ በፊት አርብቶ አደር የነበረ በመሆኑ፣ ካኗኗሩ ምንነት የመነጨ ነጻነት የሚመስል መረን ለቀቅነት ወይም ልልነት ነበረው፡፡  ዘላን የተባለበትም ምክኒያት ባሻው ጊዜ ወዳሻው ቦታ ስለሚዘል ነው፡፡  የከብት ጭራ የሚከተል አርብቶ አደር፣ በሬ እንደሚጠምድ አርሶ አደር ጥብቅ ሊሆን አይችልም፣ መሆንም የለበትም፡፡  አርብቶ አደራዊ ኑሮ የሚኖሩ ወይም ደግሞ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ይኖሩ የነበሩ ብሔረሰቦች አኗኗራቸው በተወሰነ ደረጃ ልቅ መሆኑን ለመረዳት ያፋሮችን፣ የኢሳወችን፣ የሱማሌወችን፣ የከረዩወችን፣ የቦረናወችን ልቅ አኗኗር ከደገኛው ጦቢያዊ ጥብቅ አኗኗር ጋር ማነጻጸር ይበቃል፡፡

ሙሐመድ ሐሰንን የመሳሰሉ የኦሮሞ ልሂቆች ግን የኦሮሞን ከዘላንነት የመነጨ መረን ለቀቅነት ከዲሞክራሲ ጋር ሥራየ ብለው ያምታቱታል፡፡  ይህን የሚያደርጉት ደግሞ የኦሮሞ ብሔረሰብ ከሌላው ጦቢያዊ በተለየ መልክ ዲሞክራቲክ ነበር በማለት በብዙ ረገዶች (በስነቃሎች፣ በጽሑፍነክ ትውፊቶች ወዘተ.) የሚሰማቸውን የዝቅተኝነት ስሜት፣ የባዶነት መንፈስ በውሸት ትርክት ለመወጣት ነው፡፡  በዚህ ረገድ ደግሞ ኦሮምኛ የማያውቀው አስመሮም ለገሰ በኦነጋዊ ባልደረቦቹ የተተረጎመለትን የገዳ ትርክት ተሳስቶ (ወይም ደግሞ ሆን ብሎ) ወደ ዲሞክራሲ ትርክት በመቀየር የጻፋቸው ጽሑፎች ያንበሳውን ሚና ተጫውተዋል፡፡

የሉባ የገዳ የሉባን መስፋፋትና መንሰራፋት ለማሳለጥ (make efficient) ብቻና ብቻ የተሰረተ የሉባ የጨፍጫፊወች ዕድር ነበር፡፡  በሌላ አባባል የገዳ ስርዓት በዲሞክራሲ የሚያምን ሕዝብ የሰረተው ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ሳይሆን፣ በጭፍጨፋ ለመስፋፋት የግድ ስለሚያስፈልግ ብቻ መስፋፋቱ እስከቀጠለ ድረስ እንዲያገለግል የተሰረተ የሉባ ተስፋፊወች ቅንብርና ትብብር ነበር፡፡  የገዳ ስርዓት የተሰረተው 1522 ዓ.ም ገደማ (ማለትም በ 1515 የተጀመረውን የግራኝ ወረራ ተከትሎ) እንደነበር ራሱ ሙሐመድ ሐሰን ‹‹ኦሮሞና የጦቢያ ክርስቲያናዊ ንጉሥጌ›› (Oromo and the Christian Kingdom of Ethiopia) በተሰኘው በራሱ መጽሐፍ ላይ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡  እዚህ ላይ ደግሞ ትክክል ነው፡፡  የገዳ ስርዓት ከኦሮሞ መስፋፋት በፊትም ሆነ በኋላ አልነበረም፡፡  ስለዚህም የገዳ ስርዓት የኦሮሞን ሕዝብ ዲሞክራሲያዊነት የሚያመለክት ልዩ ክስተት ሳይሆን የሉባ ጨፍጫፊወች ጭፍጨፋቸውን ለማቀላጠፍ ሲሉ ብቻ የሰረቱት የሉባ ጨፍጫፊወች ዕድር ነው፡፡

የጨፍጨፊወች ዕድር አመራሮች የሚመርጡት የጭፍጨፋውን ቱርፋቶች በተቻላቸው መጠን አመርቂ ለማድረግ በተቻላቸው መጠን ሌት ተቀን ይተጋሉ ተብለው ሙሉ በሙሉ ሲታመንባቸው ብቻና ብቻ ነው፡፡  ስለዚህም ለገዳ ስርዓት አመራርነት የሚታጩት ጭፍጨፋውን በተመለከተ ምንም ዓይነት ቅሬታ፣ ማቅማማት ወይም ማመንታት ይኖራቸዋል ተብለው ሊጠረጠሩ የማይችሉት በሺ የሚቆጠሩ እውነተኛ ኦሮሞወች (ቦረናወች) እንጅ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩት የሞጋሳና የጉዲፈቻ ውጤት የሆኑት ገርባወች አይደሉም ማለት ነው፡፡  አባ ባሕርይ በመጽሐፋቸው መግቢያ ላይ እንደገለጹት፣ የኦሮሞ መስፋፋት የተከናወነው ሰውን ለመግደል እንበለ እንቅልፍ ቀን ከሌት በሚተጋ፣ የሆዱ አውሬ (ኮሶው) እንደ እንስሳ በቋንጃው ላይ በሚፍለከለክ፣ የእንስሳነት ባሕርይ በተጠናወተው አረመኔ ሠራዊት ነው፡፡  ተገዶ ገርባ የሆነ ግለሰብ ደግሞ የገዛ ወገኖቹን ለመጨፍጨፍ እስከዚህ ድረስ አይተጋም፡፡

በቱርክ ነፍጠኞች የተመራው የግራኝ አህመድ ወረራ፣ አማራ የሚባለውን ጀግንነቱ የተመሠከረለትን ታላቅ ሕዝብ ተቋማት ከሞላ ጎደል ሙሉ በሙሉ በማፈራረስ እጅጉን አዳከመው፡፡  የሱማሌን ጅራፍ ይሸሹ የነበሩት የኦሮሞ አርብቶ አድሮች ደግሞ ግራኝ የፈጠረላቸውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ባባ ገዳወቻቸው መሪነት ድንገተኛ አደጋ እየጣሉ፣ በሐይማኖቱ ቀናኢ የነበረውን አማራ ስምንተኛው ሺ ደረሰ እስከሚያስብሉት ድረስ ሴት፣ ወንድ፣ ሕፃን፣ አዛውንት ሳይሉ በሰይጣናዊ ጭካኔ ጨፈጨፉት፡፡  የፈሪ ብትር ሆድ ይቀትር ነውና፣ የነዚህ አንድም ቀን ፊት ለፊት ተዋግተው የማያውቁ ቱርቂወች ብትር ከግራኝ ብትር የከፋበት አማራ፣ ከግራኝ ቁስል እስከሚያገግም ድረስ ምርጫ ስላልነበረው እጅግ ሰፊና ለም ከነበረው ርስቱ እየተፈናቀለ ከኦሮሞ አደጋ ጣዮች ራሱን በቀላሉ ለመከላከል ወደሚችልባቸው ተራሮች በመሸሽ ዝንጀሮቴኔ ኑሮ ለመኖር ተገደደ፡፡  ለዚህ ደግሞ በሸዋ ተራሮች ላይ አማራ ብቻ፣ ሜዳወቹ ላይ ደግሞ ኦሮሞ ብቻ መስፈሩን መታዝብ ብቻ በቂ ነው።

የሉባ ጨፍጫፊወች ደግሞ አማራውን በመጨፍጨፍ የወረሱትን ያማራውን ምድር በየጎሳቸው በመከፋፈል ወረምንትስ፣ ወረቅብጥርስ እያሉ ሰየሙት፡፡  የአማራ አገር ፈጠጋር (አሩሲ)፣ የአማራ አገር እናርያ (ወለጋ)፣ የሀድያ አገር ዳዋሮ (ጨርጨር)፣ የጃንጀሮ አገር ገሙ (ኢሉባቦር)፣ የአገው አገር አንጎት (ራያ)፣ ያማራ አገሮች መካነ ሠላም (ቃሉ)፣ ሠገነት (ወረሂመኖ)፣ ዋሰል (ወረኢሉ)፣ ቤተሳባ (ወረባቦ)፣ ገነቴ (የጁ)፣ ምድረገኝ (ከሚሴ)፣ ላኮመልዛ (ወሎ)፣ ግራርያ (ሰላሌ)፣ ገንዝ (ጅባትና ሜጫ)፣ ወጂ (ወንጂ)፣ ሸምብራ ቁሬ (ዱከም)፣ በራራ (ፊንፊኔ) እየተባሉ የመስፋፋት ስም ተሰጣቸው፡፡

አማሮች ነፍጥንና አነፋፈጥን ከፖርቱጋሎች ተምረው ግራኝን አሸንፈው ካገገሙ በኋላ ፊታቸውን ወደ ኦሮሞ ተስፋፊወች አዞሩ፡፡  አደጋ መጣል እንጅ መዋጋት የማይችለው የኦሮሞ ተስፋፊ ባራት ማዕዘናዊ የውጊያ ጥበብ (ፊታውራሪ፣ ግራዝማች፣ ቀኛዝማች፣ ደጃዝማች) በተካኑት አማሮች ፊት መቆም አቃተው፡፡  የነፍጥ ድምጽ ሲሰማ ኦቦው ካቦ ሸማኔ ፈጠነ፡፡   የቱርክ ነፍጠኞች በከፈቱለት ሰፊ በር ያለ ምንም ፊት ለፊት ውጊያ ሰተት ብሎ የገባው የኦሮሞ ተስፋፊ፣ ነፍጥና ነፍጠኛ የሚሉትን ቃሎች አምርሮ ጠላቸው፡፡  ሰይጣኑ፣ ጭራቁ በነፍጠኛ ተመሰለ፡፡  ራቡ፣ ጥማቱ፣ ማይምነቱ፣ አረመኔነቱ በነፍጠኞች ተሳበበ፡፡

አማሮች ግራኝን ድል ነስተው የሉባን ጭፍጭፋ ሲያስቆሙት፣ ጭፍጨፋውን ለማቀላጠፍ ሲባል ብቻ የተሰረተው የሉባ ገዳ ግልጋሎቱን ስለጨረሰ ወዲያውኑ አከተመ፡፡  በጭፍጨፋው ቱርፋቶች ክፍፍል ላይ እጅጉን የተጠቀሙት የጭፍጨፋው ዕድር ዐባሎች አባ ጅፋር፣ አባ ምንትስ የሚባሉ አምባገነኖች ሆኑ፡፡  በክፍፍሉ የተጎዱት የጭፍጭፋው ዕድር አባሎች በክፍፍሉ በተጠቀሙት ላይ ሲያምፁ ደግሞ ፣ የጎዳችሁ አማራ እንጅ እኛ አይደለንም ተባሉና ፀራማራ ትርክት ተጀመረ።

በሉባ ጨፍጫፊወች የተጨፈጨፈው ያማራ ሕዝብ ጭፍጨፋውን ስላስቆመና ርስቱን በትንሹም ቢሆን  ስላስመለሰ ብቻ የኦሮሞ ጨቋኝ ተደረጎ ተሳለ፡፡  አማራ ከመስፋፋት ባይገታን ኖሮ፣ አማራ ወደኋላ ባይመልሰን ኖሮ፣ አማራ እንዲህ ወይም እንዲያ ባያደርገን ኖሮ እያሉ ማላዘን ብቸኛ መጽናኛ ሆነ፡፡  ያማራ ጥላቻ ተለኮሰ፡፡  አማራን ካለጠፋነው ያጠፋናል የሚለውን የሮማን ፕሮቻዝካን (Roman Prochazka) ሐሳብ የጦቢያ ፖሊሲያቸው የማዕዘን ዲንጋይ ያደረጉት ምዕራባውያን ደግሞ ሙሐመድ ሐሰንን በመሳሰሉ የኦሮሞ ‹‹ምሁሮች›› አማካኝነት በእሳቱ ላይ ቤንዚን ጨመሩበት፡፡  እሳቱም እንደ ሰደድ ተስፋፋ።

የሙሐመድ ሐሰን ምሁርነት ሙሉ በሙሉ የተገነባው ኦሮሞን ቤተኛ ሐበሻን መጤ በሚለው ባዱ ትርክቱ ነው፡፡  ይህን ትርክት ግን ብዙም ሐተታ ሳያስፈልግ አጥቂን በቀላሉ ለመከላከል በሚቻልባቸው በኦሮሞ ወቅያኖስ ውስጥ በሚገኙት ዝቋላንና ዝዋይን በመሳሰሉት ደሴቶች የሚኖሩት ጥንታዊ አልኦሮሞወች (ኦሮሞ ያልሆኑ ጦቢያውያን) ከየት መጡ? በሚል አንድ ጥያቄ ብቻ ቆሻሻ ቅርጫት መጣል ይቻል ነበር፡፡

የነ ሙሐመድ ሐሰን ውሸት በእንጭጩ ሳይጋለጥ ቀርቶ ይህን ያህል ገዝፎ፣ ይህን ያህል ሕዝብ ለማሳሳት በመብቃቱ ዋናወቹ ተወቃሾች የጦቢያ የታሪክ ምሁራን የሚባሉት ግለሰቦች ናቸው፡፡  እነዚህ ምሁራን በምእራባውያን ታሪክ በመራቀቅ በሰው ወርቅ ለመድመቅ ሲሞክሩ፣ እነ ሙሐመድ ሐሰን በሰፊው የጦቢያ የታሪክ መስክ ላይ ያለ ምንም ተቀናቃኝ እንደ ልባቸው ፏለሉበት፡፡

ዋሾና ውሸቱ አይናቁም፡፡  ተጋጣሚው የቀረ ቡድን በፎርፌ ያሸንፋል፡፡  እነ ሙሐመድ ሐሰን ደግሞ የእስካሁን ግጥሚያወቻቸውን ሁሉንም ያሸነፉት በፎርፌ ነው፡፡  ካሁን በኋላ ግን ፎርፌው መቆም አለበት፡፡  መቆም ያለበት ደግሞ ጋጠወጦቹ የኦሮሞ ጎጠኞች ከፈሪነት በሚቆጥሩት፣ አህያ የበቅሎ አባት በሚባልበት ካህንኛ (politically correct) ዘይቤ ሳይሆን፣ አህያ አህያ በሚባልበት መዕምንኛ (politically incorrect) ዘይቤ ነው፡፡  ጥያቄው የህልውና ጥያቄ ስለሆነ፣ እንትን ብንል እንትና ይቀየማል የሚባልበት አይደለም፡፡  ሐቅ የሚያንቀው ጓጉሮ ይሙት፡፡

እየየም ሲደላ ስለሆነ፣ በሞት ሽረት ትግል ላይ ትህትናና ጨዋነት ይቅሩና ሰብአዊነትና ዲሞክራሲም ቅንጦት ናቸው፡፡  ለዚህ ማስረጃ ደግሞ ሰብአዊነትና ዲሞክራሲ ከኔ ወዲያ ላሳር የሚለው ያሜሪቃ መንግሥት በሁለተኛው ያለም ጦርነት ወቅት የገዛ ራሱን ዜጎች (እንጥፍጣፊ የጃፓን ደም ስላላቸው ብቻ) ከወንጀለኛ ቆጥሮ ሕፃን፣ ሴት፣ ወጣት፣ አዛውንት ሳይል ንብረታቸውን ነጥቆ፣ የዜግነት መብታቸውን ገፍፎ ሰብጉረኖ (concentration camp) ውስጥ ማጎሩን መጥቀስ ብቻ ይበቃል፡፡

አጼ ምኒልክን ወራሪ የሚሉ፣ ወራሪው አጼ ምኒልክ ሳይሆኑ በሉባወች የሚመራው የገዳ አረመኔ ሠራዊት እንደሆነ በግልጽ ሊነገራቸው ይገባል፡፡  ፊንፊኔ ኬኛ ሲሉ የቆጡን አወርድ ብለው የብብታቸውን እንዳይጥሉ ማስጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡  ቆንጨራ ሲያነሱ ደግሞ አፈሙዝ ማዞር የግድ ነው፡፡

አጼ ምኒልክ ያደረጉት ድርጊት ቢኖር በገዳ ሠራዊት ማንነቱን የተነጠቀውን ገርባ ወደ ቀድሞ ማንነቱ መመለስ ነበር፡፡  አጼ ምኒልክ የሚወቀሱ ከሆነ፣ ሊወቀሱ የሚገባቸው ምልሰቱን ምሉዕ ባለማድረጋቸው ብቻና ብቻ ነው፡፡  በግዴታ የተጫነ የተስፋፊ ቋንቋ ከተጫነበት ምድር ላይ ሙሉ በሙሉ የግድ መክሰም፣ በዚህ ቋንቋ የተሰየሙ ቦታወችና ስሞች ደግሞ ወደ ቀድሞ ስያሜወቻቸው ሙሉ በሙሉ የግድ መለወጥ ነበረባቸው፡፡  ኦነጋውያንን ፊንፊኔ ኬኛ፣ ከሚሴ የኛ እያሉ ለመበሻቀጥ የበቁት አጼ ምኒልክ ምልሰቱን ምሉዕ ባለማድረጋቸው ነው፡፡  የኦሮሞ ስም በግዴታ የተለጠፈበት ገርባ ደግሞ የቦረና ደም ያለበት እየመሰለው ከእውነተኞቹ ቦረኖች በላይ ጽንፈኛ የሆነው በዚሁ ባጼ ምኒልክ ስህተት ነው፡፡  ለማ መገርሳ፣ ሕዝቀኤል ጋቢሳ፣ ጸጋየ አራርሳ፣ በቀለ ገርባ፣ ዮሐንስ (ሌንጮ) ለታ፣ አንዳርጋቸው ጽጌ ቂጢሳ ቦረኔ ሳይሆኑ ቦረኔ ነን የሚሉ ያጼ ምኒልክ ስህተት ውጤቶች ናቸው፡፡

ለምሳሌ ያህል “ያማራ ሕዝብ ከየት ወደ የት?” በሚለው መጽሐፉ ያማራ ብሔርተኛ መስሎ የቀረበውና፣ “ትውልድ አይደናገር እኛም እንናገር” በሚለው መጽሐፉ ደግሞ ቀኝኋላ በመዞር የለየለት ፀራማራ ሁኖ የቀረበውን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቂጢሳን እንውሰድ፡፡  አባ ባሕርይ ዜናሁ ለጋላ (ምዕራፍ 12) ላይ እንደገለጹት ሸዋን ሙሉ በሙሉ አጥፍቶ ጎጃምን መውጋት የጀመረው ሮበሌ የሚባለው ወሮበላነቱ ወደር ያልነበረው ሰባተኛው ሉባ ነበር፡፡  ስለዚህም ያቶ አንዳርጋቸው ቤተሰቦች ሸዌወች ከሆኑ የሮበሌ ገርባወች እንደነበሩ በሙሉ እርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡  ስለዚህም አጼ ምኒሊክ የሸዋ ገርባወችን በእውነተኛ ስሞቻቸው እንዲሰየሙ አስገድደዋቸው ቢሆን ኖሮ፣ ቂጢሳና ከዚያ በላይ ያሉት የሱ ያልሆኑ የቦረና ስሞች በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ባልተለጠፉበት ነበር፡፡  እሱም ደግሞ ቦረኔ ነኝ በማለት የጊዜውን የፖለቲካ ቁማር ለመጫወት ምክኒያት ባላገኘ ነበር፡፡  አጼ ምኒልክን ደግሞ አምርሮ ከመወቀስ ይልቅ ቢያንስ ቢያንስ እሱና አባቱ በራሳቸው ቋንቋ አንዳርጋቸውና ጽጌ ተብለው እንዲጥሩ ስላስቻሏቸው አብዝቶ ባመሰገናቸው ነበር፡፡

ኦነጋውያን ክልላችን ነው በሚሉት ልቦለዳዊ ክልል ውስጥ የሚገኙትን ቦታወች ዱከም፣ ቢሸፍቱ፣ አዳማ፣ ውንጂ እያለ ሲጠሩ፣ ያማራ መሠረት በሆነው በምድረ አምሓራ (ወሎ) ውስጥ የሚገኙትን ቦታወች የጁ፣ ራያ፣ ቃሉ፣ ወረኢሉ፣ ወረባቦ እያሉ መጥራት ያማራን ሕዝብ ሆደሰፊነት፣ ትልቅነትና ጨዋነት ቢመሰክርም በሌላ አንጻር ግን እጅግ በጣም ያሳፍራል፡፡  ጨዋ መሆን የሚያስፈልገው ጨዋነትን ለሚያውቅ ብቻ ነው፡፡  ኦነጋውያን ደግሞ ጨዋነት አልተፈጠረባቸውም፡፡  ኦነጋዊው ዐብይ አህመድ የሚያበሻቅጠውን ደብረጽዮንን እያሽሞነሞነ፣ የሚያከብረውን አምባቸውን የረሸነው ጨዋነቱን ከፍራት ስለቆጠረው ብቻ ነበር፡፡

ወደ ቅርብ ታሪክ ስንመለስ ደግሞ፣ ኦነግ ስለ ልቦለዳዊው አኖሌ ሲያላዝን በእውነተኛው አርባጉጉ ሊወነጀል ይገባል፡፡  የኦሮሞ ጽንፈኛ ምዕተ ዓመታት ወደ ኋላ ሂዶ ተስፋየ ገብረአብ እና በረከት ስምኦን የተባሉ አማራጠል እኩይ ቧልተኞች (evil comedians) የጻፉለትን ልቦለዳዊ ስቅጠት (fictional trajedy) ቀን ከሌት እያነበነበ፣ ለኻጩን እያዝረበረበ ሲነፋረቅ፣  ያማራ ሕዝብ ግን አሁን ትናንትና የተፈጸሙበትን በምስል የተደገፉ አረመኔያዊ ጭፍጨፋወች ከናካቴው መርሳቱ ይቅር የማይባል ኀጢያት ነው፡፡  ለልቦለዳዊው አኖሌ የቆመው ሐውልት ፈርሶ፣ በፍርስራሹ ላይ ፈጠጋርን (አሩሲን) መሉ በሙሉ ያጠፋት ያራተኛው ሉባ የቢፎሌ ሰለባ የሆኑት ያማራ ሰማዕታት ሐውልት መገንባት ይኖርበታል፡፡

ለማጠቃለል ያህል የኦሮሞ ሕዝብ ገዳ የሚባል አፍሪቃ በቀል ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የሰረተ ዲሞክራሲያዊነትን የተላበሰ ዲሞክራቲክ ሕዝብ ነው የሚባለው ትርክት ምንም መሠረት የሌለው የቱሪናፎች ባዶ ቱልቱላ ነው፡፡ በመጀመርያ ደረጃ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንጅ ዲሞክራሲያዊ ሕዝብ የለም፡፡  በሁለተኛ ደረጃ ገዳ ጭፍጨፋን ለማሳለጥ ሲባል ብቻ የተመሠረተ ጊዜያዊ የጨፍጫፊወች ዕድር እንጅ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት አይደለም።  እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ዓይንና ናጫ የነበሩት የኦሮሞ ፅንፈኞች፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሰምና ሙጫ የሆኑት የዘመናችን ግራኝ የነበረው ወያኔ ክፉኛ ያዳከመላቸውን አማራን መጨፍጨፍ ስለጀመሩ ብቻ ነው።

ግራኝ ሙሐመድ አማራውን እጅጉን በማዳከም ላስራ ስድስተኛው ክፍለዘመን የሉባ ጭፍጫፊወች በር እንደከፈተ፣ የደደቢቱ ወያኔ ደግሞ አማራውን እጅጉን በማዳከም ለዘመናችን የሌንጮ ጭፍጫፊወች በር ከፈተ፡፡  የጭፍጨፋ በር የተከፈተላቸው ነጭ አምላኪ የሆኑት የሌንጮ ጨፍጫፊወች ደግሞ ልክ እንደ ሉባ ጨፍጫፊወች ጭፍጨፋቸውን የሚያሳልጡበት የጨፍጫፊወች ዕድር መሠርቱና ዕድሩን ገዳ ከማለት ይልቅ የሮማን ፕሮቻዝካ (Roman Prochazka) ደቀመዝሙር የነበረው ሚሽነሪው ዮሐንስ ክራፍ (Johann Ludwik Krapf) ባወጣላቸው ትናንት መጤ፣ ዳህራዊ ስም ኦሮሙማ አሉት ።

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/188916
‹‹ዳይኖሰርስ ከእነ ነፍሱ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብትል ሰላም ከሌለ ማንም ሊጎበኝ አይመጣም›› በኢትዮጵያ የጦርነት ኢኮኖሚ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በአመት ኪሳራ ተመዝግቦል!!!
(ክፍል አንድ)                             ሚሊዮን ዘአማኑኤል (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

የተባበሩት መንግሥታት (United Nations Human Rights Council)፡- የተባበሩት መንግሥታት በአማራ ክልል ወንጀሎችና ስብዓዊ ቀውስ መጨመር በሰው ዓልባ አውሮፕላን (ድሮውን)ና በነፃ እርምጃ ንፁሃን ዜጎች መጨፍጨፍ በተመለከተ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን እንዲቆቆምና በፊት የነበረው ኮሚሽን ደግም እንዲሰራ ወንጀለኞቹ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተወስኖል፡፡ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ በየሃገሩ ገለልተኛው አጣሪ ኮሚሽን ሥራውን በአስቸኳይ እንዲጀምር ድጋፋችሁን ማሰማት ይጠበቅባችኃል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት በአማራ ክልል እየተፈፀመ ያለውን የዘር ጭፍጨፍ (ጀኖሳይድ) በድሮውን ጥቃት 70 ንጹሃን ዜጎች በፍኖተሰላም መፈፀሙን፣ በደብረ ብርሃን ከተማ በከባድ መሣሪያ ንፁሃን ዜጎች መገደልና በተሸሸጉበት ስፍራ ሆስፒታል፣ ቤተክርስቲያነ ፣ ትምህርት ቤት ውስጥ በግፍ መገደል፣ ባህር ዳር ከተማን በተወንጫፊ ከባድ መሳሪያ መደብደብየተነሳ በመቶ የሚቆጠሩ ንጡሃን አማራዎች ተገድለዋል፣በጎንደር የተነሳ ጦርነት ከሃያ ንፁሃን አማራዎች ተገለዋል፣ሁለት መቶ ቆስለዋል፣ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ንጡሃን ዜጎች መታገትና በኃይል መሠወር በተባበሩት መንግሥታት የአማራ ጀኖሳይድ ሪፖርት  ላይ በሰፊው ተገልፆል፡፡ ሙሉውን ከድረገፁ ያንብቡት፡፡ The international community's swift and resolute action is crucial to addressing the deteriorating Amhara genocide in Amhara Region of Ethiopia: The atrocities being committed against the Amhara people in the Amhara region of Ethiopia are deeply concerning and require immediate attention. The following incidents provide a glimpse into the severity of the ongoing crisis:…………………………..(1)

 

የኮነሬል አብይ አህመድ  የኦህዴድ ብልፅግና አንባገነን መንግሥት በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያን በጦርነት ኢኮኖሚ ውስጥ ዘፍቆ ሃያ ስምንት ቢሊዮን ዶላር የመሰረተልማት ውድመት ያስከተለና አንድ ሚሊዮን ወጣቶችን ጭዳ ያደረገ ፋሽስታዊ መንግስት በአስቸኮይ ከሥልጣን ካልተወገደ በጦርነት የሰው እልቂትና ርሃብ እጣ ፈንታችን ሆኖ ይቀጥላል:: ኢትዮጵያ የጦርነት ኢኮኖሚ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በአመት ኪሳራ ተመዝግቦል! እንደ ቶፕ ቴን ቪፒኤን መሠረት በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለው የኢንተርኔት አገልግሎት መዘጋት የተነሳ ሀገሪቱ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶባታል፡፡

በኢትዮጵያ የጦርነት ኢኮኖሚ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በአመት ኪሳራ ተመዝግቦል፡፡ በሪፖርቱ መሠረት የኮቪድ 19 እና የትግራይ ጦርነት በጣምራ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ  የሁለት ቢሊዮን ዶላር ገቢ በአመት ኪሳራ በአለፈው ሁለት አመታት አስከትሎል፡፡ በቀጣይነት በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው ጦርነት እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጂ የተነሳ ብዙ አገሮች ለዜጎቻቸው የጉዞ ማስጠንቀቂያ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይሄዱ በማሳሰባቸው የቱሪስቶች ቁጥር ሲቀንስ የሃገሪቱን ዓለም አቀፍ የቱሪስት መስህብነትና ዝና የነበራትን ስምና ክብር  ሊጠለሽ ችሎል፡፡ Reports estimate that combined, the COVID-19 pandemic and violence in Tigray cost Ethiopia’s tourism industry two billion dollars yearly over the last two years in lost revenue. Following the conflict in the Amhara region and announcement of a state of emergency, several countries issued stern travel warnings advising their citizens not to visit areas affected by violence or unrest. This decline in visitors has damaged Ethiopia’s reputation as a stable tourist destination worldwide, according to Henok……………………….…………..(2)

በአገልግሎት ዘርፍ ውስጥ የሚካተተው  የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍል ሲሆን ወደ አገር ቤት የገቡ የቱሪስቶች ቁጥር (Number of tourists) ዘርፉ በውጪ ምንዛሬ ያስገኘ ገቢ (Receipts) እንዲሁም  ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) (% of GNP) በመቶኛ  ሲሰላ ያለውን ከ2017 እስከ 2021እኤአ የቁልቁለት ጉዞን በማስረጃ እንቃኛለን፡፡

- በ2017እኤአ ወደኢትዮጵያ የመጡ 933,000 (ዘጠኝ መቶ ሠላሳ ሦስት ሽህ) ቱሪስቶችን  በማስተናገድ  ከፍተኛው ክብረ ወሰን ነበር፣51 (ሁለት ቢሊዮን ነጥብ ሃምሳ አንድ) ዶላር የውጪ ምንዛሬ ያስገኘ ሲሆን ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት(ጂዲፒ) 3.1 % (ሦስት ነጥብ አንድ)በመቶ ሸፍኖ ነበር፡፡

- በ2018እኤአ ወደኢትዮጵያ የመጡ 849,000 (ስምንት መቶ አርባ ዘጠኝ ሽህ) ቱሪስቶችን  በማስተናገድ፣55 (ሦስት ቢሊዮን ነጥብ ሃምሳ አምስት) ዶላር የውጪ ምንዛሬ ያስገኘ ሲሆን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 4.2 % (አራት ነጥብ ሁለት) በመቶ ሸፍኖ ነበር፡፡

- በ2019እኤአ ወደኢትዮጵያ የመጡ 812,000 (ስምንት መቶ አስራሁለት ሽህ) ቱሪስቶችን  በማስተናገድ፣53 (ሦስት ቢሊዮን ነጥብ ሃምሳ ሦስት) ዶላር የውጪ ምንዛሬ ያስገኘ ሲሆን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 3.7 % (ሦስት ነጥብ ሰባት) በመቶ ሸፍኖ ነበር፡፡ Ethiopia tourism statistics for 2019 was 3,529,000,000.00, a 0.54% decline from 2018.

- በ2020እኤአ ወደኢትዮጵያ የመጡ 518,000 (አምስት መቶ አስራስምንት ሽህ) ቱሪስቶችን  በማስተናገድ፣28 (ሁለት ቢሊዮን ነጥብ ሃያ  ስምንት) ዶላር የውጪ ምንዛሬ ያስገኘ ሲሆን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 2.1 % (ሁለት ነጥብ አንድ) በመቶ ሸፍኖ ነበር፡፡ Ethiopia tourism statistics for 2020 was 2,282,000,000.00, a 35.34% decline from 2019.በ2021እኤአ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ 518,000  (አምስት መቶ አስራስምንት ሽህ) ቱሪስቶችን  በማስተናገድ፣ 2.60 (ሁለት ቢሊዮን ነጥብ ስድስት) ዶላር የውጪ ምንዛሬ ያስገኘ ሲሆን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 2.3 % (ሁለት ነጥብ ሦስት) በመቶ ሸፍኖ ነበር፡፡

- በ2022 እና 2023እኤአ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቱሪስቶች ቁጥር በጣም በመቀነሱ የተነሳ መረጃውን መንግሥት ደብቆል፡፡ በሆቴልና ቱሪዝም የተገኘው የውጪ ምንዛሬ አልተገለፀም  ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት በመቶ የሸፈነው አልተሰላም፡፡

- በ2024 እኤአ በኢትዮጵያ የሆቴል ገበያ ገቢ 1.14 (አንድ ቢሊዮን ነጥብ አስራ አራት) ዶላር እንደሚገመትና ከ2024 እስከ 2028 እኤአ  እድገቱ 6.01 በመቶ እንደሚሆን ተተንብዬል፡፡ By 2024, the Hotels market in Ethiopia is projected to reach a revenue of US$1.14bn, with an expected annual growth rate (CAGR 2024-2028) of 6.01%. This growth is expected to result in a projected market volume of US$1.44bn by 2028.

 

ዝነኛው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ ‹‹አትሌት ኃይሌ፡- ይህ በጣም ከባድ ነው፡፡ እንደምትሰማው እንዲያውም በአሁኑ ሰዓት ሆቴሎች እየተዘጉ ነው፡፡ ይህ ማለት ቱሪስት ወይም ተጠቃሚ እየጠፋ ነው ማለት ነው፡፡ ተጠቃሚው በአንድ በኩል በቱሪስትነት ነው የሚመጣው ወይም ደግሞ በስብሰባ ነው የሚመጣው፡፡ የፈለገውን ያህል በወርቅ ለብጠን ሆቴል ወይም ሪዞርት ብንሠራ ሰላም ከሌለ ማንም መጥቶ አይጠቀምም፡፡ ሌላው ይቅርና ኢትዮጵያ ውስጥ ዳይኖሰርስ አለ ብትል እንኳ ሰላም ከሌለ ማንም መጥቶ መጎብኘት አይፈልግም፡፡ የዛሬ ስንት ሚሊዮን ዓመት የጠፋው እንስሳ ዳይኖሰርስ ከእነ ነፍሱ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብትል ሰላም ከሌለ ማንም አይመጣም፡፡ አንድ ቱሪስት መጀመሪያ የሚያስቀምጠው መጀመሪያ ለመቀመጫዬ እንዳለችው እንስሳ ሕይወቱን ነው፣ ይህንን መገንዘብ አለብን፡፡ እንደ ሕዝብም፣ እንደ መንግሥትም ይህንን ካላደረግንና ሰላምን ካላረጋገጥን እንኳን ቱሪስት ለማምጣት ቀርቶ አንተም እኔም ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስም አንችልም፡፡››…………………………………………….(3)

የኢትዮጵያ ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት መቶ አስራአንድ ቢሊዮን ዶላር በ2021እኤአ እንደነበር የዓለም ባንክ አስታውቆ ነበር፡፡ (Gross domestic product: 111.3 billion USD (2021) World Bank)

- ግብርና ዘርፍ (Agriculture):- የኢትዮጵያ ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት(ጂዲፒ) በየዘርፉ ግብርና ዘርፍ (Agriculture: 35.5%) ሠላሳ አምስት ነጥብ አምስት በመቶ ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት ይሸፍናል፡፡ የግብርናው ዘርፍ የሰው ኃይል አቅርቦቱ (agriculture: 72.7%) ሰባሁለት ነጥብ ሰባት በመቶ የሰው ኃይል ይሸፍናል፡፡

- የኢንዱስትሪ ዘርፍ (Industry):-የኢትዮጵያጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት(ጂዲፒ) በየዘርፉ የኢንዱስትሪ ዘርፍ (Industry: 23.11%) ሃያ ሦስት ነጥብ አስራአንድ በመቶ ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት ይሸፍናል፡፡ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የሰው ኃይል አቅርቦቱ (industry: 7.4% ) ሰባት ነጥብአራት በመቶ የሰው ኃይል ይሸፍናል፡፡

- የአገልግሎት ዘርፍ (Services):-የኢትዮጵያ ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት(ጂዲፒ) በየዘርፉ የአገልግሎት ዘርፍ (Services: 36.81%) ሠላሳ ስድስት ነጥብ ሰማንያ አንድ በመቶ ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት ይሸፍናል፡፡ የአገልግሎት ዘርፍ የሰው ኃይል አቅርቦቱ (services: 19.9%) አስራ ዘጠኝ  ነጥብ ዘጠኝ በመቶ የሰው ኃይል ይሸፍናል፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊሪፓብሊክ ሕገ-መንግሥት፣ አንቀፅ 42 ‹‹የመዘዋወር ነፃነት›› መሠረት አንደኛ/ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ይም በሕጋዊ መንገድሀገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ በመረጠው የሀገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖሪያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሀገር የመውጣት ነጻነት አለው፡፡ ሁለተኛ/  ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወደ ሀገሩ የመመለስ መብት አለው፡፡››

ኮነሬል አብይ አህመድ የብልጽግና ሹማምንት የሆኑትን ፓስፖርት በማገት ያለእሳቸው ፍቃድ ማንም ባለስልጣን ከአገር መውጣት እንደማይችል በማሳወቅ የጠቅላይ ሚንስርነትና የኢሚግሬሽን ኃላፊነቱንም ጠቅልለዋል፡፡ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ስዩም መስፍን፣ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ወዘተ ከአገር ኮብልለዋል፡፡

 

‹‹ከሰሞኑ ዓይተናል ሁላችንም ከአዲስ አበባ ለመውጣት እንኳ እየተሳቀቅን ነው፡፡ እኔ ለምሳሌ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው እዚህ ሶዶ በአውሮፕላን የመጣሁት፡፡ በአውሮፕላን መጥቼ አላውቅም፡፡ መኪናዬን እየነዳሁ ከሶዶ አልፌ አርባ ምንጭ ደርሼ ሥራዬን ሠርቼ እመለሳለሁ፡፡ ሰሞኑን ግን ያሠጋል፡፡ በመኪና መሄድ አትችልም አሉኝ፡፡ እንዴት የማውቀውን መንገድ ትከለክሉኛላችሁ ብልም በፍፁም አይሆንም አሉኝ፡፡ ሐዋሳ በአውሮፕላን ለመሄድ ? ኧረ ባካችሁ ግፍ ነው ነበር ያልኩት፡፡ እንዲህ ባለው አስገዳጅ ሁኔታ ግን በመኪና መሄድ የሚቻሉ ቦታዎችን በአውሮፕላን ለመሄድ ትገደዳለህ፡፡ ይህ ሁኔታ ቱሪስቱን ብቻም ሳይሆን፣ የብዙ ሺሕ ሠራተኛ ኃላፊነት ያለበት እንደ እኔ ያለውን ሰው እንቅስቃሴም ይገድባል። ይህንን ቆም ብለን ሁላችንም ልናስብበት ይገባል፡፡››

(1) የመለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊሪፓብሊክ ሕገ-መንግሥት፣አንቀፅ 49 መሰረት ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ልዩ ጥቅም ይጠበቅላታል ባለው መሠረት የአማራ፣ የትግራይ፣ የዶርዜ ሰዎች አዲስ አበባ እንዳይገቡ በማድረግ ልዩ ጥቅምማቸውን ተግባራዊ አድርገዋል፡፡ ህወሓት ለትግራየ ህዝብ በፕሪቶሪያ ስምምነት ያስገኘው ጥቅም ቢኖር ተጋሩ አዲስ አበባ እንዳይገባ ማድረግ ነው፡፡

(2) የአማራ ህዝብ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ከተማ መግባት ተከልክለዋል፡፡ ተላላኪዎቹ ብአዴኖች ከባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ደብረብርሃን ከተሞች መግባትም መውጣትም አልቻሉም፡፡ ብአዴን ብልፅግና አባላት ወደ ውጪ አገራት መሄድ አይችሉም፣ፓስፖርታቸው ኮነሬል አብይ እጅ ነው፡፡

(3) ህወሓት ኢህአዴግ ከትግራይ ክልል ወደ ሌሎች ክልሎች መንቀሳቀስ አይችሉም፡፡ ህወሓት ኢህአዴግ አባሎች ወደ ውጪ ሀገራትም መጎዝን መንቀሳቀስ አይችሉም፡፡ ተጋሩ ከትግራይ ክልል ወደ ሌሎች ክልሎች መሄድና መምጣት አልቻሉም፡፡ ህወሓት ለታላቁ የትግራየ ህዝብ ያጎናፀፈው መብትና ነጻነት በኦህዴድ ብልጽግና ባርነት ስር ወድቆል፡፡

(4) ዶርዜዎች ከአዲስ አበባ ንዋሪ ነበሩ አስር ሽህ ዶርዜዎች ወደ አርባ ምንጭ በግፍ ተሸኝተዋል፡፡

(5) የኦነግ ሸኔ እገታና ኦህዴድ ብልፅግና የአማራ ዜጎች ላይ ያነጣተረ እገታና የቻይና የህንድ ዜጎች እገታ

ቱሪስትና የኢንተርኔት ዓለም፡- የኮነሬል አብይ አህመድ  የኦህዴድ ብልፅግና አንባገነን መንግሥት በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ኢንተርኔት የሚከረችም መንግሥት ነው፡፡ ቱሪስቶች ኢንተርኔት አገልግሎት በሌለበት ሀገር ምን ሊሰሩ ይመጣሉ? እንኳን ቱሪስቶች ሀገር በቀሉ ዲያስፖራ አገር ቤት መምጣት ከአቆመና በሃዋላ የሚልከውን የዶለር ፍሰቱን በማቆም የኮነሬል አብይን መንግሥት በመፋለም ላይ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከአፍሪካ አህጉር ዝቅተኛ ሲሆን ከጠቅላላው ሕዝብ ቁጥር 16.7 (አስራ ስድስት ነጥብ ሰባት) በመቶ በ2021እኤአ እንደነበር የዓለም ባንክ አስታውቆ ነበር፡፡ (Internet users: 16.7% of the population (2021) World Bank)

· Jan 9, 2024 — እንደ ቶፕ ቴን ቪፒኤን መሠረት በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለው የኢንተርኔት አገልግሎት መዘጋት የተነሳ ሀገሪቱ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶባታል፡፡ According to a report by Top10VPN, Ethiopia experienced the second largest economic losses globally as a result of government-mandated internet ..( News: Internet shutdown costs Ethiopia nearly $2 billion in .../Addis Standard/https://addisstandard.com › Business)

- Jan 12, 2023 —  ኢትዮጵያ በ2020 እኤአ በኢንተርኔት የምታገኘው ገቢ በመቶ ሚሊዮኝ ዶላር ኪሳራ ሲደርስበት  በ2021እኤአ ደግሞ መቶ ስልሳአራት ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶባታል፡፡A new report by Top10VPN ... In 2020, the country lost $100 million tointernet outage which rose to $164.5 million in 2021, affecting 21.3 ...( Ethiopia lost $146 million due to internet blackouts in 2022//Quartz | Make business better.™️/https://qz.com › ethiopia-lost-146-million-due-to-internet...)

- Jan 16, 2023 — በኢትዮጵያና ትግራይ የሁለት አመት ጦርነት የኢንተርኔት መዘጋት የተነሳ አራት መቶ አስር ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ  ደርሶባታል፡፡ A war in the Tigray region of Ethiopiahas caused a two-year-long internet shutdown, costing the country an estimated $410 million. (Ethiopia has lost $410 million to a war-induced internet ... /Ventures Africa/https://venturesafrica.com › ethiopia-has-lost-410-million...)

ምንጭ

 

- (1)Urgent Call to Address Escalating Human Rights Violations and Crisis in Amhara, Ethiopia (https://documents.un.org/doc/undoc/gen/g24/025/69/pdf/g2402569.pdf?)

- Tourism faces existential crisis/ByAbraham Tekle/August 19, 2023

- ‹‹ዳይኖሰርስከእነ ነፍሱ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብትል ሰላም ከሌለ ማንም ሊጎበኝ አይመጣም›› አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ/ ሪፖርተር ጋዜጣ በዮናስ አማረ/February 11, 2024

ተፃፈ 23/2/2024

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/188907

Thursday, February 22, 2024

ወጣት ሆይ! እንደ ቀደምቱም ሆነ  እንደ አድዋና አምስቱ ዘመን አርበኛ ፋኖዎች ሸለል ፎክር!
በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

አንዳንድ ባህላቸውና ማንነታቸው ሸጠው የዘቀጡ አህያውን ቢፈራ ዳውላውን አይነት ምሁር ተብዮዎች ተጭራቅ ወሮበላ ገዥዎች ጋር በጓዳ በር እየሰሩ “ወደ ሁላ ያስቀረን ባህላችን ነው” እያሉ እንደ በፊቱ ድፍን አፍሪካ፣ ኤሽያና ደቡብ አሜሪካ ባርያ ሊያደርጉህ ሲዳዱ ይስተዋላሉ፡፡ ተጭራቅ ገዥዎች በተጨማሪ አገሪቱን ወደ ሁዋላ ያስቀሩ እነዚህ የራሳቸውን ባህልና ሃይማኖት አሽቀንጥረው ጥለው የምእራቡንም የምስራቁንም እድፍ በጭንቅላታቸው የተሸከሙ ምሁር ተብዮዎች እንደሆኑ ይክዳሉ፡፡ ወጣት ሆይ! ለእንደዚህ ዓይነት ራሳቸውን የሸጡ ድስኩራም ከሀዲ ምሁራን ጆሮህ ጥጥ ነው፡፡ አትስረቅ፣ አትዝረፍ፣ አታታል፣ አታወናብድ፣ ሰውን በዘሩ አትለይ፣ እሬሳ አትጎትት፣ ሳይነኩህ አትንካ፣ ጥቃትን አትታገስ፣ ከመለኮት በቀር ለማንም ላለመገዛት ሸልልና ፎክር የሚል ባህል ወደር የሌለውና የተቀደሰ ባህል መሆኑን የምታውቀው ነው፡፡ ስለዚህ ከመለኮት ውጪ ለማንም ላለመገዛት እንደ እንደ ቀደምቱም ሆነ እንደ አድዋና አምስቱ ዘመን አርበኛ ፋኖዎች ዝንተ ዓለም ሸልል! ፎክር!

 

የካቲት፣ መጋቢትና ሚያዚያ አርበኞች ደማቸውን እንደ ጅረት አፍሰውና አጥንታቸውን እንደ እሾህ ከስክሰው በድል አገር፣ ነፃነት፣ ክብር፣ ሃይማኖትና ባህልን ያስጠበቁባቸው ወራቶች ናቸው፡፡ እነዚህ አርበኞች ልቡ እንደ እንቧይ ያበጠበትን ተስፋፊ በመርፌ እንደተወጋ ፊኛ እያስተነፈሱ ለበርካታት ድሎች የበቁት በሃይማኖታቸው ተጠምቀው፤ ሽለላ፣ ፉከራና ሰምና ወርቅ ዘፈኖችን እንደ ማርና ወተት እየተመገቡ ስላደጉ ነው፡  ሽለላ፣ ፉከራና ባህላዊ ዘፈኖች የጀግና መፀነሻ ማህፀኖች፣ የፋኖ መወለጃ ወለሎች፣ የአርበኛ መጠመቂያ ባህሮችና የፋኖ ማደጊያ መስኮች ናቸው፡፡

በዋንሽንት ቀዳዳዎች የሚንቆረቆሩት ሽለላ፣ ፊከራና ባህላዊ ዘፈኖች የጀግናን አካል እንደ ብረት የሚያጠነክሩ፣ የአርበኛን ወኔ እንደ እሳተ ገሞራ የሚያስገነፍሉና ፋኖን  ተአንበሳና ተነብር ጋር የሚያሳድሩ በጠቢባን የተረቀቁ ብርቱ መንፈሳዊ ሀይሎች ናቸው፡፡

 

ወጣት ሆይ!

እነዚህን ረቂቅ መንፈሳዊ ሀይሎች ተባህልህ እንዲጠፉ ተውጪ ቅድመ አያቶችህ እየቀለጠሙ የመልሷቸው ተስፋፊዎች፣ ተውስጥ እነሱ የመለመሏቸው ባንዳዎች ያልሸረቡት ሴራ የለም፡፡ አብዛኛው ዓለም እንደ አራዊት በሚኖርበት ዘመን ጠቢባን ቅደመ አያቶችህ የጠበቧቸውን ጥበቦች በኃላ ቀር ባህልነት እየፈረጁ ለመቅበር ያልቆፈሩት የሸር ጉድጓድ የለም፡፡ ይህ አድግ የተባለው የባንዳ ጥርቅም እነዚህን ረቂቅ መንፈሳዊ እሴቶች በመጤ የባህል አረም አስወርሮ አማራን በጀግናና በአርበኛ ድርቅ ለማስመታት ያልቀላወጠበት መንገድ የለም፡፡

 

ወጣት ሆይ አጢን! የቱርክን እብሪት ያንበረከኩት ቀረርቶና ሽለላ ናቸው፡፡ የግብጥን እብጠት ሲያስተነፍሱት የኖሩ ባህላዊ ሰምና ወርቅ ዘፈኖች ናቸው፡፡ የጣሊያንን ታንክ፣ መርዝና እሮቢላ አፈር ድሜ ያስጋጡት ሽለላና ፉከራ ናቸው፡፡ የሽለላ፣ ፉከራና ባህላዊ ዘፈኖች ባይኖሩ ሥምህ ሮማኖ፤ የምትጽፍበት ፊደልም ላቲን ሆኖ ያርፈው ነበር፡፡ ስለዚህ ባንዳዎች እንደሚሉት ፉከራ ጉራ ሳይሆን ነፃነት ነው፡፡ ሰምና ወረቅ ዘፈን ኃላ ቀር ባህል ሳይሆን ጥበብ፤ ክበርና ፀጋ ነው፡፡ ሽለላ ያልሰለጠነ ሕዝብ ወግ ሳይሆን እጅግ የረቀቀና የሰለጠነ ነፃ ሕዝብ ባህሪ ነው፡፡ ሽለላና ፉከራ ወኔ ነው፡፡ ወኔም የነፃነትና የክብር ባህር ነው፡፡ ስለዚህ ይኸንን ባህልህን ሲያጣጥሉብህ የወኔና የጀግንነት ባህሪህን ማድረቃቸው ነው፡፡ ባህላዊ ዘፈንህን በቅናት ጦዘው ሲያናንቁት ጥበብህን፣ ክብርህንና ፀጋህን እንድትጥል ተፅእኖ ማሳደራቸው ነው፡፡ ሽለላና ፉከራህን ሲነፍጉህ ወኔህን፣ ክብርህንና ነፃነትህን መንጠቃቸው ነው፡፡

ወጣት ሆይ! እንደምታውቀው ሃይማኖትህ ዓለም በቅዱሳን የምትመራ የፍትህ ምድር እንድትሆን ያዝዛል፡፡ ዳሩ ግን የትናንትናዋም ሆነ የዛሬዋ ዓለም ለጉልበተኞች እንጅ ለቅዱሳን ተመችታ እንደማታውቅ ታሪክ ይመሰክራል፡፡ ድርሳናትም ዓለም የጉልበተኞች እንጅ የቅዱሳን ሐብት የሆነችበት ዘመን እንዳልነበረ አስረድተዋል፡፡ ጉልበተኞች ጉልበትን በጠመንጃ፣ በስብከትና በገንዘብ እንደ ጆፌ መጭልፈው ዓለምን እንደ ኳስ እያነጠሩ ሲያሽከረክሯት ኖረዋል፡፡ ዓለም እስከ ዳግም ምጣትም ተጉልበተኞች መዳፍ መውጣቷ ያጠራጥራል፡፡ ይህ እውነታ ጉልበት ለህልውና ያለውን ወሳኝ ሚና ያመለክታል፡፡ ጉልበት ለህልውና ያለው ወሳኝ ሚና በዳርዊን ምርምር ተረጋግጧል፡፡ ዳርዊን “ሰው በአዝጋሚ ለውጥ ተፈጠረ” ያለው ስብከት ውሀ ባይቋጥርም “ጉልበታም ደካማውን አጥፍቶ ዓለምን ይቆጣጠራል!” የሚለው ክርክሩ ትክክል እንደነበር ያለም ታሪክ ይመሰክራል፡፡

 

ወጣት ሆይ! ጉልበት ሲኖርህ ጀሮውን ከፍቶ የሚሰማህ ታገኛለህ! ጉልበት ሲኖርህ በድርድር ታሸንፋለህ! ጉልበት ሲኖርህ በጦር ውሎ ታሸንፋለህ! ጉልበት ሲኖርህ ህልውናህን ታረጋግጣለህ! ጉልበት ሲኖርህ እየመረጡ የሚያሳድዱህን ባለ ሁለት እግር አውሬዎች ታንበረክካለህ! ጉልበት ሲኖርህ የውጪ ሀይሎችን ዝምድናና ወዳጅነትም ታተርፋለህ፡፡ ጉልበት ሲኖርህ በዚች ከንቱ ዓለም የሚገባህን አግኝተህ ትኖራለህ፡፡ ጉልበት ከሌለህ ደግሞ ትጠፋለህ!

 

ጉልበት ለህልውና የሚጫወተውን ወሳኝ ሚና አያቶችህ ተረድተውት እንደነበር የፈጠሩት የባህል ዘፈን፣ ሽለላና ፊከራ ይመሰክራል፡፡ አያቶችህ በአጥንታቸው ካስማነትና በደማቸው ምርግነት ገንብተው በጠበቋት አገር እንደ ጠላት የምትገደለው፣ የምትፈናቀለውና የምትሰደደው ያሁኑ አማራም እንደ አያቶችህ ከአውሬዎች ራስህን ተከላክለህ ትውልድን ለማስቀጠል የጉልበትን ጠቀሜታ መገንዘብ ይኖርብሃል፡፡ በጉልበት ለመጠንከርም የባህላዊ ዘፈንን፣ የሽለላንና የፊከራን አስፈላጊነት ማጤን ግድ ይልሃል፡፡ እግዚአብሔር ሰውን በመልኩ ፈጠረው” ከሚለው የድስት ሺህ ዘመን እምነትህ በተጨማሪ በዚች ከንቱ ዓለም ለህልውና ጉልበት አስፈላጊ መሆኑን መረዳት ይኖርብሃል፡፡ እግዚአብሔር “ቀኝህን ሲመታህ ግራህን ስጥ”ን ያዘዘው አምላክ በመልኩ የፈጠረው ሰው ሲመታህ እንጅ ሰይጣን ተእግዚአብሔር ፈልቅቆ በተንኮልና በጭካኔ ያደቆነው አውሬ ሲነክስህ አለመሆኑን ማወቅ ይኖርብሃል፡፡

 

ሰይጣን ተእግዚአብሔር ጉያ ነጥቆ ያደቆነው ወራሪ ቀኛቸውን ሲመታቸው ግራቸውን በመስጠት ፋንታ አያቶችህ ወራሪውን እንደ አውሬ በመቁጠር እንደ አንበሳ አግስተው ከአናቱ ተጎምረው እስተንፋሱን እየዘጉ ዘርረውታል፡፡ እንደ አያቶችህ ተአውሬዎች ራስህን ተከላክለህ በክብር ለመኖር ያያቶችህን ፈለግ መከተል ይኖርብሃል፡፡ ሁለት እጅ፣ ሁለት እግር፣ ሰላሳ ሁለት ጥርስና እሚናገር ምላስ ያለውን ሁሉ እግዚአብሔር በመልኩ እንደፈጠረው ሰው በመቁጠር “ለኢትዮጵያ ህልውና ስል ቀኝ ፊቴን ሲመቱኝ ግራ ፊቴን ሰጠሁ” የሚል በምድር የመኖር መብትህን የሚነሳ በሰማይም ከገነት የሚያርቅህን ጅል ዐመል ማቆም ይኖርብሃል፡፡ ለግማሽ ክፍለ ዘመን የዘር መጥረግ ወንጀል እየተፈጠመብህና በእየ አስር አምቱ በሁለት ሚሊዮን እየጎደልክ ህልውናህ እንዳያከትም ያያቶችህን ፈለግ መከተል ይኖርብሃል፡፡ ያያቶችህን ፈለግ መከተል እንድትችልም ወደ ባህልህ መመለስ ግድ ይልሃል፡፡

ከባህሉ ያፈነገጠ ማህበረሰብ ከባህሩ እንደሸሸ አሳ በህልውናው አደጋ ይጋረጥበታል፡፡ አማራ በጀግና አፍላቂ ባህሩ በሚዋኝበት ዘመን ከዱር አራዊት አንበሳና ነብርን፤ ከሰው አራዊትም ቅኝ-ገዥዎችንና ተስፋፊዎችን አንድ ለአምስት የሚገጥሙ ጀግኖችን እንደ ብርቱካን እያንዠረገገ ሲያፈራ ኖሯል፡፡ ከባህሩ ባፈነገጠባቸው ግማሽ ክፍለ ዘመናት ወዲህ ግን በክብሩ ብቻ ሳይሆን በህልውናውም አደጋ ተጋርጦበት ይገኛል፡፡

 

ወጣት ሆይ! ስንዴ ጉዛም እስተ ሆድ ዕቃው በርቅሶ ታረሰው ለም መሬት ተዘርቶና ታርሞ እንደሚያፈራው ጀግናም በጀግንነት መንፈስና ወኔ ከለማ የባህል ማሳ ሲተከልና ሲኮተኮት ፍሬው ይጎመራል፡፡ ጠላትን እንደ ፍልጥ ተርክከውና እንደ ማገዶ አንድደው ድል ስልነሱ የምትዘፍንላቸውና የምትኮራባቸው አርበኞችህ በተፈጥሯቸው ሰዎች ነበሩ፡፡ እነዚህን ሰዎች ከአላህ በቀር ማንንም የማይፈሩ ጀግኖች ያደረጋቸው ሲወለዱ የተነቀሩበት በጀግንነት ባህል የታሸ ቅቤ ሲያድጉም የበሉት በጀግንነት መንፈስ የተቦካ የባህል እንጀራ ነበር፡፡

 

በጀግንነት ባህል የተቦካ እንጀራን ጀግና አፍሪነት የተገነዘቡ ምዕራባውያን ከአምስቱ ዘመን ዳግም ሽንፈታቸው በኋላ ባህልህን በተለያዬ መንገድ ማጥቃት ጀመሩ፡፡ ብፁእ ቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ እንዳሉት ያገራቸው ባህልና ታሪክ ያልተቀዳበትን የጭንቅላት ቶፋ ይዘው ወደ ምዕራብ የተላኩትን ድስኩራም ተማሪዎች በምዕራባውያን ርዕዮተ ዓለም እያጠመቁ የራሳቸውን ባህል እንደ አተላ እንዲደፉት አደረጉ፡  እነዚህ የራሳቸውን ባህል እንደ አተላ የደፉ “ስልጡን” ተማሪዎችም ጠጉራቸውን እንደ ጫጉላ ሙሽራ እየከፈከፉ በባህላቸውና በሃይማኖታቸው ዘመቱ፡፡ ጀግና እንደ ደን የሚያፋፉ ቀረርቶዎችና ፉከራዎችን እንደ አልሰለጠነ ባህል ቆጥረው “ዘመናዊ” በሚሉት የምዕራባውያን ዳንስ እንደ ጋማ ከብት መራገጥ ጀመሩ፤ እርግጫቸውን ለሌሎችም አስተማሩ፡፡ ፉከራና ሽለላን እየተመለከቱ እንደ አባቶቻቸው ነፃ ሕዝብ መሆነ ትተው በውጪ ሲኒማ ፈዘው የእጅ አዙር ቅኝ ተገዥ ሆነው አረፉ፡፡

እነዚህ የዳንስ እርግጫና ሲኒማ ወረርሽኝ ተጠቂዎች ቅረርቶንና ፉከራን በዳንስ ኮቴ ስብርብር ከማድረግም አልፈው የቅኔን ፍልስፍና ማስተማሪያ የሆኑትን የባህል ዘፈኖች እያጠፉ የምዕራባውያንን ሙዚቃና ሲኒማ አስፋፉ፡፡ በእነዚህ ወራሪ ሙዚቃዎችና ሲኒማዎች ወጣቱን እያነፈዙ ለአገሩ ባህል ባይተዋር አደረጉ፡  በዚህም ምክንያት የቆንጆ ወንድ መለኪያው ጀግንነት መሆኑ ቀረና ሱሪን ከጪን ታጥቆ መዥገር እንደ ሸበባት ግታም ላም እየተውለደለዱ መራመድ ሆነና አረፈው፡፡

 

ይህ ጀግና አምራች ባህል ከአምስቱ ዘመን ድል ማግስት ጀምሮ በምዕራባውያን የባህል ጎርፍ እንደ ዓባይ ሸለቆ ዳገት መሸርሸር ቢጀምርም ጭራሹን የተጠረገው አማራን በጠላትነት የፈረጀ የወንበዴዎች አገዛዝ ከመጣበት ሶስት አስርተ ዓመታት ወዲህ ነው፡  ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ቀረርቶና ፉከራ በሬዲዮና በቴሌቪዥን ብቻ ሳይሆን በሰፈርና በመንደርም እንዳይሸለል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ተከለከለ፡፡ በዚህ ክልከላ ምክንያትም ይህ ጀግናን እንደ አሳ ገንዳ የሚያራባው ባህር እንደ ጣና በእምቦጭ ተመጦ እንዲደርቅ ትልቅ ሴራ ተሸረበ፡፡ በዚህ ሴራም አዲሱ ትውልድ በቀረርቶና በፉከራ አይምሮንን በጀግነት እንዳያንፅ በምዕራባውያን አጉል ሱስ ተጠምዶ በባህል ሸቀን እንዲቆሽሽ ተደረገ፡፡

 

ወጣቱ እንደ አያቶቹ በጀግንነት እንዲታነፅ ይህ የባህል ቆሻሻ በሕዝባዊ ዘመቻ መጠረግ ይኖርበታል፡  የባህል ቆሻሻው በበረኪና ታጥቦ ወጣቱ በራሱ የባህል ባህር መዋኘት ሲጀምር እንደ አያቶቹ እንኳን ራሱን ሌሎችንም በጎርፍ ከመጠረግ ያድናል፡፡ ከሸረኞች ደባ የፀዳ ባህል እንደ አያቶችህ ቆራጥ፣ ታማኝና ሩህሩህ ጀግኖችን ያፈራል፡፡ ባህልህ ከቆሻሻ ሲፀዳ በእግዚአብሔር ሚዛን የሚፈርዱ ሽማግሌዎችና ዳኞችን ይፈጥራል፡፡ ከተንኮለኞች ሸቀን የፀዳ ባህል ሲኖርህ እንደ ጥንቱ ለቆባቸው የሚያድሩ ሼሆችና መነኩሴዎች ይኖሩሃል፡፡ ከባህል እድፍ የፀዳ ባህል ሲኖር የሰው የማይነካ የራሱንም የማይሰጥ ኩሩና ሙሉ ትውልድ ይገነባል፡፡

 

ወጣት ሆይ! ስለዚህ ለህልውናህም ሆነ ለክብርህ ወደ ባህልህ መመለስ ይኖርብሃል፡፡ ሱሪህን ከጪንህ ከፍ አድርገህ ከወገብህ በቀበቶ ማጥበቅ ይጠበቅብሃል፡  በባዕዳን ዳንስ እንደ ማይክል ጃክሰን እንደ ጥንዚዛ መፈናጠሩን ትተህ እንደ ሞላ ሰጥአርጌ በሽለላና በፉከራ መንጎራደድ ይኖርብሃል፡፡

 

ወጣት ሆይ! ወደ ባህልህ ተመልሰህ የቅድመ አያቶችህን ዱካ ስትከተል የማትወጣው ተራራና የማትሻገረው ባህር አይኖርም፡  ከፊትህ የተገተረው ተራራ ከኦቶማን ኢምፓየዬር ወይም ከአውሮጳውያን ቅኝ ገዥዎች አጠገብ የሚደርስ አይደለም፡፡ በባህልህ ዳግም ታንፀህ ይኸንን ዳገት ሜዳ ማድረግ አቅቶህ ሕዝብህንም ሆነ ቅርሶችህን ማስፈጀት አይኖርብህም፡፡

 

ዓለም በሚያንቀላፋበት ዘመን ቅደመ-አያቶችህ የጠበቡትን ላሊበላን ማደስ አቅቶህ እንደ አይምሮ በሽተኛ ፈረንሳይን እየለመንክ ክብርህን እንደ ድሪቶ መጣል የለብህም፡፡ እሳት ማጥፋት አቅቶህ በአያቶችህ እርዳታ ትናንት ነፃ የወጡትን ደቡብ አፍሪካውያን እጅና እግሩን እንዳጣ “በእይነተ-ስመዓለማርያም” እያልክ የዓለም መሳቂያ መሆን አይኖርብህም፡፡ የሙሴ ጽላት ለስምንት መቶ ዓመታት የተጠለለበት፣ የብዙ የሃይማኖትና ፍልስፍና መዛግብት የሚገኙበትና የእልፍ አእላፍ ፍጥረታት መኖሪያ የሆነው ጣና ሲደርቅ እንደ ባዕድ ቆመህ ማየት የለብህም፡፡

 

ከአያቶችህ ባህል በማፈንገጥህ የምዕራባቡም የምስራቁም ሎሌ በሆኑ ለማኝ ገዥዎች ሥር ስትማቅቅ መኖር የለብህም፡፡ የወኔና የጀግንነት የባህል ባህርህን አድርቀው ሊያጠፉህ የሚሹ ጭራቆች እንዳሉ ለሰከንድም መርሳት የለብህም፡፡

 

አንዳንድ ባህላቸውና ማንነታቸው ሸጠው የዘቀጡ አህያውን ቢፈራ ዳውላውን አይነት ምሁር ተብዮዎች ተጭራቅ ወሮበላ ገዥዎች ጋር በጓዳ በር እየሰሩ “ወደ ሁላ ያስቀረን ባህላችን ነው” እያሉ እንደ በፊቱ ድፍን አፍሪካ፣ ኤሽያና ደቡብ አሜሪካ ባርያ ሊያደርጉህ ሲዳዱ ይስተዋላሉ፡፡ ተጭራቅ ገዥዎች በተጨማሪ አገሪቱን ወደ ሁዋላ ያስቀሩ እነዚህ የራሳቸውን ባህልና ሃይማኖት አሽቀንጥረው ጥለው የምእራቡንም የምስራቁንም እድፍ በጭንቅላታቸው የተሸከሙ ምሁር ተብዮዎች እንደሆኑ ይክዳሉ፡፡ ወጣት ሆይ! ለእንደዚህ ዓይነት ራሳቸውን የሸጡ ድስኩራም ከሀዲ ምሁራን ጆሮህ ጥጥ ነው፡፡ አትስረቅ፣ አትዝረፍ፣ አታታል፣ አታወናብድ፣ ሰውን በዘሩ አትለይ፣ እሬሳ አትጎትት፣ ሳይነኩህ አትንካ፣ ጥቃትን አትታገስ፣ ከመለኮት በቀር ለማንም ላለመገዛት ሸልልና ፎክር የሚል ባህል ወደር የሌለውና የተቀደሰ ባህል መሆኑን የምታውቀው ነው፡፡ ስለዚህ ከመለኮት ውጪ ለማንም ላለመገዛት እንደ እንደ ቀደምቱም ሆነ እንደ አድዋና አምስቱ ዘመን አርበኛ ፋኖዎች ዝንተ ዓለም ሸልል! ፎክር!

 

ከአያቶችህ ባህል በማፈንገጥህ የምዕራባቡም የምስራቁም ሎሌ በሆኑ ለማኝ ገዥዎች ሥር ስትማቅቅ መኖር የለብህም፡  የወኔና የጀግንነት የባህል ባህርህን አድርቀው ሊያጠፉህ የሚሹ ጭራቆች እንዳሉ ለሰከንድም መርሳት የለብህም፡፡ ወጣት ሆይ! ህልውናህም ሆነ ክብርህ የሚቀዳው አያቶችህ ከጠበቡት የባህል ባህርህ!

 

ወጣት ሆይ! ከመለኮት ውጪ ለማንም ላለመገዛት እንደ እንደ ቀደምቱም ሆነ እንደ አድዋና አምስቱ ዘመን አርበኛ ፋኖዎች ዝንተ ዓለም ሸልል! ፎክር!

 

የካቲት ሁለት ሺ አስራ ስድስት  ዓ.ም.

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/188893
የተመድ የሰብዓዊ መብት ም/ቤት በአማራ ጉዳይ | “ተፀፅችያለሁ ይቅርታ ለመጠየቅ እፈልጋለሁ” አብይ | የመራዊ ፖሊስ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋየ
https://youtu.be/3uTW3AHFZ14?si=qp4gwqmZMABeuU-A

 

https://youtu.be/NAMX3BEGyiI?si=0uYIGLkQZT7zRuNd

 

 የመራዊ ፖሊስ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋየ

 

https://youtu.be/iPQMD8MT-q0?si=7T-Hd8jIO14WNbF5
https://amharic.zehabesha.com/archives/188884

Wednesday, February 21, 2024

“ተፀፅችያለሁ ይቅርታ ለመጠየቅ እፈልጋለሁ” አብይ | የመራዊ ፖሊስ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋየ
https://youtu.be/NAMX3BEGyiI?si=0uYIGLkQZT7zRuNd

 

 የመራዊ ፖሊስ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋየ

 

https://youtu.be/iPQMD8MT-q0?si=7T-Hd8jIO14WNbF5
https://amharic.zehabesha.com/archives/188884
“ተፀፅችያለሁ ይቅርታ ለመጠየቅ እፈልጋለሁ” አብይ | የመራዊ ፖሊስ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋየ
https://youtu.be/NAMX3BEGyiI?si=0uYIGLkQZT7zRuNd

 

 የመራዊ ፖሊስ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋየ

 

https://youtu.be/iPQMD8MT-q0?si=7T-Hd8jIO14WNbF5
https://amharic.zehabesha.com/archives/188884

Tuesday, February 20, 2024

ኮለኔል መሀመድ አህመድ የመራዊን ጭፍጨፋ ከመሩት የብልጽግና መኮነኖች አንዱ ነበር። የአማራ ህዝባዊ ሃይል የጣናው መብረቅ ብርጌድ በወሰደው የአፃፋ እርምጃ ኮለኔሉ መደምሰሱን አስታውቆ ነበር። ዛሬ ቀብሩ በትውልድ አካባቢው ተፈፅሟል።
ኮለኔል መሀመድ አህመድ የመራዊን ጭፍጨፋ ከመሩት የብልጽግና መኮነኖች አንዱ ነበር። የአማራ ህዝባዊ ሃይል የጣናው መብረቅ ብርጌድ በወሰደው የአፃፋ እርምጃ ኮለኔሉ መደምሰሱን አስታውቆ ነበር። ዛሬ ቀብሩ በትውልድ አካባቢው ተፈፅሟል። pic.twitter.com/Nung43HHpt— мιѕgαиαω zє gнισи (@Misganaw_92) February 19, 2024

ኮለኔል መሀመድ አህመድ የመራዊን ጭፍጨፋ ከመሩት የብልጽግና መኮነኖች አንዱ ነበር። የአማራ ህዝባዊ ሃይል የጣናው መብረቅ ብርጌድ በወሰደው የአፃፋ እርምጃ ኮለኔሉ መደምሰሱን አስታውቆ ነበር። ዛሬ ቀብሩ በትውልድ አካባቢው ተፈፅሟል።
https://amharic.zehabesha.com/archives/188874
ኮለኔል መሀመድ አህመድ የመራዊን ጭፍጨፋ ከመሩት የብልጽግና መኮነኖች አንዱ ነበር። የአማራ ህዝባዊ ሃይል የጣናው መብረቅ ብርጌድ በወሰደው የአፃፋ እርምጃ ኮለኔሉ መደምሰሱን አስታውቆ ነበር። ዛሬ ቀብሩ በትውልድ አካባቢው ተፈፅሟል።
ኮለኔል መሀመድ አህመድ የመራዊን ጭፍጨፋ ከመሩት የብልጽግና መኮነኖች አንዱ ነበር። የአማራ ህዝባዊ ሃይል የጣናው መብረቅ ብርጌድ በወሰደው የአፃፋ እርምጃ ኮለኔሉ መደምሰሱን አስታውቆ ነበር። ዛሬ ቀብሩ በትውልድ አካባቢው ተፈፅሟል። pic.twitter.com/Nung43HHpt— мιѕgαиαω zє gнισи (@Misganaw_92) February 19, 2024

ኮለኔል መሀመድ አህመድ የመራዊን ጭፍጨፋ ከመሩት የብልጽግና መኮነኖች አንዱ ነበር። የአማራ ህዝባዊ ሃይል የጣናው መብረቅ ብርጌድ በወሰደው የአፃፋ እርምጃ ኮለኔሉ መደምሰሱን አስታውቆ ነበር። ዛሬ ቀብሩ በትውልድ አካባቢው ተፈፅሟል።
https://amharic.zehabesha.com/archives/188874

Monday, February 19, 2024

በእጅጉ ከቆሸሸ ሥርዓት የቆሻሻ ዑደት እና ውጤት እንጅ የተለየ ነገር አይጠበቅም!!!
February 18, 2024

ጠገናው ጎሹ

ከቆሸሸ ግብአት የቆሸሸ ውጤት (GARBAGE IN, GARBAGE OUT) እንጅ የተለየ ውጤት መጠበቅ ፈፅሞ አይቻልም።

ይበልጥ አስከፊ በሆነ መልኩ ፈፅሞ ሊፀዳ በማይችል መርዘኛ የፖለቲካ ቆሻሻ /ወንጀል ከበበሰበሰና ከከረፋ የፖለቲካ ሥርዓተ ዑደትም ይበልጥ አደገኛ የሆነ መርዘኛ ቆሻሻን እንጅ ሌላ የተለየ ውጤትን መጠበቅ ፈፅሞ አይቻልም ።

ለዚህ ደግሞ በእኩያን የህወሃት የፖለቲካ ኢሊቶች የበላይ ዘዋሪነት (ተቆጣጣሪነት) እና ከአምስት ዓመታት በፊት ጀምሮ በተረኝነት ሥልጣነ መንበር ላይ ተሰይመው የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካውን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ አስከፊና አስፈሪ ሁኔታ እያስኬዱት ባሉት ገዥ ቡድኖች አሽከርነት (መሣሪያነት) ተፈፃሚ የሆነውና እየሆነ ያለው ህገ መንግሥት (ህገ ጥላቻ፣ ህገ መለያየት ፣ ህገ ጭቆና ፣ ህገ ዝርፊያ ፣ ህገ ሰቆቃ፣ ህገ መከራ፣ ህገ ውርደት፣ ህገ ገዳይ/ አስገዳይ/አገዳዳይ፣ ህገ ምድረ ሲኦል፣ ወዘተ) በመሣሪያነት እየተጠቀሰ ካደረሰውና እያደረሰ ካለው ሁለንተናዊ አገራዊ ሰቆቃ በላይ ግዙፍና መሪር ማስረጃ የለም ፤ አይኖርምም። ለእንዲህ አይነት ምንነት፣ ማንነት፣ እንዴትነት እና ከየት ወደ የትነት የዳረገንን የገዛ ራሳችን ግዙፍና መሪር እውነት በመጋፈጥ ትውልዳዊ የሆነ መሠረታዊ ዴሞክራሲያው ለውጥን እውን ከማድረግ ይልቅ ሰንካላ የሰበብ ድሪቶ መደረቱ ስለሚቀናን መቀበል እያቃተን ነው እንጅ በፖለቲካ ታሪካችን ሂደት እንዲህ አይነት በመርዛማ ቆሻሻ ዑደትና ውጤት የተበከልንበት ፈተና አጋጥሞን አያውቅም።

ይህንን አስተያየቴን የተጋነነ ወይም ለገዥ ቡድኖች ከሚኖር ጭፍን ጥላቻ እንደሆነ አድርገው ለማየትና ለማሳየት የሚሞክሩ ወገኖች እንደሚኖሩ በሚገባ እገነዘባለሁ። እንዲህ አይነቱ አስተሳሰብ የሚመነጨው ግን መሬት ላይ ያለውን ግዙፍና መሪር እውነታ ተረድተው የሚጠበቅባቸውን ድርሻ ለመወጣት ጥረት ከሚያደርጉ ወገኖች ሳይሆን አንድም ቀጥተኛ ከሥርዓቱ ተጠቃሚዎች ወይም በንፁሃን ደምና መከራ ከሚነግዱ ግለሰቦችና ቡድኖች ወይም  የሥርዓቱ ፍርፋሪ ለቃሚዎች ከሆኑ የአድርባይነት ልክፍተኞች ወይንም ደግሞ ከእኩያን ገዥዎች የሚመነጨውን መከራና ውርደት እንደ እጣ ፈንታ እንድንቆጥር ካደረገን ሥር የሰደደ ድንቁርና እንደሚሆን ለማወቅ የተለየ እውቀትን አይጠይቅምና ቢያሳዝነኝም አይገርመኝም።

በተለይም የለየላቸው የሥርዓቱ ባለሥልጣናትና ካድሬዎች ፈጣሪ ራሱ ተገልጦ “በአምሳሌ በፈጠርኩት ህዝበ አዳምና ሄዋን ላይ ግዙፍና እጅግ አስከፊ የመከራ ዶፍ እያወረዳችሁ ስለ የትኛው ሰላምና ብልፅግና ነው የምተርኩት ወይም የምትሰብኩት ወይም የድል አድራጊነት ዲስኩር የምትደሰኩሩት”? ብሎ ቢጠይቃቸው “ይህ በእግዜር አምሳል የተገለጠ ሰይጣን እንጅ እግዜር ራሱ አይደለም” እስከ ማለት የሚደርሱ እጅግ ባለጌዎች፣ ደንቆሮዎች ፣ ሴረኞች፣ ሸፍጠኞችና ጨካኞች መሆናቸውንን መሬት ላይ ተዘርግቶ የሚነበበው ድርጊታቸው ስለሚናገር ብዙ ማለት የሚያስፈልገኝ አይመስለኝም።

እንዲህ አይነቱን እጅግ አስከፊና ዘመን ጠገብ አዙሪት ሰብሮ ለመውጣት ከምር የምንፈልግ ከሆነ መሠረታዊ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ለውጥን በብሩህ ራዕይ ፣ በፅዕኑ የመርህ፣ የዓላማና የግብ መሠረት ላይ ተመሥርቶ እውን ከማድረግ ይልቅ እገሌ የሚባለው/ዋ ካድሬ ወይም አድርባይ ተሽሮ/ራ እገሌ የሚባል/ትባል ተሾመ/ች ወይም  በሽግሽግ ወደ ሌላ ሥልጣን ተዛወረ/ች ወይም “በክብር” ተሰናበተ/ች ወይም የተቃውሞ ዲስኩር ደስኩሮ/ራ ተሰደደ/ች ወይም በካድሬነቱ/ቷ ወቅት ንፁሃንን ሲያሳስርበት /ስታሳስርበት ወደ ነበረው ከርቸሌተወረወረ/ች ፣ ወዘተ የሚለውን የመርዘኛ ቆሻሻ ዑደት (garbage in, garbage out) ከማመንዠክ ክፉ ልማድ አሁንኑ ሰብረን በመውጣት ለዜጎች ሁሉ የምትመች አገርን እውን ማድረግን ግድ ይለናል። ዘመናትን ያስቆጠረው የሸፍጥ፣ የሴራ እና የጭካኔ ፖለቲካ ባህሪያቸውና ተግባራቸው ግልፅና ግልፅ የሆነውን የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማርተኞች የቆሻሻ ግባ እና የቆሻሻ ውጣ (garbage in, garbage out) የፖለቲካ ጨዋታ እንደ ሰላማዊ የሥልጣን መተካካት ፣ እንደ ጤናማ የሥልጣን ሽግሽግ እና በአጠቃላይ እንደ አወንታዊ የለውጥ ሂደት እየቆጠርን ራሳችንን ከደመ ነፍስ እንስሳት በማይሻል ሁኔታ ውስጥ የማግኘታችንን መሪር እውነታ በቅጡ (ከምር) ካልተረዳነውና ካልተፀየፍነው የመረረ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎ ለማካሄድና የምንመኘውን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ለማድረግ ፈፅሞ አይቻለንም።

የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን የሞራልና የሥነ ምግባር ሰብዕና ቀውስ የተጠናወተው የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየ አብይ አህመድ ከዛሬ ስድስት ዓመታት በፊት የህወሃቱን መለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ ተላብሶ (የራሱን የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን የሞራል ሰብዕና ለሟች አለቃው በቀፎነት አሳልፎ ሰጥቶ) በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣነ መንበር ላይ የቆየውን ሃይለማርያም ደሳለኝን  ሲተካው እና ታሪካዊ የሆነ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር (መተካካት) በሚል በመከረኛው ህዝብ ላይ ሲሳለቁበት ከምር በመቆጨት፣ በመፀፀትና በመቆጣት እምቢ ለመሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለውጥ ብሎ ለመነሳትና ለማነሳሳት ያለመቻላችን አስከፊና አሳፋሪ ውድቀት ያስከተለብንና እያስከተለብን ያለው ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ የመከራና የውርደት ዶፍ አሁንም መሪር ተሞክሮ ካልሆነን ምን አይነት መከራና ውርደት ትምህርት ሆኖ ሊያነሳሳን እንደሚችል ከባድ እእቆቅልሽ ነው።

በዚህ ረገድ ቀዳሚው ከፈተና ወዳቂ በአብዛኛው ተማርኩ ብቻ ሳይሆን “ሊቅነት ከእኔ ወዲያ ላሳር ነው” በሚል የሚኮፈሰው የህብረተሰብ ክፍል ነበር። አሁንም ነው። ዘመን ጠገብ የሆነውንና በእጅጉ የተበላሸውን የአገሩን ፖለቲካ በመስማት ሳይሆን በመኖር የሚያውቀው ይህ የህብረተሰብ ክፍል መከረኛው ህዝብ የሸፍጠኞችንና የሴረኞችን "የተሃድሶ ገድል" አክሽፎ የእውነተኛ ለውጥ ባለቤት ይሆን ዘንድ ማነሳሳቱ (እምቢ ለቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ ፖለቲካ  ጨዋታ እንዲል) ማስቻሉ ቢቀር እንኳ ለምን? እንዴት? እና ከየት ወደ የት? የሚሉ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ጊዜ ሳይወስድ የአዙሪቱ ሰለባ የሆነ እለት ነበር የመከራውና የውርደቱ ፖለቲካ በአስከፊ ሁኔታ ሊቀጥል እንደሚችል ግልፅና ግልፅ የሆነው።

ካለፈ ስህተትና ውድቀት ተምረን የተሻለ ዛሬንና በጣም የሚሻል ነገን እውን ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ ላይ ብንሆንና ይህንን ግዙፍና መሪር የሆነ የውድቀት ድግግሞሽ በዚህ አይነት የምሬት ስሜት ባልገልፀው ደስ ባለኝ ነበር።

አሁንም ወርቃማ የሆነውን የህልውና ማስከበር እና የመሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለውጥን በቆሻሻ ግባ እና በቆሻ ውጣ (garbage in, garbage out)  የፖለቲካ ሥርዓት መቃብር ላይ ስለ መመሥረትና ስለ መገንባት ሳይሆን ከቆሻሻ  የፖለቲካ ዑደት አንዳች መልካም ነገር (ወጤት) ከመጠበቅ ክፉ አባዜ አልተላቀቅንምና ወደድንም ጠላንም የውድቀታችን እንቆቅልሽ እስኪፈታ ድረስ በግልፅና በቀጥታ መነጋገራችን የግድ ነው።

"በሙሲያዊው አብይ አህመድ" መሪነትና በካምፓኒው (በኦህዴድ/ኦነግ ብልፅግና) መዋቅራዊ አስፈፃሚነት የተካሄደውና እየተካሄደ ያለው ፖለቲካ ወለድ ወንጀል በመርዘኛ የሥልጣን መተካካት ቆሻሻ የጨቀየ መሆኑን ግልፅ ካላደረገልን እውነትም አቻ የማይገኝለት ድንቁርና ፣ የትኛውንም ምድራዊ መከራና ውርደት የመለማመድ አስከፊ ልክፍት ፣ ጨርሶ አቻ የማይገኝለት የአድርባይነት ደዌ ፣ ወደ ተግባር ሊተረጎም የማይችል ተስፈኝነት ፣ ወዘተ አባዜ  በእጅጉ ተጠናውቶናልና ከምር ሊያሳስበን ይገባል።

የተፈጠርንበትን በነፃነት ጥሮና ግሮ የመኖር ዓላማ ከፈጣሪ ድጋፍ ጋር እውን እያደረግን እንደ መልካም ዜጋ እና እንደ ሰው ሰው ሆነን የምንኖርበትን ሥርዓተ ፖለቲካ አምጦ ከመውለድና ከማጎልበት ይልቅ የመርዘኛ ቆሻሻ ፖለቲካ ዑደትንና ውጤትን (መሾምና መሻርን ወይም የጉልቾች መቀያየርን /garbage in, garbage out) እንደ አበረታች (አወንታዊ) የለውጥ አካል የመቁጠራችንን እጅግ ወራዳና አዋራጅ ሁኔታ ከምር ለሚረዳ የአገሬ ሰው ምን ያህል ህሊናውን እንደሚፈታተነው ለመገመት አያስቸግርም።

እውነት ነው በሥራ ሂደት ውስጥ በአቅም ማነስ ወይንም በጊዜያዊ የፍላጎትና የጥቅም ግጭት ምክንያት የመቆሸሽ እንከን ሊያጋጥመው እንደሚችል አካል በመንበረ ሥልጣን ላይ የተቀመጡ ወይም የሚቀመጡ ፖለቲከኞችም የመቆሸሽ ፈተና ሊገጥማቸው እንደሚችል ለመረዳት አያስቸግርም።የማይጠበቅም አይደለም። የእኛ ግን ከዚህ አይነት ሊጠበቅ ከሚችል የመቆሸሽ እውነታ ፈፅሞ ሊታይና ሊነፃፀር የሚችል ጉዳይ አይደለም። ሊጠበቅ ይችላል የምንለው የመቆሸሽ ፈተና ወይም ችግር ቅንነትንና አስተዋይነትን በተላበሰ አስተሳሰብና የተግባር ውሎ መስተካከል (መፅዳት) የሚቼል ሲሆን ለሩብ ምዕተ ዓመት የዘለቀውና ከስድስት ዓመታት ወዲህ ደግሞ የመከራውንና የውርደቱን አገዛዝ እንኳን ለመገመት ለማሰብም በእጅጉ በሚዘገንን ፖለቲካ ወለድ ወንጀል እያስኬደ ያለው ብልፅግና ተብየ ግን ያለ መሠረታዊ የለውጥ ህክምና (ተጋድሎ) በፍፁም የሚስተካከል ወይም የሚፈወስ አይደለም።

እናም ለዘመናት በሥልጣነ መንበር ላይ በመፈራረቅ ወይም ቆሻሻን አስገብቶ ቆሻሻን በመተካት (garbage in, garbage out) የፖለቲካ ጨዋታ በህዝብ ላይ እጅግ አሰቃቂ የመከራና የውርደት ዶፍ ማውረድ በትክክለኛው ሃይማኖታዊም ሆነ ዓለማዊ አስተሳሰብና እምነት እንኳንስ ተቀባይነት ታጋሽነትም ፈፅሞ ሊቸረው የሚገባው ጉዳይ አይደለምና ልብ ያለው ልብ ይበል ።

ለመሆኑ፦

Ø  የአገርን ልዑላዊነት በግልፅ አሳልፎ እየሰጠ (ከሱዳን እና ከደቡብ ሱዳን ጋር በምንዋሰንባቸው አካባቢዎች የሆነውንና እየሆነ ያለውን ልብ ይሏል) የልዑላዊነት  ሥልጣን (ወደ ሥልጣን የማውጣትና ከሥልጣን የማውረድ ሃይል) አለው የሚባለውን የገዛ አገሩን  ህዝብ ለፖለቲካ መንበሩ ያሰጋል በሚል ከውጭ ጠላት በባሰ ጭፍጨፋ  ዝም ጭጭ ያስደርግለት  ዘንድ በቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ የፖለቲካ ዑደት (the political cycle of garbage in, garbage out) መርህና አሠራር መሠረት  ለሾመው  ብርሃኑ ጁላ በዓለም ወታደራዊ የሥልጣን እርከን በቀላሉ የማይገኘውን የፊልድ ማርሻልነት ማዕረግ ከማሸከም የከፋ ምን አይነት የህዝብ (የአገር) ንቀት ይኖራል? ምንስ አይነት መርዘኛ የሆነ የቆሻሻ ግባና የቆሻሻ ውጣ የፖለቲካ አዙሪት ይኖራል?

Ø  ሲሆን የፖለቲካው አውድ በየመስኩ ለሚደረጉ ሙያዊ ጥረቶችና ውጤቶች  (professional engagements and products) የሚበጅ እንዲሆን የመልካም ዜግነት ድርሻን በመወጣት ፣ ያ ካልሆነ ደግሞ በሙያቸው የሚችሉትን አስተዋፅኦ በማድረግ የሚጠበቅባቸውን ተልእኮ መወጣት የነበረባቸውንና ያለባቸውን ባለሙያዎች የመርዘኛ ቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ ፖለቲካ ጨዋታ ተዋንያን ማድረግ በእጅጉ አስከፊና አስፈሪ  የሆነ ውድቀታችንን ካልነገረን ሌላ ምን ሊነግረን የሚችል ነገር ይኖራል?

 

Ø  በዚህ ደረጃ በበከተና በከረፋ የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ የሚተካኩ ሹማምንቶችና ካድሬዎች (የቆሻሻ ግባ እና የቆሻሻ ውጣ ፖለቲካ እድምተኞች) ንፁሃን ዜጎች እንደ የውጭ ጠላት በምድር እና በአየር ላይ ጦር ለምን የጨፈጨፋሉ? ከእለት ጉርስና ከመጠለያነት የማያልፈው ንብረታቸውስ ለምን ይወድማል?  ሲባሉ “ህግ የማስከበር ጉዳይ ነው” ፣ በፖለቲካ ወለድ ወንጀል ምክንያት ሚሊዮኖች የአሰቃቂ ርሃብ ሰለባዎች ሆነዋል እኮ ሲባሉ “ገፅታችን ለማበላሸት ሲባል እየተጋነነ ነው እንጅ ከቁጥጥራችን አልወጣም/ሰው በርሃብ አልሞተም” ፣ እጅግ አያሌ ቁጥር ያላቸው ዜጎች በሚፈበረክ  የወንጀል ክስ በየማሰቃያው ማእከል እየተሰቃዩ አይደለም ወይ? ተብለው ሲጠየቁ “በፖለቲካ ምክንያት የታሰረ የለም፤ለማነኛውም በህግ እየታየ ያለ ጉዳይ ነው” ፣ አያሌ ንፁሃን በማንነታቸው ሲገደሉና ሚሊዮኖች ደግሞ እጅግ ኢሰብአዊ ለሆነ መፈናቀል ሲዳረጉ ማየት አያስጨንቅም ወይ? ሃላፊነቱስ በዋናነት የመንግሥታችሁ አይደለም ወይ? የሚል መሪር ጥያቄ ሲቀርብባቸው “በለውጥ ሂደት የሚያጋጥም እንጅ እንደሚወራው አይደለምና የሚጣራ ካለም  ይጣራል፤ ተፈናቃዮችንም ወደ አካባቢያቸው ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው” ፣ ወዘተ እያሉ በሚጣልላቸው (በሚከፈላቸው) ምንዳእ (ደመወዝና ልዩ ጥቅም) ከርሳቸውን ሞልተው  መኖራቸውን እንደ  የህይወት ስኬት የመቁጠራቸው መሪር እውነት ለማይታጠፍ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎ የማያነሳሳው ትውልድ ምን አይነት ነፃነትንና ፍትህን እንደሚናፍቅና መቸ እውን እንደሚያደርገው ለመረዳት አይከብድም እንዴ?

 

Ø  ከክልሎች ሁሉ በተለየ የአማራ ክልል እነ ገዱ አንዳርጋቸውን፣ ተመስገን ጥሩነህን፣ ይልቃል ከፍያለን፣ እና የአሁኑን አረጋ ከበደን የመርዘኛ ቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ የፖለቲካ ጨዋታ አሻንጉሊቶች (የሰው አምሳል ያላቸው እቃዎች) በማድረግ በህዝብ ላይ  የመከራና የውርደት ዶፍ ባወረደውና እያወረደ ባለው ኦህዴድ/ኦነግ መራሽ ብልፅግና ተብየ የበላይነት ሥር በሚካሄድ ንግግርና ድርድር  ከዘመን ጠገቡ ክፉ የፖለቲካ አስተሳሰብና አካሄድ ተላቀን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እናዋልዳለን ብሎ ከማሰብ የባሰ የፖለቲካ አስተሳሰብ ድንቁርና እና የሞራል ድህነት ይኖር ይሆን?

 

Ø  ዘመን ጠገብ የሆነውን የጉልቾች የመተካካት (ቆሻሻን አስገብቶ ቆሻሻ የማስወጣት) የፖለቲካ ዑደት አራጊና ፈጣሪ እኩያን ገዥ ቡድኖች ጥሩ ሲሠሩ እያመሰገንና ሲሳሳቱ እየወቀስን ካልያዝናቸው አገር ይፈርሳል የሚሉት እጅግ ደምሳሳና የወረደ የፖለቲካ ማስፈራሪያ የቦቅቧቆች ወይም በቁም እየሞቱ አለን የሚሉ ፖለቲከኞች (cowardly and dead alive politicians) ማስፈራሪያ ካልሆነ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?  የገዛ ራስን መሪር እውነት ከምር በሆነ ፀፀትና ቁጭት ተረድቶ ከዚህ አይነቱ ልክ የሌለው የመከራና የውርደት አዙሪት ሰብሮ በመውጣት ህልውና የሚረጋገጥባት እና ለዜጎቿ ሁሉ የምትመች ዴሞክራሲያዊት አገርን እውን ለማድረግ የበኩሉን ድርሻ የማይወጣ ነፃነትና ፍትህ ፈላጊ ነኝ ባይ ምን አይነት ነፃነትና ፍትህ ነው የሚፈልገው?

 

Ø  ከዛሬ ሰላሳ ዓመታት በፊት ህወሃት በአምሳሉ ጠፍጥፎ በሠራቸው አሽከሮቹ (የሚናገሩ አጋሰሶች) እየተመራ ወደ መሃል አገር ሲገሰግስ ለአሽከርነት ምልመላ ዒላማዎቹ ካደረጋቸው ተቋማት መካከል የትምህርት ተቋማት ዋነኛዎቹ ነበሩ ። የዚህ እኩይ ዒላማው ለመሆን በሙሉ ፈቃደኝነት ይጠባበቁ ከነበሩት ደናቁርትና ትውልድ ገዳይ ፊደል ቆጣሪዎች (አስተማሪዎች) መካከል ደመቀ መኮንን አንዱ ነበር። ለዚህም ነበር በቡሬ (ጎጃም) በባዮሎጅ አስተማሪነት ላይ እያለ በጉጉት ሲጠባበቅ የነበረውን የፍፁም ታማኝነት ካድሬነቱን ተልእኮ በደስታ ተቀብሎ መፈፀምና ማስፈፀም የጀመረው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ የኢህአዴግ ስምሪቶችን እየተቀበለ (የእኩይ ፖለቲካ መልእክቶችንና ዓላማዎችን የሚጫንና የሚያስተላልፍ አጋሰስ እየሆነ) ለሰላሳ ዓመታት ካገለገለ በኋላ ከሰሞኑ “በል በቃህ ጥቅማጥቅምህን ይዘህ ዘወር በል” ሲሉት ውርደቱን እንደ ክብር ቆጥሮ ፣ በአጠቃላይ በመላው ህዝብ እና በተለይ ደግሞ ተገኘሁበት በሚለው ማህበረሰብ ላይ የፈፀመውንና ያስፈፀመውን ግፍ  እንደ  መልካም ውለታ ቆጥሮ፣ አጋሰስ ካድሬነቱን (መሣሪያነቱን) ትጉህና ቅን መሪ አስመስሎ ፣ ከራሱ አልፎ የቤተሰቦቹ ማፈሪያ የመሆኑን መሪር እውነታ የኩራት ተምሳሌት አድርጎ ፣ ወዘተ ሊያሳምነን (ሊያቄለን) ሲሞክር መስማትና ማየት ቅንና ሚዛናዊ ህሊና ባለው የአገሬ ሰው ላይ የሚያሳድረውን ህመም ስንቶቻችን ነን ከምር የምንጋራው? ታዲያ መቸና እንዴት ነው ከዚህ አይነቱ የእኩያን ፖለቲከኞች የጉልቾች መተካካት (ቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ  ውጣ) አዙሪት ሰብሮ በመውጣት እውነተኛ ዴሞክራሲያዊት አገርን እውን ማድረግ የሚቻለው?

 

Ø  የደመቀ ድርብ የታማኝ ካድሬነት ሥልጣን የተቸራቸው ሁለት ግለሰቦች ናቸው። አንደኛውና በአብይ አህመድ መልካም ፈቃድ የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሹመተ ቅብአት የተቀባው በግልፅ የባለጌዎች፣ የሸፍጠኞች፣ የሴረኞች ፣ የፈሪዎችና የጨካኞች ስብስብና እጅግ አስከፊ የኢህአዴግ ውላጅ የሆነው የብልፅግና አባል የሆነው እና ሰብዕናውን ለእኩያን ገዥዎች ሶፍት ዌር ማስቀመጫነት (as a hardware) አሳልፎ የሰጠ መሆኑን ባህሪውና ድርጊቱ የሚመሰክርበት ተመስገን ጥሩነህ ነው። ለጌቶቹ፣ ለቢጤዎቹ፧ ለፍርፋሪ ለቃሚ አድርባዮች ካልሆነ በስተቀር የዚህ ሰው ምንነት፣ ማንነት ፣ ለምንነት፣ እንዴትነት፣ እና ከየት ወደ የትነት ግልፅና ግልፅ ስለሆነ ብዙ ማለት የሚያስፈልገኝ አይመስለኝም።

 

Ø  ሌላኛው ደግሞ “አባል አይደለሁም” በሚል ሽፋን በሥልጣነ መንበር ላይ ለሚፈራረቁ እኩያን ገዥ ቡድኖች ሁሉ ከለየላቸው ካድሬዎቻቸው በባሰ ሁኔታ በፍፁም ታማኝነት ለረዥም ጊዜ ያገለገለው (የራሱ የሆነና ሥር የሰደደ ወይም አብሮት ያደገና የጎለመሰ የአድርባይነት ፍልስፍና እና ባህሪ የተጠናወተው) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመተ ቅብአትን የተቀባው ታየ አፅቀ ሥላሴ ነው።  ለሦስት ዓሥርተ ዓመታትና በተለይም ከስድስት ዓመታት ወዲህ አገረ ኢትዮጵያን የንፁሃን ዜጎች (ልጆቿ) ምድረ ሲኦል ያደረጓትንና እያደረጓት ያሉትን እጅግ ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች መመሪያና ትእዛዝ እየተቀበሉ ንፁሃንን እንደ ወንጀለኛ እና  በሌላ በኩል ግን ጨካኝ የፖለቲካ ሰይፋቸውን  እንደ ህግና ሰላም አስከባሪ በማድረግ በዲፕሎማሲ ስም ርካሽና አደገኛ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ  ያካሄዱትንና አሁንም እያካሄዱ ያሉትን ወገኖች አካፋን አካፋን ለማለት በሚያስችል አቋምና ቁመና ቢያንስ ነውር ነው ማለት የግድ አይለንም ወይ?

እንደ ታየ አይነት እጅግ አሳሳችና አደገኛ ግለሰቦችን ጎምቱ ዲፕሎማት፣ በታላቁ ግድብ ጉዳይ ዙሪያ ግብፅን ያንቀጠቀጡ፣ ህወሃትና ብልፅግና ባካሄዱት ጦርነት ብልፅግናን ወክለውና ሸንጣቸውን ገትረው የተከራከሩ ፣ ለአብይ አህመድ የኖቬል እና የፋኦ ሽልማት መብቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ ፣ የአብይ አህመድን የመናፈሻ፣ የችግኝ ተከላ፣ የመንገድ ጥረጋ፣ ወዘተ ዘመቻ በዓለም አድናቆትን እንዲያተርፍ ያደረጉና እያደረጉ ያሉ በሚል መከረኛውን ህዝብ ጨምሮ የርካሽ ፕሮፓጋንዳ ሰለባ የማድረጋቸው መሪር እውነት የሚነግረን የዲፕሎማሲን እውነተኛ ምንነትና ለምንነት (የህዝብ/የብሔራዊ ጥቅም ማራመጃና ማስከበሪያነት) ለባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች ርካሽ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፃሚነት እንዲውል የማድረጋችንና በማድረግ ላይ የመሆናችንን መሪር እውነታ ነው።ታዲያ ለዚህ ሁሉ አስከፊ ሁኔታ መቀጠል ዋነኛው ምክንያት ሴረኛ፣ ሸፍጠኛና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ዘዋሪዎች (አራጊና ፈጣሪዎች) የሚያካሂዱትን የጉልቻ መቀያየር (የቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ) ፖለቲካ እንደ የተሃድሶ ለውጥ እና  የሰላማና የልማት ዋስትና እያደረጉ ሲሳለቁብን ለዚሁ በሚመጥን የጋራ ትግል አደባባይ ላይ ለመሰባሰብ አለመቻላችን ነውና አሁንም ተጨማሪ ጊዜ እና ሌላም ውድ ነገር ሳናባክን ህልውና ለሚረጋገጠባትና ነፃነትና ፍትህ (ዴሞክራሲ) ለሚሰፍንባት አገረ ኢትዮጵያ እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ በማካሄድ ላይ ከሚገኙ ወገኖች ጋር ከምርና ጨርሶ ወደ ኋላ በማይመለስ አቋምና ቁመና መተባበርን የማይቀበል ነፃነትና ፍትህ ፈላጊ ይኖርህ ይሆን?

 

Ø  እስኪ ለመሆኑ የትኛ ው/ዋ የቅንና የሚዛናዊ ህሊና ባለቤት የአገሬ ሰው ነው/ናት  ንፁሃን በገፍና በግፍ ቢገደሉም፣ ለማይተካ የአካል ጉዳት ቢዳረጉም፣ ለሰቆቃዊ መፈናቀል ቢጋለጡም ፣ በየማሰቃያ ማእከሉ የከባድ ሰቆቃ ሰለባዎቸ ቢሆኑም ፣ ህፃናት ከወላጆቻቸው አስከሬን ሥር ተቀምጠው በእንቅልፍ ቢንገላቱም ፣ እናት ከማህፀኗ ተተርትሮ እንዲወጣ ከተደረገው ልጇ ጋር ህይወቷ ቢያልፍም፣ ቤተ እምነቶች ከአገልጋዮቻቸውና አማኞቻቸው ጋር በእሳት ቢጋዩም፣ እጅግ አያሌ ቁጥር ያላቸውን ህፃናትንና አረጋዊያንን ጨምሮ በአያሌ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ንፁሃን ወገኖች በአስከፊ የርሃብ ቸነፈር ቢመቱም ፣ ወዘተ "ታሪካዊ"  ግድብ ወይም መንገድ ወይም መታሰቢያ ወይም መናፈሻ ፣ ወዘተ ከተሠራልኝ ለደስታዬ ወሰን የለውም የሚል (የምትል)?

Ø  የትኛው እውነተኛ ሃይማኖታዊ እምነት ነው በፈጣሪ አምሳል የተፈጠረው ሰብአዊ ፍጡር (ሰብአዊ ህንፃ) በባለጌና በጨካኝ ገዥዎች ለማመን በሚከብድ አኳኋን ቢወድምም ቁሳዊ ፕሮጀክቶች እዚህና እዚያ እስከ ተገነቡ ድረስ ደስ ይበላችሁ የሚል???

Ø  የትኛው ትክክለኛ ዓለማዊ አስተሳሰብና ፍልስፍና ነው በነፃነት፣ በፍትህና በተገቢው አያያዝ ቢያድጉ ፣ ቢማሩና ቢመራመሩ አገራቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ምድረ ገነት በሚያደርጉ የእድገትና የልማት አውታሮችና መረቦች ሊያጎናፅፉ የሚችሉ ህፃናትና ታዳጊ ወጣቶች ህይወት በእኩያን ገዥ ቡድኖች ጨካኝ ሰይፍ ቢሰየፉም የእነ አብይ/የእነ ብልፅግና ፕሮጀክቶችን በአድናቆትና በምሥጋና መቀበልና መደገፍ ተገቢ ነውና ተቀበሉና ደግፉ  የሚለው? ሁለገብ እውነትን በውስጣቸው የተሸከሙ ንፁሃን ወገኖችን መገደል እውነትን ራሱን መግደል አይደለም እንዴ???

 

የአሁኖቹ ተረኛ ገዥ ቡድኖች ለሩብ ምእተ ዓመት የዘለቀውን ቆሻሻን አስገብቶ በቆሻሻ የመተካት እጅግ መሪር የፖለቲካ ሥርዓት ዑደትን እንደ ዴሞክራሲያዊ ፣ ሰላማዊና የሥልጡኖች ፖለቲካ እያስመሰሉ የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሰብእና ቀውስ ልክፍተኛ በሆነው አብይ አህመድ አማካኝነት ሊያሳምኑን የመሞከራቸው ድፍረት የሚነግረን እንደ አገር (እንደ ህዝብ) እየወረድን ያለንበትን አስከፊና አስፈሪ ሁኔታ ነውና በስሜታዊነትና በክስተቶች ፈረስ ከመጋለብ ተቆጥበን የየራሳችንን ህሊና መጠየቅ ግድ ከሚለን ጊዜና ሁኔታ ላይ ነው የምንገኘውና ልብ ያለው ልብ ይበል።

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/188872
በእጅጉ ከቆሸሸ ሥርዓት የቆሻሻ ዑደት እና ውጤት እንጅ የተለየ ነገር አይጠበቅም!!!
February 18, 2024

ጠገናው ጎሹ

ከቆሸሸ ግብአት የቆሸሸ ውጤት (GARBAGE IN, GARBAGE OUT) እንጅ የተለየ ውጤት መጠበቅ ፈፅሞ አይቻልም።

ይበልጥ አስከፊ በሆነ መልኩ ፈፅሞ ሊፀዳ በማይችል መርዘኛ የፖለቲካ ቆሻሻ /ወንጀል ከበበሰበሰና ከከረፋ የፖለቲካ ሥርዓተ ዑደትም ይበልጥ አደገኛ የሆነ መርዘኛ ቆሻሻን እንጅ ሌላ የተለየ ውጤትን መጠበቅ ፈፅሞ አይቻልም ።

ለዚህ ደግሞ በእኩያን የህወሃት የፖለቲካ ኢሊቶች የበላይ ዘዋሪነት (ተቆጣጣሪነት) እና ከአምስት ዓመታት በፊት ጀምሮ በተረኝነት ሥልጣነ መንበር ላይ ተሰይመው የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካውን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ አስከፊና አስፈሪ ሁኔታ እያስኬዱት ባሉት ገዥ ቡድኖች አሽከርነት (መሣሪያነት) ተፈፃሚ የሆነውና እየሆነ ያለው ህገ መንግሥት (ህገ ጥላቻ፣ ህገ መለያየት ፣ ህገ ጭቆና ፣ ህገ ዝርፊያ ፣ ህገ ሰቆቃ፣ ህገ መከራ፣ ህገ ውርደት፣ ህገ ገዳይ/ አስገዳይ/አገዳዳይ፣ ህገ ምድረ ሲኦል፣ ወዘተ) በመሣሪያነት እየተጠቀሰ ካደረሰውና እያደረሰ ካለው ሁለንተናዊ አገራዊ ሰቆቃ በላይ ግዙፍና መሪር ማስረጃ የለም ፤ አይኖርምም። ለእንዲህ አይነት ምንነት፣ ማንነት፣ እንዴትነት እና ከየት ወደ የትነት የዳረገንን የገዛ ራሳችን ግዙፍና መሪር እውነት በመጋፈጥ ትውልዳዊ የሆነ መሠረታዊ ዴሞክራሲያው ለውጥን እውን ከማድረግ ይልቅ ሰንካላ የሰበብ ድሪቶ መደረቱ ስለሚቀናን መቀበል እያቃተን ነው እንጅ በፖለቲካ ታሪካችን ሂደት እንዲህ አይነት በመርዛማ ቆሻሻ ዑደትና ውጤት የተበከልንበት ፈተና አጋጥሞን አያውቅም።

ይህንን አስተያየቴን የተጋነነ ወይም ለገዥ ቡድኖች ከሚኖር ጭፍን ጥላቻ እንደሆነ አድርገው ለማየትና ለማሳየት የሚሞክሩ ወገኖች እንደሚኖሩ በሚገባ እገነዘባለሁ። እንዲህ አይነቱ አስተሳሰብ የሚመነጨው ግን መሬት ላይ ያለውን ግዙፍና መሪር እውነታ ተረድተው የሚጠበቅባቸውን ድርሻ ለመወጣት ጥረት ከሚያደርጉ ወገኖች ሳይሆን አንድም ቀጥተኛ ከሥርዓቱ ተጠቃሚዎች ወይም በንፁሃን ደምና መከራ ከሚነግዱ ግለሰቦችና ቡድኖች ወይም  የሥርዓቱ ፍርፋሪ ለቃሚዎች ከሆኑ የአድርባይነት ልክፍተኞች ወይንም ደግሞ ከእኩያን ገዥዎች የሚመነጨውን መከራና ውርደት እንደ እጣ ፈንታ እንድንቆጥር ካደረገን ሥር የሰደደ ድንቁርና እንደሚሆን ለማወቅ የተለየ እውቀትን አይጠይቅምና ቢያሳዝነኝም አይገርመኝም።

በተለይም የለየላቸው የሥርዓቱ ባለሥልጣናትና ካድሬዎች ፈጣሪ ራሱ ተገልጦ “በአምሳሌ በፈጠርኩት ህዝበ አዳምና ሄዋን ላይ ግዙፍና እጅግ አስከፊ የመከራ ዶፍ እያወረዳችሁ ስለ የትኛው ሰላምና ብልፅግና ነው የምተርኩት ወይም የምትሰብኩት ወይም የድል አድራጊነት ዲስኩር የምትደሰኩሩት”? ብሎ ቢጠይቃቸው “ይህ በእግዜር አምሳል የተገለጠ ሰይጣን እንጅ እግዜር ራሱ አይደለም” እስከ ማለት የሚደርሱ እጅግ ባለጌዎች፣ ደንቆሮዎች ፣ ሴረኞች፣ ሸፍጠኞችና ጨካኞች መሆናቸውንን መሬት ላይ ተዘርግቶ የሚነበበው ድርጊታቸው ስለሚናገር ብዙ ማለት የሚያስፈልገኝ አይመስለኝም።

እንዲህ አይነቱን እጅግ አስከፊና ዘመን ጠገብ አዙሪት ሰብሮ ለመውጣት ከምር የምንፈልግ ከሆነ መሠረታዊ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ለውጥን በብሩህ ራዕይ ፣ በፅዕኑ የመርህ፣ የዓላማና የግብ መሠረት ላይ ተመሥርቶ እውን ከማድረግ ይልቅ እገሌ የሚባለው/ዋ ካድሬ ወይም አድርባይ ተሽሮ/ራ እገሌ የሚባል/ትባል ተሾመ/ች ወይም  በሽግሽግ ወደ ሌላ ሥልጣን ተዛወረ/ች ወይም “በክብር” ተሰናበተ/ች ወይም የተቃውሞ ዲስኩር ደስኩሮ/ራ ተሰደደ/ች ወይም በካድሬነቱ/ቷ ወቅት ንፁሃንን ሲያሳስርበት /ስታሳስርበት ወደ ነበረው ከርቸሌተወረወረ/ች ፣ ወዘተ የሚለውን የመርዘኛ ቆሻሻ ዑደት (garbage in, garbage out) ከማመንዠክ ክፉ ልማድ አሁንኑ ሰብረን በመውጣት ለዜጎች ሁሉ የምትመች አገርን እውን ማድረግን ግድ ይለናል። ዘመናትን ያስቆጠረው የሸፍጥ፣ የሴራ እና የጭካኔ ፖለቲካ ባህሪያቸውና ተግባራቸው ግልፅና ግልፅ የሆነውን የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማርተኞች የቆሻሻ ግባ እና የቆሻሻ ውጣ (garbage in, garbage out) የፖለቲካ ጨዋታ እንደ ሰላማዊ የሥልጣን መተካካት ፣ እንደ ጤናማ የሥልጣን ሽግሽግ እና በአጠቃላይ እንደ አወንታዊ የለውጥ ሂደት እየቆጠርን ራሳችንን ከደመ ነፍስ እንስሳት በማይሻል ሁኔታ ውስጥ የማግኘታችንን መሪር እውነታ በቅጡ (ከምር) ካልተረዳነውና ካልተፀየፍነው የመረረ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎ ለማካሄድና የምንመኘውን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ለማድረግ ፈፅሞ አይቻለንም።

የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን የሞራልና የሥነ ምግባር ሰብዕና ቀውስ የተጠናወተው የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየ አብይ አህመድ ከዛሬ ስድስት ዓመታት በፊት የህወሃቱን መለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ ተላብሶ (የራሱን የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን የሞራል ሰብዕና ለሟች አለቃው በቀፎነት አሳልፎ ሰጥቶ) በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣነ መንበር ላይ የቆየውን ሃይለማርያም ደሳለኝን  ሲተካው እና ታሪካዊ የሆነ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር (መተካካት) በሚል በመከረኛው ህዝብ ላይ ሲሳለቁበት ከምር በመቆጨት፣ በመፀፀትና በመቆጣት እምቢ ለመሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለውጥ ብሎ ለመነሳትና ለማነሳሳት ያለመቻላችን አስከፊና አሳፋሪ ውድቀት ያስከተለብንና እያስከተለብን ያለው ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ የመከራና የውርደት ዶፍ አሁንም መሪር ተሞክሮ ካልሆነን ምን አይነት መከራና ውርደት ትምህርት ሆኖ ሊያነሳሳን እንደሚችል ከባድ እእቆቅልሽ ነው።

በዚህ ረገድ ቀዳሚው ከፈተና ወዳቂ በአብዛኛው ተማርኩ ብቻ ሳይሆን “ሊቅነት ከእኔ ወዲያ ላሳር ነው” በሚል የሚኮፈሰው የህብረተሰብ ክፍል ነበር። አሁንም ነው። ዘመን ጠገብ የሆነውንና በእጅጉ የተበላሸውን የአገሩን ፖለቲካ በመስማት ሳይሆን በመኖር የሚያውቀው ይህ የህብረተሰብ ክፍል መከረኛው ህዝብ የሸፍጠኞችንና የሴረኞችን "የተሃድሶ ገድል" አክሽፎ የእውነተኛ ለውጥ ባለቤት ይሆን ዘንድ ማነሳሳቱ (እምቢ ለቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ ፖለቲካ  ጨዋታ እንዲል) ማስቻሉ ቢቀር እንኳ ለምን? እንዴት? እና ከየት ወደ የት? የሚሉ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ጊዜ ሳይወስድ የአዙሪቱ ሰለባ የሆነ እለት ነበር የመከራውና የውርደቱ ፖለቲካ በአስከፊ ሁኔታ ሊቀጥል እንደሚችል ግልፅና ግልፅ የሆነው።

ካለፈ ስህተትና ውድቀት ተምረን የተሻለ ዛሬንና በጣም የሚሻል ነገን እውን ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ ላይ ብንሆንና ይህንን ግዙፍና መሪር የሆነ የውድቀት ድግግሞሽ በዚህ አይነት የምሬት ስሜት ባልገልፀው ደስ ባለኝ ነበር።

አሁንም ወርቃማ የሆነውን የህልውና ማስከበር እና የመሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለውጥን በቆሻሻ ግባ እና በቆሻ ውጣ (garbage in, garbage out)  የፖለቲካ ሥርዓት መቃብር ላይ ስለ መመሥረትና ስለ መገንባት ሳይሆን ከቆሻሻ  የፖለቲካ ዑደት አንዳች መልካም ነገር (ወጤት) ከመጠበቅ ክፉ አባዜ አልተላቀቅንምና ወደድንም ጠላንም የውድቀታችን እንቆቅልሽ እስኪፈታ ድረስ በግልፅና በቀጥታ መነጋገራችን የግድ ነው።

"በሙሲያዊው አብይ አህመድ" መሪነትና በካምፓኒው (በኦህዴድ/ኦነግ ብልፅግና) መዋቅራዊ አስፈፃሚነት የተካሄደውና እየተካሄደ ያለው ፖለቲካ ወለድ ወንጀል በመርዘኛ የሥልጣን መተካካት ቆሻሻ የጨቀየ መሆኑን ግልፅ ካላደረገልን እውነትም አቻ የማይገኝለት ድንቁርና ፣ የትኛውንም ምድራዊ መከራና ውርደት የመለማመድ አስከፊ ልክፍት ፣ ጨርሶ አቻ የማይገኝለት የአድርባይነት ደዌ ፣ ወደ ተግባር ሊተረጎም የማይችል ተስፈኝነት ፣ ወዘተ አባዜ  በእጅጉ ተጠናውቶናልና ከምር ሊያሳስበን ይገባል።

የተፈጠርንበትን በነፃነት ጥሮና ግሮ የመኖር ዓላማ ከፈጣሪ ድጋፍ ጋር እውን እያደረግን እንደ መልካም ዜጋ እና እንደ ሰው ሰው ሆነን የምንኖርበትን ሥርዓተ ፖለቲካ አምጦ ከመውለድና ከማጎልበት ይልቅ የመርዘኛ ቆሻሻ ፖለቲካ ዑደትንና ውጤትን (መሾምና መሻርን ወይም የጉልቾች መቀያየርን /garbage in, garbage out) እንደ አበረታች (አወንታዊ) የለውጥ አካል የመቁጠራችንን እጅግ ወራዳና አዋራጅ ሁኔታ ከምር ለሚረዳ የአገሬ ሰው ምን ያህል ህሊናውን እንደሚፈታተነው ለመገመት አያስቸግርም።

እውነት ነው በሥራ ሂደት ውስጥ በአቅም ማነስ ወይንም በጊዜያዊ የፍላጎትና የጥቅም ግጭት ምክንያት የመቆሸሽ እንከን ሊያጋጥመው እንደሚችል አካል በመንበረ ሥልጣን ላይ የተቀመጡ ወይም የሚቀመጡ ፖለቲከኞችም የመቆሸሽ ፈተና ሊገጥማቸው እንደሚችል ለመረዳት አያስቸግርም።የማይጠበቅም አይደለም። የእኛ ግን ከዚህ አይነት ሊጠበቅ ከሚችል የመቆሸሽ እውነታ ፈፅሞ ሊታይና ሊነፃፀር የሚችል ጉዳይ አይደለም። ሊጠበቅ ይችላል የምንለው የመቆሸሽ ፈተና ወይም ችግር ቅንነትንና አስተዋይነትን በተላበሰ አስተሳሰብና የተግባር ውሎ መስተካከል (መፅዳት) የሚቼል ሲሆን ለሩብ ምዕተ ዓመት የዘለቀውና ከስድስት ዓመታት ወዲህ ደግሞ የመከራውንና የውርደቱን አገዛዝ እንኳን ለመገመት ለማሰብም በእጅጉ በሚዘገንን ፖለቲካ ወለድ ወንጀል እያስኬደ ያለው ብልፅግና ተብየ ግን ያለ መሠረታዊ የለውጥ ህክምና (ተጋድሎ) በፍፁም የሚስተካከል ወይም የሚፈወስ አይደለም።

እናም ለዘመናት በሥልጣነ መንበር ላይ በመፈራረቅ ወይም ቆሻሻን አስገብቶ ቆሻሻን በመተካት (garbage in, garbage out) የፖለቲካ ጨዋታ በህዝብ ላይ እጅግ አሰቃቂ የመከራና የውርደት ዶፍ ማውረድ በትክክለኛው ሃይማኖታዊም ሆነ ዓለማዊ አስተሳሰብና እምነት እንኳንስ ተቀባይነት ታጋሽነትም ፈፅሞ ሊቸረው የሚገባው ጉዳይ አይደለምና ልብ ያለው ልብ ይበል ።

ለመሆኑ፦

Ø  የአገርን ልዑላዊነት በግልፅ አሳልፎ እየሰጠ (ከሱዳን እና ከደቡብ ሱዳን ጋር በምንዋሰንባቸው አካባቢዎች የሆነውንና እየሆነ ያለውን ልብ ይሏል) የልዑላዊነት  ሥልጣን (ወደ ሥልጣን የማውጣትና ከሥልጣን የማውረድ ሃይል) አለው የሚባለውን የገዛ አገሩን  ህዝብ ለፖለቲካ መንበሩ ያሰጋል በሚል ከውጭ ጠላት በባሰ ጭፍጨፋ  ዝም ጭጭ ያስደርግለት  ዘንድ በቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ የፖለቲካ ዑደት (the political cycle of garbage in, garbage out) መርህና አሠራር መሠረት  ለሾመው  ብርሃኑ ጁላ በዓለም ወታደራዊ የሥልጣን እርከን በቀላሉ የማይገኘውን የፊልድ ማርሻልነት ማዕረግ ከማሸከም የከፋ ምን አይነት የህዝብ (የአገር) ንቀት ይኖራል? ምንስ አይነት መርዘኛ የሆነ የቆሻሻ ግባና የቆሻሻ ውጣ የፖለቲካ አዙሪት ይኖራል?

Ø  ሲሆን የፖለቲካው አውድ በየመስኩ ለሚደረጉ ሙያዊ ጥረቶችና ውጤቶች  (professional engagements and products) የሚበጅ እንዲሆን የመልካም ዜግነት ድርሻን በመወጣት ፣ ያ ካልሆነ ደግሞ በሙያቸው የሚችሉትን አስተዋፅኦ በማድረግ የሚጠበቅባቸውን ተልእኮ መወጣት የነበረባቸውንና ያለባቸውን ባለሙያዎች የመርዘኛ ቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ ፖለቲካ ጨዋታ ተዋንያን ማድረግ በእጅጉ አስከፊና አስፈሪ  የሆነ ውድቀታችንን ካልነገረን ሌላ ምን ሊነግረን የሚችል ነገር ይኖራል?

 

Ø  በዚህ ደረጃ በበከተና በከረፋ የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ የሚተካኩ ሹማምንቶችና ካድሬዎች (የቆሻሻ ግባ እና የቆሻሻ ውጣ ፖለቲካ እድምተኞች) ንፁሃን ዜጎች እንደ የውጭ ጠላት በምድር እና በአየር ላይ ጦር ለምን የጨፈጨፋሉ? ከእለት ጉርስና ከመጠለያነት የማያልፈው ንብረታቸውስ ለምን ይወድማል?  ሲባሉ “ህግ የማስከበር ጉዳይ ነው” ፣ በፖለቲካ ወለድ ወንጀል ምክንያት ሚሊዮኖች የአሰቃቂ ርሃብ ሰለባዎች ሆነዋል እኮ ሲባሉ “ገፅታችን ለማበላሸት ሲባል እየተጋነነ ነው እንጅ ከቁጥጥራችን አልወጣም/ሰው በርሃብ አልሞተም” ፣ እጅግ አያሌ ቁጥር ያላቸው ዜጎች በሚፈበረክ  የወንጀል ክስ በየማሰቃያው ማእከል እየተሰቃዩ አይደለም ወይ? ተብለው ሲጠየቁ “በፖለቲካ ምክንያት የታሰረ የለም፤ለማነኛውም በህግ እየታየ ያለ ጉዳይ ነው” ፣ አያሌ ንፁሃን በማንነታቸው ሲገደሉና ሚሊዮኖች ደግሞ እጅግ ኢሰብአዊ ለሆነ መፈናቀል ሲዳረጉ ማየት አያስጨንቅም ወይ? ሃላፊነቱስ በዋናነት የመንግሥታችሁ አይደለም ወይ? የሚል መሪር ጥያቄ ሲቀርብባቸው “በለውጥ ሂደት የሚያጋጥም እንጅ እንደሚወራው አይደለምና የሚጣራ ካለም  ይጣራል፤ ተፈናቃዮችንም ወደ አካባቢያቸው ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው” ፣ ወዘተ እያሉ በሚጣልላቸው (በሚከፈላቸው) ምንዳእ (ደመወዝና ልዩ ጥቅም) ከርሳቸውን ሞልተው  መኖራቸውን እንደ  የህይወት ስኬት የመቁጠራቸው መሪር እውነት ለማይታጠፍ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎ የማያነሳሳው ትውልድ ምን አይነት ነፃነትንና ፍትህን እንደሚናፍቅና መቸ እውን እንደሚያደርገው ለመረዳት አይከብድም እንዴ?

 

Ø  ከክልሎች ሁሉ በተለየ የአማራ ክልል እነ ገዱ አንዳርጋቸውን፣ ተመስገን ጥሩነህን፣ ይልቃል ከፍያለን፣ እና የአሁኑን አረጋ ከበደን የመርዘኛ ቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ የፖለቲካ ጨዋታ አሻንጉሊቶች (የሰው አምሳል ያላቸው እቃዎች) በማድረግ በህዝብ ላይ  የመከራና የውርደት ዶፍ ባወረደውና እያወረደ ባለው ኦህዴድ/ኦነግ መራሽ ብልፅግና ተብየ የበላይነት ሥር በሚካሄድ ንግግርና ድርድር  ከዘመን ጠገቡ ክፉ የፖለቲካ አስተሳሰብና አካሄድ ተላቀን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እናዋልዳለን ብሎ ከማሰብ የባሰ የፖለቲካ አስተሳሰብ ድንቁርና እና የሞራል ድህነት ይኖር ይሆን?

 

Ø  ዘመን ጠገብ የሆነውን የጉልቾች የመተካካት (ቆሻሻን አስገብቶ ቆሻሻ የማስወጣት) የፖለቲካ ዑደት አራጊና ፈጣሪ እኩያን ገዥ ቡድኖች ጥሩ ሲሠሩ እያመሰገንና ሲሳሳቱ እየወቀስን ካልያዝናቸው አገር ይፈርሳል የሚሉት እጅግ ደምሳሳና የወረደ የፖለቲካ ማስፈራሪያ የቦቅቧቆች ወይም በቁም እየሞቱ አለን የሚሉ ፖለቲከኞች (cowardly and dead alive politicians) ማስፈራሪያ ካልሆነ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?  የገዛ ራስን መሪር እውነት ከምር በሆነ ፀፀትና ቁጭት ተረድቶ ከዚህ አይነቱ ልክ የሌለው የመከራና የውርደት አዙሪት ሰብሮ በመውጣት ህልውና የሚረጋገጥባት እና ለዜጎቿ ሁሉ የምትመች ዴሞክራሲያዊት አገርን እውን ለማድረግ የበኩሉን ድርሻ የማይወጣ ነፃነትና ፍትህ ፈላጊ ነኝ ባይ ምን አይነት ነፃነትና ፍትህ ነው የሚፈልገው?

 

Ø  ከዛሬ ሰላሳ ዓመታት በፊት ህወሃት በአምሳሉ ጠፍጥፎ በሠራቸው አሽከሮቹ (የሚናገሩ አጋሰሶች) እየተመራ ወደ መሃል አገር ሲገሰግስ ለአሽከርነት ምልመላ ዒላማዎቹ ካደረጋቸው ተቋማት መካከል የትምህርት ተቋማት ዋነኛዎቹ ነበሩ ። የዚህ እኩይ ዒላማው ለመሆን በሙሉ ፈቃደኝነት ይጠባበቁ ከነበሩት ደናቁርትና ትውልድ ገዳይ ፊደል ቆጣሪዎች (አስተማሪዎች) መካከል ደመቀ መኮንን አንዱ ነበር። ለዚህም ነበር በቡሬ (ጎጃም) በባዮሎጅ አስተማሪነት ላይ እያለ በጉጉት ሲጠባበቅ የነበረውን የፍፁም ታማኝነት ካድሬነቱን ተልእኮ በደስታ ተቀብሎ መፈፀምና ማስፈፀም የጀመረው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ የኢህአዴግ ስምሪቶችን እየተቀበለ (የእኩይ ፖለቲካ መልእክቶችንና ዓላማዎችን የሚጫንና የሚያስተላልፍ አጋሰስ እየሆነ) ለሰላሳ ዓመታት ካገለገለ በኋላ ከሰሞኑ “በል በቃህ ጥቅማጥቅምህን ይዘህ ዘወር በል” ሲሉት ውርደቱን እንደ ክብር ቆጥሮ ፣ በአጠቃላይ በመላው ህዝብ እና በተለይ ደግሞ ተገኘሁበት በሚለው ማህበረሰብ ላይ የፈፀመውንና ያስፈፀመውን ግፍ  እንደ  መልካም ውለታ ቆጥሮ፣ አጋሰስ ካድሬነቱን (መሣሪያነቱን) ትጉህና ቅን መሪ አስመስሎ ፣ ከራሱ አልፎ የቤተሰቦቹ ማፈሪያ የመሆኑን መሪር እውነታ የኩራት ተምሳሌት አድርጎ ፣ ወዘተ ሊያሳምነን (ሊያቄለን) ሲሞክር መስማትና ማየት ቅንና ሚዛናዊ ህሊና ባለው የአገሬ ሰው ላይ የሚያሳድረውን ህመም ስንቶቻችን ነን ከምር የምንጋራው? ታዲያ መቸና እንዴት ነው ከዚህ አይነቱ የእኩያን ፖለቲከኞች የጉልቾች መተካካት (ቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ  ውጣ) አዙሪት ሰብሮ በመውጣት እውነተኛ ዴሞክራሲያዊት አገርን እውን ማድረግ የሚቻለው?

 

Ø  የደመቀ ድርብ የታማኝ ካድሬነት ሥልጣን የተቸራቸው ሁለት ግለሰቦች ናቸው። አንደኛውና በአብይ አህመድ መልካም ፈቃድ የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሹመተ ቅብአት የተቀባው በግልፅ የባለጌዎች፣ የሸፍጠኞች፣ የሴረኞች ፣ የፈሪዎችና የጨካኞች ስብስብና እጅግ አስከፊ የኢህአዴግ ውላጅ የሆነው የብልፅግና አባል የሆነው እና ሰብዕናውን ለእኩያን ገዥዎች ሶፍት ዌር ማስቀመጫነት (as a hardware) አሳልፎ የሰጠ መሆኑን ባህሪውና ድርጊቱ የሚመሰክርበት ተመስገን ጥሩነህ ነው። ለጌቶቹ፣ ለቢጤዎቹ፧ ለፍርፋሪ ለቃሚ አድርባዮች ካልሆነ በስተቀር የዚህ ሰው ምንነት፣ ማንነት ፣ ለምንነት፣ እንዴትነት፣ እና ከየት ወደ የትነት ግልፅና ግልፅ ስለሆነ ብዙ ማለት የሚያስፈልገኝ አይመስለኝም።

 

Ø  ሌላኛው ደግሞ “አባል አይደለሁም” በሚል ሽፋን በሥልጣነ መንበር ላይ ለሚፈራረቁ እኩያን ገዥ ቡድኖች ሁሉ ከለየላቸው ካድሬዎቻቸው በባሰ ሁኔታ በፍፁም ታማኝነት ለረዥም ጊዜ ያገለገለው (የራሱ የሆነና ሥር የሰደደ ወይም አብሮት ያደገና የጎለመሰ የአድርባይነት ፍልስፍና እና ባህሪ የተጠናወተው) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመተ ቅብአትን የተቀባው ታየ አፅቀ ሥላሴ ነው።  ለሦስት ዓሥርተ ዓመታትና በተለይም ከስድስት ዓመታት ወዲህ አገረ ኢትዮጵያን የንፁሃን ዜጎች (ልጆቿ) ምድረ ሲኦል ያደረጓትንና እያደረጓት ያሉትን እጅግ ባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች መመሪያና ትእዛዝ እየተቀበሉ ንፁሃንን እንደ ወንጀለኛ እና  በሌላ በኩል ግን ጨካኝ የፖለቲካ ሰይፋቸውን  እንደ ህግና ሰላም አስከባሪ በማድረግ በዲፕሎማሲ ስም ርካሽና አደገኛ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ  ያካሄዱትንና አሁንም እያካሄዱ ያሉትን ወገኖች አካፋን አካፋን ለማለት በሚያስችል አቋምና ቁመና ቢያንስ ነውር ነው ማለት የግድ አይለንም ወይ?

እንደ ታየ አይነት እጅግ አሳሳችና አደገኛ ግለሰቦችን ጎምቱ ዲፕሎማት፣ በታላቁ ግድብ ጉዳይ ዙሪያ ግብፅን ያንቀጠቀጡ፣ ህወሃትና ብልፅግና ባካሄዱት ጦርነት ብልፅግናን ወክለውና ሸንጣቸውን ገትረው የተከራከሩ ፣ ለአብይ አህመድ የኖቬል እና የፋኦ ሽልማት መብቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ ፣ የአብይ አህመድን የመናፈሻ፣ የችግኝ ተከላ፣ የመንገድ ጥረጋ፣ ወዘተ ዘመቻ በዓለም አድናቆትን እንዲያተርፍ ያደረጉና እያደረጉ ያሉ በሚል መከረኛውን ህዝብ ጨምሮ የርካሽ ፕሮፓጋንዳ ሰለባ የማድረጋቸው መሪር እውነት የሚነግረን የዲፕሎማሲን እውነተኛ ምንነትና ለምንነት (የህዝብ/የብሔራዊ ጥቅም ማራመጃና ማስከበሪያነት) ለባለጌና ጨካኝ ገዥ ቡድኖች ርካሽ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፃሚነት እንዲውል የማድረጋችንና በማድረግ ላይ የመሆናችንን መሪር እውነታ ነው።ታዲያ ለዚህ ሁሉ አስከፊ ሁኔታ መቀጠል ዋነኛው ምክንያት ሴረኛ፣ ሸፍጠኛና ጨካኝ የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ዘዋሪዎች (አራጊና ፈጣሪዎች) የሚያካሂዱትን የጉልቻ መቀያየር (የቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ) ፖለቲካ እንደ የተሃድሶ ለውጥ እና  የሰላማና የልማት ዋስትና እያደረጉ ሲሳለቁብን ለዚሁ በሚመጥን የጋራ ትግል አደባባይ ላይ ለመሰባሰብ አለመቻላችን ነውና አሁንም ተጨማሪ ጊዜ እና ሌላም ውድ ነገር ሳናባክን ህልውና ለሚረጋገጠባትና ነፃነትና ፍትህ (ዴሞክራሲ) ለሚሰፍንባት አገረ ኢትዮጵያ እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ በማካሄድ ላይ ከሚገኙ ወገኖች ጋር ከምርና ጨርሶ ወደ ኋላ በማይመለስ አቋምና ቁመና መተባበርን የማይቀበል ነፃነትና ፍትህ ፈላጊ ይኖርህ ይሆን?

 

Ø  እስኪ ለመሆኑ የትኛ ው/ዋ የቅንና የሚዛናዊ ህሊና ባለቤት የአገሬ ሰው ነው/ናት  ንፁሃን በገፍና በግፍ ቢገደሉም፣ ለማይተካ የአካል ጉዳት ቢዳረጉም፣ ለሰቆቃዊ መፈናቀል ቢጋለጡም ፣ በየማሰቃያ ማእከሉ የከባድ ሰቆቃ ሰለባዎቸ ቢሆኑም ፣ ህፃናት ከወላጆቻቸው አስከሬን ሥር ተቀምጠው በእንቅልፍ ቢንገላቱም ፣ እናት ከማህፀኗ ተተርትሮ እንዲወጣ ከተደረገው ልጇ ጋር ህይወቷ ቢያልፍም፣ ቤተ እምነቶች ከአገልጋዮቻቸውና አማኞቻቸው ጋር በእሳት ቢጋዩም፣ እጅግ አያሌ ቁጥር ያላቸውን ህፃናትንና አረጋዊያንን ጨምሮ በአያሌ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ንፁሃን ወገኖች በአስከፊ የርሃብ ቸነፈር ቢመቱም ፣ ወዘተ "ታሪካዊ"  ግድብ ወይም መንገድ ወይም መታሰቢያ ወይም መናፈሻ ፣ ወዘተ ከተሠራልኝ ለደስታዬ ወሰን የለውም የሚል (የምትል)?

Ø  የትኛው እውነተኛ ሃይማኖታዊ እምነት ነው በፈጣሪ አምሳል የተፈጠረው ሰብአዊ ፍጡር (ሰብአዊ ህንፃ) በባለጌና በጨካኝ ገዥዎች ለማመን በሚከብድ አኳኋን ቢወድምም ቁሳዊ ፕሮጀክቶች እዚህና እዚያ እስከ ተገነቡ ድረስ ደስ ይበላችሁ የሚል???

Ø  የትኛው ትክክለኛ ዓለማዊ አስተሳሰብና ፍልስፍና ነው በነፃነት፣ በፍትህና በተገቢው አያያዝ ቢያድጉ ፣ ቢማሩና ቢመራመሩ አገራቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ምድረ ገነት በሚያደርጉ የእድገትና የልማት አውታሮችና መረቦች ሊያጎናፅፉ የሚችሉ ህፃናትና ታዳጊ ወጣቶች ህይወት በእኩያን ገዥ ቡድኖች ጨካኝ ሰይፍ ቢሰየፉም የእነ አብይ/የእነ ብልፅግና ፕሮጀክቶችን በአድናቆትና በምሥጋና መቀበልና መደገፍ ተገቢ ነውና ተቀበሉና ደግፉ  የሚለው? ሁለገብ እውነትን በውስጣቸው የተሸከሙ ንፁሃን ወገኖችን መገደል እውነትን ራሱን መግደል አይደለም እንዴ???

 

የአሁኖቹ ተረኛ ገዥ ቡድኖች ለሩብ ምእተ ዓመት የዘለቀውን ቆሻሻን አስገብቶ በቆሻሻ የመተካት እጅግ መሪር የፖለቲካ ሥርዓት ዑደትን እንደ ዴሞክራሲያዊ ፣ ሰላማዊና የሥልጡኖች ፖለቲካ እያስመሰሉ የፖለቲካ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሰብእና ቀውስ ልክፍተኛ በሆነው አብይ አህመድ አማካኝነት ሊያሳምኑን የመሞከራቸው ድፍረት የሚነግረን እንደ አገር (እንደ ህዝብ) እየወረድን ያለንበትን አስከፊና አስፈሪ ሁኔታ ነውና በስሜታዊነትና በክስተቶች ፈረስ ከመጋለብ ተቆጥበን የየራሳችንን ህሊና መጠየቅ ግድ ከሚለን ጊዜና ሁኔታ ላይ ነው የምንገኘውና ልብ ያለው ልብ ይበል።

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/188872

Sunday, February 18, 2024

   ‹‹የቆላ አጋዘን የገደለ መቶ ከብት ወይም ተመጣጣኝ ካሣ እንዲከፍል አባ ገዳዎች ወሰኑ፡፡››    
ኢት-ኢኮኖሚ            /ET- ECONOMY

  ‹‹የወባ ትንኝ ለመግደል መድፍ አይተኳስም!!!›› Do not use a cannon to kill a mosquito.

ፂዮን ዘማርያም (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

‹‹ወጡ ሳይወጠወጥ

ወስከንባው ላይ ቁጢጥ!!!››

‹‹ በዚያም ወራት በግንቦት አስር ቀነ በ1901 ዓመተ ምህረት ዳግማዊ ምኒልክ ሰፊ በሆነችው አደባባይ በጃንሜዳ ጉባዔ አደረገ፡፡ አዛውንቱን፣ መኳንንቱን፣ የኢትዮጵያን ህዝብ ሁሉ ሰበሰበ፡፡ እንዲህም አላቸው፡- በአፄ ቴዎድሮስ ሞት ጊዜ የተደረገውን ልንገራችሁ ስሙኝ፡፡ አንዱ ሁለተኛውን እየገፋው፣ ሁለተኛው ሦስተኛውን እየገፋው ሠራዊቱ ሁሉ አለቁ፡፡ ከእነርሱም አንድ አልቀረ፡፡ በአፄ ዮሐንስ ሞት ጊዜም በየሀገሩ የሆነውን  አይታችኃል፤ ይልቁንም በትግሬ ምድር፡፡ በሀገራቸው ህመም /በሽታ/ ሳይገባ፣ጠላትም ሳይመጣባቸው ሁሉም እርስ በእርሳቸው አለቁ፡፡ ይህ ሁሉ እንዳይሆንባቸው ሁላችሁም በፍፁም ልባችሁ ተዋደዱ፡፡ ፍቅር ሁሉንም በደሎች ይደመስሳልና፡፡ አነዱ የሌላውን ሹመት አይመኝም፡፡ ለእርሱ በተሰጠው ይፀናል እንጂ፡፡ እርስ በእርሳችሁም አትቀናኑ፣ ቅንዓት የብዙዎችን ልብ በቁጣ ትበላዋለችና፡፡ በቅናትም የእግዚአብሔር ፀጋ አይገኝም፡፡ ልጄን አደራ ሰጥቻችኃለሁ፣ ፈቃዳችሁን ቢያደርግ ከእርሱ ጋር ኑሩ፡፡ ፈቃዳችሁን ባያደርግ፣ ምክራችሁን ባይሰማ ግን ወደ ውጭ አውጡት፤ እኔ ንቄዋለሁ፣ እንደ ጉድፍ ጥራጊም ጥየዋለሁና፡፡››…………………………….……………….(1)

‹‹የቆላ አጋዘን የገደለ መቶ ከብት ወይም ተመጣጣኝ ካሣ እንዲከፍል አባ ገዳዎች ወሰኑ፡፡›› አዲስ አበባ ግንቦት 16 ቀን 2013 ኤፍ ቢሲ (ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) አማራ በማንነቱ የተነሳ፣ በእምነቱ የተነሳ፣ “መጤ”ና “ኗሪ” እና ‹መጤ/ ሠፋሪ› በሚል የጥላቻ ትርክት ተገድለዋል፣ ታርደዋል፣ ተቃጥለዋል፡፡ ይህ ግፍ ዛሬም አልቆመም፡፡ የኦሮሞ አባገዳዎች አማራ እንዳይገደል በይፋ ያሉት ነገር የለም፡፡ የኦሮሞ አባገዳ አጋዘን እንዳይገደል ሲሞገት፣ ለምን በኦሮሞ ምድር አማራ እንዳይገደል አልተማፀነም? ለምን  የኦሮሞ ድርጅቶች ኦነግ፣ ኦፌኮ፣ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች አላወገዙም? ለምን  የክልል መንግሥቶች ይህን ገደላ አላወገዙም?   ዛሬም የአማራ ልጆች መገንዘብ የሚገባቸው በዚህ የአማራ የህልውና ትግል  አማራ ከእንሰሳ ያነሰ ዋጋ እንደተሰጠው በመረዳት ትግላችንን ምንም ሳንከፋፈል በህብረት በወንድማማችነት ከመቀጠል ሌላ ለክፍፍል ቦታ መስጠት አይገባን እንላለን፡፡  የአማራን ህዝብ ከኦህዴድ ብልጽግና መንግሥት የሰው አልባ ድሮውን ጥቃት ሳናስጥለው፣ በመራዊ በግፍ ተረሽነው በየመንገዱ ለተጣሉት የአማራዎች ደም ሳይደርቅ፣ የአማራ ገድለው በጅምላ መቃብር በግሬደር ለተቀበሩት ረስተን፣ የተቃጠሉትን የታረዱትን አማራዎችቤቱ ይቁጠራቸው ብለን፣ የሴቶችን መደፈር ሳናስቆም፣ የአማራ ፋኖ ለበትረ ሥልጣን ሳይደርስ ለሥልጣን ተጣላ ቢባል አባቶች ምንኛ ያዝናሉ! ‹‹ወጡ ሳይወጠወጥ፣ ወስከንባው ላይ ቁጢጥ ›› ከማለት በስተቀር፣ ለቅሶችን ከመቼው ተረሳ! ሐዘናችን ከመቼው ተረሳና! እግዚአብሔር ልብ ይስጠን!!!

 

የኮነሬል አብይ አህመድ የኦህዴድ ብልጽግና መንግሥት መር ሽብርተኛነት በአማራ ህዝብ ላይ

‹‹በሀገራችን ውስጥ በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት የአማራ ብሄረሰብ ተወላጆች ግምባር ቀደም ተጠቂ ይሁኑ እንጂ፣ “መጤ”ና “ኗሪ” በሚል የጥላቻ ትርክት የተቀመረው ሕገ-መንግሥት ሌሎች ብሄረሰቦችንም ለጥቃት አጋልጧቸዋል። ጉራጌዎች፣ ስልጤዎች ጋሞዎች…ወዘተ ተጠቂዎች ሆነዋል። በሃይማኖትም ክርስቲያን ኦሮሞዎች የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑት መካከል ይገኛሉ። የፌዴሬሽኑን ሕገ-መንግሥትና የክልል ሕገ-መንግሥቶችም፣ ተቀርፀው የተዋቀሩት አንዱን ‹ኖሪ/ባለቤት› የአንደኛ ደረጃ ዜጋ ሌላውን ‹መጤ/ ሠፋሪ›  በሚል የሁለተኛ ደረጃ ዜጋ ማዕከልነት ላይ የተመሠረቱ ናቸው።  በቡራዩ፣ በአርሲ፣ በሐረር፣ በድሬዳዋ፣ በሻሸመኜ፣ በዝዋይና በባሌ እስከ ሦስት ጊዜ ድረስ የተካሄደው ጥቃት፣ ባመዛኙ የአማራና ሌሎችንም “መጤ” ተብለው የተሰየሙ ብሄረሰብ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ፣ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኞችንና የዕምነት ቤቶችን ዒላማ ያደረገ ጥቃት ነው። በኢትዮጵያ የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦነግ) የዘር ማፅዳትና ኃይማኖት ፍጅት ከ1982 እስከ 2016ዓ/ም ለትውስታ ያህል እንሆ፡-

- በ1982 ዓ/ምመግቢያ ላይ፣ ህወሓት ሥልጣን ከመያዙ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ፣ በአሶሳ ከተማ ኦነግና ሻዕቢያ የተሳተፉበት ክርስቲያኖችንና አማራዎች የሚሏቸውን ለይተው ቤት ዘግተው በእሳት ማቃጠላቸው የሕዝቡ መፃዒ ዕድል ምን ሊሆን እንደሚችል አመላካች አሰቃቂ ተግባር ነበር። በሻብያ፣ ህወሓትና በኦነግ የተፈፀመ የዘር ጭፍጨፋ ነበር፡፡ ሻብያ መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ መለስ ዜናዊና ሌንጮ ለታ በጆኖሳይዱ ተጠያቂዎች ናቸው፡፡

- በ1984/85 ዓ/ም በአርሲ ሃገረ-ስብከት አርባጉጉ አውራጃ በ680 ካህናትና ኦርቶዶክሳዊያን በአሰቃቂ አረመኔዊ ተግባር ታርደዋል፣ ተቃጥለዋል ከገደል ላይ ተወርውረዋል፡፡ቤተክርስቲያኖች ተቃጥለዋል፣ ቅርሶች ተዘርፈዋል፣ አርባ ሦስት ሽህ ምዕመናን ተሰደዋል፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- በምዕራብ ሐረርጌ ሃገረስብከት አሰቦት ገዳምና አቡነ ሣሙኤል ገዳም መነኮሳትና ምዕመናን በግፍ ታርደዋል፣ አብያተ ክርስቲያኖች ተቃጥለዋል፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- 1998 ዓ/ም በህዳር 8 እና 9 ቀን፣ በአርሲ ሃገረስብከት ኮፈሌ ቆሬ ከተማ አይሻ ሰበካ ስድስት ምዕመናን ተገለዋል፡፡ ከመቶ በላይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን ተከታዬች ቤታቸው ተቃጥሎ ተሰደዋል፡፡ የማርያም ቤተከርስቲያን ተቃጥላለች፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- 1999 ዓ/ም ከመስከረም እስከ ጥቅምት አምስት፣  በሻሻ ዴዴሳና በሞናቶ  አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ተቃጥሎል፡፡ካህናትና ምዕመናን ታርደዋል፣ የምዕመናን መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- በ2011 ዓ/ም የጁዋር መሃመድ የተከብቢለሁ የ86 ሰዎች ሞት፣ ንብረት ውድመትና የሰብዓዊመብት ጥሰቶች ወንጀሎች ተፈፅመዋል፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- በ2012 ዓ/ም ሃጫሉ ሁንዴሳ 187 ሰዎች ተገድለዋል የኦነግቄሮ፣ ኦነግ ሸኔ፣ ኦፌኮ ቄሮ ድርጅታዊ የዘር ፍጅት ተዋናዬች በነፃና ገለልተኛ ኮሚሽን ተጣርቶ ለፍርድ ይቅረቡ!!!  በዚህ የህቡዕ መፈንቅለ መንግሥት  የፖለቲካ ሴራ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ምክንያት የተደገሠው የዘር ፍጅት ሁለት መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ሰዎች ሞት፣ ሁለት መቶ ሰዎች መቁሰል፣ ሁለት መቶ ሃምሳ መኪኖች መሰባበርና ሃያ መኪኖች መቃጠል፣ የአርባ  አምስት ፎቆች መቃጠል፣ ብዙ ሽህ ቤቶች መቃጠል፣ መሠረቱ በዘርና በኃይሞኖት የማንነት ላይ ያነጣጠረ ሲሆን፤ ወንጀለኞቹን ለፍርድ ማቅረብ የመንግሥት ሥራ ሲሆን በአመዛኙም የመከላከያ ሠራዊቱ፣ የፖሊስ ሠራዊቱና የፀጥታና የደህንነት መስሪያ ቤቱ ሠራተኞች እንዲሁም የክልል ሹማምንቶች የኦዴፓ/ብልፅግና ፓርቲ ካድሬዎች ሃላፊነትና ተጠያቂነት  መኖር አለበት እንላለን፡፡ ዓለም አቀፍ ትብብር በኢትዮጵያ መብት ሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶችንና ዲያስፖራውን አስተባብረው ለዓለም አቀፍ ወንጀለኛ ፍርድ ቤት (International Criminal Court)  በገለልተኛ ተቆማት ፍርድ እንዲሰጥ ማድረግ የጊዜው አንገብጋቢ ጥያቄ ነበር፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- በ2013 ዓ/ም በጥቅምት 9 ቀን እና ጥቅምት 13ቀን እንዲሁም  ጥቅምት 23 ቀን በኦሮሚያክልል በምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ጉሊሶ ወረዳ፣ ጋዋ ቃንቃ ቀበሌ በሰላማዊ ዜጎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት እስካሁን የ54 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ይታወሳል። የክልሉ ቃል አቀባይ ጥቃቱ የተፈጸመው በስብሰባ ስም በአንድ ቦታ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ ነው ብሏል። አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- ‹‹በኦሮሚያ ክልል ሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጉር ወረዳ ዳቢስ በሚባል ቀበሌ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 22 ሰዎች መገደላቸውን የዞኑ አስተዳዳሪና የአካባቢው ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገለፁ።  "በአካባቢው በሚኖሩ የአማራ ብሔር አባላት ላይ መሆኑን" የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ በቀለ ደቻሳ ይህንኑ አረጋግጠዋል።…"ጥቃቱን የፈጸሙት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው" ብለዋል፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

- ከየካቲት27 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ወለጋ በሆሮጉድሩ ወረዳ ውስጥ አማራዎች ላይ ማንነትን መሰረት ባደረጉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች ምክንያት ከ60 በላይ ወገኖቻችን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ታርደውና ተጨፍጭፈው ተገድለዋል፤ በአስር ሽህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተፈናቅለው ለችግር ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡ ንጹሃን  ዜጎች በኦህዴድ/ብልጽግና ይሁንታ እና በኦነግ ሸኔ አድራጊነት የዘር ማጥፋት ወንጀል ሰለባ ሆነዋል፡፡ አብዛኛዎቹ በማንነታቸው አማራዎች በመሆናቸው ነበር፡፡

የኮነሬል አብይ መንግሥት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያካሄደው የድሮውን ጥቃት ብዙ ዜጎች ተጨፍጭፈዋል በትግራይ ክልል (መቀሌ ከ23 እስከ 30 የአየር ጥቃት፣ተጎጋ ገበያ፣ አዲያቦ ከተማ፣ ደደቢት)በኦሮሚያ ክልል ወለጋ (ምዕራብ ሸዋ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ)፤ በአማራ ክልል ደሴ ጭፍራ ቤት፣ቆቦ፣ ባቲ፣ ወልዲያ፣ ስሪንቃ፣ ደላንታ ውርጌሳ፣ በረህት፣ መራቤቴ፣ ፍኖተሠላም፣ ደብረማርቆስ፣ ውኃ በር፣ ወይን ውኃ፣ ሞጣ ደጋዳሞት፣ ዓይና ቡጉና፣ ዘመሮ ወዘተ በገበያ ሥፍራ፣ በተፈናቃዬች ካንፕ ላይ፣ ወዘተ የቦንብ ጭፍጨፋ ተደርጎል፡፡ በአንድ ላይ ተነስቶ ሥርዓቱን ማስወገድ ጊዜው አሁን ነው፡፡

በ2016ዓ/ም በመራዊ  ከመቶ ኃምሳ እስከ ሁለት መቶ አማራዎች ከየቤታቸው ተወስደው በአደባባይ መንገድ ላይ በግፍ ተረሽነዋል፡፡ ዓለም አቀፍ ህብረተሰብ ድርጊቱን አውግዞል፡፡ የአሜሪካ፣ የእንግሊዝ፣ የካናዳ፣ የሲውድን መንግስቶች ድርጊቱን በማውገዝና ገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን ተቆቁሞ እንዲያጣራ አሳስበዋል፡፡

የአማራ ፋኖ የድል ጎዳና የጎንደር፣ የጎጃም፣ ወሎና የሸዋ አርበኞች ገድል፤ብአዴን ከአማራ ክልል ተነቅሎል! የአማራ ፋኖ ያፈረሰውን መንግሥታዊ መዋቅር ዳግም የማዋቀር፣ ህግና ሥርዓት ማስከበር፣ ግብርና ታክስ ሰብስበው ተማሪዎችን በትምህርት ቤቶች ማስተማር፣ የጤና ተቆማት ሥራ ማስቀጠል፣ የንግድና ገበያ ስርዓቱን ማስቀጠል፣ ወዘተ የፍትህና የዳኝነት ሥርዓት መገንባት፣ ዴሞክራሲያዊ ህዘባዊ አስተዳደር እንዲገነባ መጣር  የመሳሰሉት አድካሚ ሥራዎች ከፊቱ ይጠብቀዋል፡፡

አማራ ብአዴን፡- የብልፅግና ፓርቲ የተመሠረተው በቀሪዎቹ ዋነኞቹ ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ እና ደኢህዴን ፓርቲዎች  ሲሆኑ በአሁኑ ጊዜ በፋኖ የአማራ ህዝባዊ ትግል ከአማራ ክልላዊ መንግሥት መዋቅሮች ውስጥ 95 (ዘጠና አምስት) በመቶ የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን)  አባሎች ከክልሉ መንግሥት መዋቅር በህዝባዊው አመፅና እንቢተኛነት ተባረዋል፡፡ በዚህም መሠረት ብአዴን ተወካዬች ከፌዴሬሽን ምክር ቤትና የሕዝብ ተወካዬች ምክር ቤት አባልነት የህዝብ ውክልና የላቸውም፡፡ ብአዴን ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥታዊ መዋቅር ሳይወድ በግዱ ከሥልጣን መንበሩ ከአማራ ክልላዊ መንግሥት መዋቅራዊ አስተዳደሩ ተንኮታኩቶ ወድቆል፡፡

ለህዝብ ተወካዩች የፌዴራል ምክር ቤት ካሉት 547 መቀመጫ ወንበሮች  የአማራ ክልል 138 ወንበር በብአዴን የተያዘ ነበር ፋኖ የአማራ ህዝብ በትግሉ የብአዴን ተላላኪ ምስለኔዎች ነቅሎ ጥሎል፡፡ ለክልል ምክር ቤት ካሉት 1900 መቀመጫ ወንበሮች የአማራ ክልል 294 ወንበሮች በብአዴን የተያዙ ነበሩ ፋኖ የአማራ ህዝብ በትግሉ የብአዴንን ተላላኪ ምስለኔዎች ከክልሉ መንግሥታዊ መዋቅር አባሮ፣ የአማራ ፋኖ በድል ጎዳና በጎንደር፣ በጎጃም፣ ወሎና ሸዋ አርበኞች ህዝባዊ የሽግግር መንግሥት እየመሠረተ ህዝቡን በማስተዳደር ላይ ይገኛል፡፡   የአማራ  ሠላሳ ሚሊዮን ህዝብ በላይ በፌዴራልና ከህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት ውስጥ ህዝብ ያልወከላቸው አሻንጉሊት ተወካዬች ይገኛሉ፡፡ የአማራ ህዝብ የብአዴንን አንባገነን የጦር አበጋዞች መንግሥትን አስወግዶ በፋኖ አማራ ህዝባዊ ትግል ጋር ተቀናጅቶ የኢትዮጵያ ህዝብ ቀጣይ ህልውና የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት የአማራ ፋኖ ታላቅ ኃላፊነት ከፊቱ ይጠብቀዋል እንላለን፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ከአማራ ፋኖ ትግልን በመደገፍ የኦህዴድ ብልጽግና መንግሥትን የግፍ ዘረኛ አስተዳደር ነቅሎ በመጣል የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት በተስፋ ይጠብቃል፡፡

የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ትግል አፈፃፀም ፋኖ ባንኮች አይዘርፍም፣ የህዝብ ንብረት አይወስድም፣ ሴቶች አይደፍርም፣ ስብዓዊ መብቶች አይጥስም፣ የማንነት መብትን አይጥስም፣ የእስረኞች መብትን በዓለም አቀፍ ህግ መሠረት በማክበር ያሳየው ሥነ-ሥርዓት በዓለም ተመስክሮለታል፡፡ የአማራ ብሔርተኛነት በጎንደር፣ በጎጃም፣ በወሎና ሸዋ በህዝባዊ እንቢተኛነትና ህዝባዊ ተጋድሎ እያደገ ሄዶ ወደ አንድ የአማራ ፋኖ እዝ  ወታደራዊ ኃይልና አመራር  ያመራሉ ብሎ የአማራ ህዝብ ይጠብቃል፡፡ የአማራ ፋኖ ወደ አንድ እዝ ያልተካተቱ ፋኖዋች በፍቃዳቸው ወደ ውህደቱ እስኪገቡ ድረስ በትግሥት በመጠበቅ ከአንድ የአማራ ዕዝ ጋር ተናበው እንዲሠሩ ማድረግ ይጠበቃል፡፡ በተመሳሳይ የአማራ ብሔርተኛነት አንድ ወጥ የፖለቲካ አመራር  የሚሠጥ የአማራ ብሔርተኛነት የፖለቲካ ፓርቲ መመሥረት ይገባል፡፡ በመቀጠልም ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ የሽግግር መንግስት መመስረትና በጋራ ሃገር አቀፍ ፍኖተ-ካርታ መቅረፅ፤ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ጉዳይ ያካተተ ማኒፌስቶ ማውጣት  ይጠበቅባቸዋል፡፡ የፋኖ አማራ ብአዴንን ከስልጣን አውርዶ ጥሎል፣ የኦሮሞ ህዝብ ኦህዴድን አሽቀንጥሮ ይጣል፣ የትግራይ ህዝብ ህወሓትን አሽቀንጠሮ ከሥልጣኑ ይጣል እንላለን፡፡ ህዝባዊ እንቢተኛነትና ህዝባዊ ተጋድሎ ይቀጣጠል!!! የኢትዮጵያ ህዝብ ተባብረህ የኮነሬል አብይ አህመድን መንግሥት ገርስሰህ ጣል እንላለን፡፡

በአማራ ከልል የተጣለው ዳግማዊ ‹የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ!!!›

‹‹በመሣሪያ የመጣ፣ በመሣያ ይወጣ!!!›› ‹‹ በኃይል የመጣ፣ በኃይል ይወጣ!!!››‹‹ከአጋዘን በፊት ማንኛውም ሰው በህይወት የመኖር መብት አለውና!!!›› የኮነሬል አብይ አህመድ ኦህዴድ ብልፅግና  መንግሥት፣ ህወሓት ኢህአዴግ፣ ‹ብልፅግና ሸኔ› ኦነግ ሸኔና ኦነግ በዓለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት (International Criminal Court) መቅረባቸው አይቀርም!!! እንደ ህወሓት የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ደኢህዴን ወንጀለኞች ለፍርድ ይቀርባሉ፡፡

የአውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የአሜሪካ፣ የእንግዚዝ፣ የካናዳ፣ በአጠቃላይ የአለም ህብረተሰብ በተደጋጋሚ በኦሮሚያ ክልል፣ በወለጋ ዞን እና በቤኒሻንጉል ክልል፣ መተከል ዞን፣ በቅርቡም በጎጃም መራዊ በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ተከታታይ የዘር ማፅዳት ወንጀል የኦነግ፣ ኦነግ ሽኔ እና ሌሎች ታጣቂ ጏይሎች ወንጀል በማስረጃ አቅርቦ ማስቀጣት የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው፡፡ የዘርና የኃይማኖት ፍጅቱንና ጥቃቱን ባለማስቆም የክልሎቹ መንግስታት እና የፌደራል መንግስቱም እኩል ተጠያቂዎች ለፍርድ የሚቀርቡበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም፡፡ የአገር ውስጥና የዲያስፖራው ትግል በዘላቂነት ከቀጠለ የኮነሬል አብይ አህመድ እድሜ እንደሚያጥር ምንም ጥርጥር የለም፡፡

የአለም ህብረተሰብ ዓይን ኢትዮጵያ ዜጎች ላይ ነው ለአንዴና ለሁሌ በነፃነት በህይወት የመኖር መብታችንን ለማስከበር ጊዜው አሁን ነው!!!! አራጆቻችንን ለዓለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት መስጠት ታሪካዊ ሃላፊነት አለብን፡፡  ፌዴራል መንግሥት ብልፅግና ፓርቲና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት መር ሽብርተኛነትን አጋልጦ መስጠት ጊዜው አሁን ነው!!! የኦነግ ሠራዊት ኦነግ ሸኔ በህዝብ ላይ ጥቃት ሲፈፅም የአማራ ፋኖ በሠላም አሰከባሪ ኃይል ሆኖ  በክልሎች የሚፈፀም ግድያን በጋራ መቅረፍ ይጠበቅበታል አጋርነቱንም በተግባር ማሳወቅ ይጠበቅበታል፡፡ የኦነግ ተረኞቹ አራጆች የሚወገዱት ጊዜው አሁን ነው!!! በተመሳሳይ ሁኔታም ትግራይ ውስጥ በንጹሐን ዜጎች ላይ ለደረሰው እና እየደረሰ ላለው አሰቃቂ ጉዳት፤ በሰሜን ዕዝ እና በማይካድራ የደረሱትን እጅግ አሰቃቂ ጥቃቶች ጨምሮ ተጠያቂ መሆን የሚገባቸው፤በአንደኛ ደረጃ ህውሃት እና አመራሮቹ፤ በተለይም የክልሉ ም/ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጺዮን እና ካቢኔያቸው፤ ጦርነቱን ከመለኮስ ጀምሮ ለደረሰው ጠቅላላ ጉዳት፣በሁለተኛ ደረጃ፣ ገዥው ፖርቲ ብልጽግና እና አመራሮቹ፤ በዋነኝነት ጠ/ሚንስትር አብይ አህመድ እና ካቢኔያቸው፤ ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ደኢህዴድ ካቢኔቸው ጦርነቱ ተጠናቋል ከተባለበት ጊዜ አንስቶ በንጹሀን ዜጎች ላይ ለደረሰው ሰቆቃ፣በሦስተኛ ደረጃ የኤርትራ መንግስት፤ በተለይም ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፎወርቂ፤ በወታደሮቻቸው ለተፈጸመው ዝርፊያ፣ ግድያ እና አስገድዶ መድፈር፤ በእነዚህ አካላት በአንድ ወይ በሌላ መልኩ ለተፈጸሙት የዘር ማፅዳት ወንጀል፣ የመብት ጥሰቶች፣ ጭፍጨፋዎች እና ግጭቶች፤ ማድረግ የማይገባቸውን በማድረግ ይሁን፤ ማድረግ የሚገባቸውን ባለማድረግ ተጠያቂ የሆኑትን ሁሉ በገለልተኛ አካል በዓለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንዲጣራ ማድረግ ለኢትዮጵያ ህዘብ  ጊዜው አሁን ነው!!! ይሄን ፍርድ በተግባር ማስፈፀም የሚችለው የአማራ ፋኖና አጋሮቹ ብሄር ብሔረሰቦች ከጎኑ በማድረግ ነው እንላለን፡፡ የታሪክ አደራ ነውና!!!

ምንጭ

(1) የልፁል ራስ መኮንን ዜና መዋዕል በግራ ጌታ ኃይለ ጊርጊስ ዘ-ሐረር የተሰናዳ (ከግዕዝ 1938ዓ/ም ተፃፈ ወደ አማርኛ ሰኔ 2015 ዓ/ም የተተረጎመ ) ገፅ 124 የዳግማዊ ምኒልክ የአዋጅ ቃል ለአማራ ፋኖ
https://amharic.zehabesha.com/archives/188862

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...