Saturday, April 13, 2024

የፋኖ ናሁሰናይ የመጨረሻ ትንቅንቅ | አብይ አስቸኳይ ስብሰባ አፈትልኮ ወጣ | ለብልጽግና ባለስልጣናትና ለአዲስ አበባ ህዝብ የቀረበ ጥሪ |
https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD

 

 

 

https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf

 

https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=PxgZ5SzamPTF_cH2

አብይ አስቸኳይ ስብሰባ አፈትልኮ ወጣ |

https://youtu.be/Nnlsd7FgoEE?si=c72IiPi4HWIdEkZz

መሀል ቦሌ ላይ በተገደሉት የፋኖ ታጣቂዎች ዙሪያ ያልተጠበቀ አዲስ መረጃ ወጣ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189722
የፋኖ ናሁሰናይ የመጨረሻ ትንቅንቅ | አብይ አስቸኳይ ስብሰባ አፈትልኮ ወጣ | ለብልጽግና ባለስልጣናትና ለአዲስ አበባ ህዝብ የቀረበ ጥሪ |
https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD

 

 

 

https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf

 

https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=PxgZ5SzamPTF_cH2

አብይ አስቸኳይ ስብሰባ አፈትልኮ ወጣ |

https://youtu.be/Nnlsd7FgoEE?si=c72IiPi4HWIdEkZz

መሀል ቦሌ ላይ በተገደሉት የፋኖ ታጣቂዎች ዙሪያ ያልተጠበቀ አዲስ መረጃ ወጣ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189722

Friday, April 12, 2024

የፋኖ ናሁሰናይ የመጨረሻ ትንቅንቅ | አብይ አስቸኳይ ስብሰባ አፈትልኮ ወጣ |
https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf

 

https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=PxgZ5SzamPTF_cH2

አብይ አስቸኳይ ስብሰባ አፈትልኮ ወጣ |

https://youtu.be/Nnlsd7FgoEE?si=c72IiPi4HWIdEkZz

መሀል ቦሌ ላይ በተገደሉት የፋኖ ታጣቂዎች ዙሪያ ያልተጠበቀ አዲስ መረጃ ወጣ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189722
https://youtu.be/pnCOZ5p4Dzw?si=RhzARBzIChdQnCtC

ፋኖ አዲስ አበባ ገባ ከባድ ተኩስ ትንቅንቅ ናሆ ሰናይ ጀግናችን ዳግማዊ ቴድሮስ አዲስ አበባን አንቀጠቀጣት
https://amharic.zehabesha.com/archives/189719
https://youtu.be/pnCOZ5p4Dzw?si=RhzARBzIChdQnCtC

ፋኖ አዲስ አበባ ገባ ከባድ ተኩስ ትንቅንቅ ናሆ ሰናይ ጀግናችን ዳግማዊ ቴድሮስ አዲስ አበባን አንቀጠቀጣት
https://amharic.zehabesha.com/archives/189719

Thursday, April 11, 2024

ፕሬዚዳንቱ ወደ አሜሪካ ሸሹ | ሁለት ጀነራሎች ሲጠጡ በጎንደር ተቀነደሹ | አዲስ አበባ የብልፅግና ባለስልጣን ተገደለ | ፋኖ እና ወርቁ አይተነው |
https://youtu.be/duLoETKFdvQ?si=QoYjQDGU1s6Sma5e

ሁለት ጀነራሎች ሲጠጡ በጎንደር ተቀነደሹ | አዲስ አበባ የብልፅግና ባለስልጣን ተገደለ | ፋኖ እና ወርቁ አይተነው |

https://youtu.be/fwjCVTRu0rw?si=wocBlY8YH0Czy-5m

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189713
ፕሬዚዳንቱ ወደ አሜሪካ ሸሹ | ሁለት ጀነራሎች ሲጠጡ በጎንደር ተቀነደሹ | አዲስ አበባ የብልፅግና ባለስልጣን ተገደለ | ፋኖ እና ወርቁ አይተነው |
https://youtu.be/duLoETKFdvQ?si=QoYjQDGU1s6Sma5e

ሁለት ጀነራሎች ሲጠጡ በጎንደር ተቀነደሹ | አዲስ አበባ የብልፅግና ባለስልጣን ተገደለ | ፋኖ እና ወርቁ አይተነው |

https://youtu.be/fwjCVTRu0rw?si=wocBlY8YH0Czy-5m

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189713

Wednesday, April 10, 2024

አሁን ባህርዳር ከባድ ውጊያ ተደረገ | "ዘመነ ካሴ ከኢሳያሰ ጋር እየሰራ ነው" ጀነራል አበባው ' 4 ባለስልጣናት ተገደሉ |
https://youtu.be/YaLxLeg7M6o?si=Jo7Kd8Ilbu33M0_V

አሁን ባህርዳር ከባድ ውጊያ ተደረገ | "ዘመነ ካሴ ከኢሳያሰ ጋር እየሰራ ነው" ጀነራል አበባው

 

https://youtu.be/12YW2iYxeKA?si=NXmtoEp1aJb1I2Dm
https://amharic.zehabesha.com/archives/189709
አሁን ባህርዳር ከባድ ውጊያ ተደረገ | "ዘመነ ካሴ ከኢሳያሰ ጋር እየሰራ ነው" ጀነራል አበባው ' 4 ባለስልጣናት ተገደሉ |
https://youtu.be/YaLxLeg7M6o?si=Jo7Kd8Ilbu33M0_V

አሁን ባህርዳር ከባድ ውጊያ ተደረገ | "ዘመነ ካሴ ከኢሳያሰ ጋር እየሰራ ነው" ጀነራል አበባው

 

https://youtu.be/12YW2iYxeKA?si=NXmtoEp1aJb1I2Dm
https://amharic.zehabesha.com/archives/189709

Tuesday, April 9, 2024

እራሳቸው ፈተና የወደቁ፤ ፈተና ፈታኞች !!  (አሥራደው ከካናዳ)
ምስሎች : ከባንክሲ የመንገድ ላይ የጥበብ ሥራዎች የተዋስኳቸው::

መንደርደርያ :

- « The only thing we have to fear is fear itself. »        Franklin D. Roosevelt

«  ልንፈራው የሚገባ ነገር ቢኖር፤ እራሱን ፍራቻን ብቻ ነው »   ፍራንክሊን ሩዝቬልት

- « Only when we are no longer afraid do we begin to live »    Dorothy Thompson

« ፍራቻን ስናስወግድ ብቻ ነው መኖር የምንጀምረው »

- « Hate is the consequence of fear; we fear something before we hate it...» Cyril Connolly

« ጥላቻ የፍርሃት ውጤት ነው፤ ከመጥላታችን በፊት፤  የሆነ ነገር እንፈራለን (ሌላውን መፍራት እንጀምራለን)… »    ሲሪል ኮኖሊ

 

መግቢያ :

ለመሆኑ የፈተና ዓላማና ግቡ ምንድነው ?!  ፈተናን ማን ለማን ይሰጣል ?!  የፈተና መለኪያ መሳሪያዎች ምንድናቸው ?!  ፈተና መቼና እንዴት ይሰጣል ? ፈተናውን ለማለፍ፤ መስፈርቶቹ ምንድናቸው ?!  መስፈርቶቹስ እንዴትና በማን ይወሰናሉ፤ በፈታኝና ተፈታኝ መሃከል ያለው ግኑኝነት ምን መሆን አለበት……….. ወዘተ.

በመጀመሪያ አንድ አገር፤ ከሁሉም አገራዊ ጉዳዮች በማስቀደም፤ የትምህርት ፍልስፍና (Educational Philosophy) ሊኖራት ይገባል::

ከዚያም፤ የትምህርት ፍልስፍናዋን  (Educational Philosophy) በሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ ቀመሮች ላይ በመንተራስ፤ የህዝቧን ታሪካዊ ፈለግ፤ የማህረሰባዊ ትስስርና የአኗኗር ልምድ በማጤን፤ ጤናማ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት መቅረጽ (መንደፍ) ይኖርባታል ::

በአንጻሩ በአገራችን ኢትዮጵያ፤ ቀደም ብሎ ህወሃት፤ አሁን (የኦህዴድ/ኦነግ) ጥምር ብልጽግና ተብዬ የነደፉት ሥርዓተ ትምህርት፤ ሆን ተብሎ ትውልድን የአይምሮ ሰንካላ አድርጎ የሚገድል፤ አገርን አመክኖ ለማፍረስ የተወጠነ በመሆኑ፤ ይኸው አሁን ያለንበት አገራዊ የትምህርትና የትውልድ ውድቀት ላይ ደርሰናል ::

እነዚህ እራሳቸው የኢትዮጵያዊነት ፈተናን፤ ተፈትነው ደጋግመው የወደቁ፤ የዘረኝነት፤ የጎሠኝነትና የጥላቻ ፖለቲካ ሰባኪዎች፤ ለአዲስ አበባ ህዝብ፤ ብሎም ለመላው የኢትዮጵያ፤ ህዝብ፤ ፈተና የመስጠት የዕውቀት ችሎታ፤ የሞራል ብቃትና  የሰብአዊነት ሚዛን የማይደፉ፤ አርቆ ለማስተዋል የማይችሉ፤ ዳፍንታሞች በመሆናቸው፤ ህዝብ በአንድላይ በመነሳት በቃ ሊላቸው ይገባል ::

የአዲስ አበባ ሕዝብ ! ብሎም  መላው የኢትዮጵያ  ሕዝብ ሆይ ! !

- እንዴት ውርደትን አሜን ብለህ ለመቀበል፤ እነዚህ የዘር ፖለቲከኞች የሚሰጡህን ፈተና ለመፈተን ትሰለፋለህ ??!!

- በዘረኝነትና በጎሠኝነት፤ ከዜሮ በታች በእጅጉ የዘቀጡ ሲያዋርዱህ፤ ጥቃቱ አንገፍግፎህ በቃ ! የምትላቸው መቼ ነው ?!

- ለመሆኑ: ከዜሮ በታች እስከ ስንት ዲግሪ ሴንትግሬድ ድረስ: ሲያዋርዱህ ነው ጥቃቱ የሚያንገፈግፍህ ?!

- መቼነው እነዚህ አርቆ ለማስተዋል የማይችሉ፤ የፖለቲካ ዳፍንታሞችን፤ ከጀርባህ ላይ አሽቀንጥረህ በመጣል ነፃ ህዝብ የምትሆነው ?!

 

- የአዲስ አበባ : ብሎም  መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ ! ውርደትህ የሚያበቃው፤ በህዝባዊ እምቢተኝነት መሆኑን በመረዳት፤ ተባብረህ በአንድነት ተነሳ !  ያለ ፍላጎትህ በግድ የጫኑብህን፤ የዘርና የጎሣ ፖለቲካ፤ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከትከሻህ ላይ አሽቀንጥረህ ጣል !!

ማሳረጊያ

በሰው ልጆች የአኗኗር ሂደት ውስጥ፤ ሦስት ዓይነት የማህበራዊ ግንኙነቶች ያሉ ሲሆን እነሱም :

- የእኔየእኔ ነው

- 2. የእኔ የእኔ ነው፤ ያንተም የእኔ ነው

- 3. የእኔ ያንተ ነው፤ ያንተም የእኔ ነው የሚሉት ሲሆኑ፤

ከነዚህ ውስጥ፤ በቁጥር 1 እና 2 ያሉት ሁለቱ፤ ጤናማ ያልሆኑ ግንኙነቶች ሲሆኑ፤

አንዱ ብቻ፤ በቁጥር 3 ያለው፤ ለሰው ልጆች ጤናማና፤ አብሮ በጋራ የመኖር መሠረት የሆነ ሲሆን፤ እሱም: የእኔ ያንተ ነው፤ ያንተም የእኔ ነው የሚለው : የጋርዮሽና የመተሳሰብ ማህበራዊ ግንኙነት ነው ::

ህወሃት ለ27 ዓመታት፤ ያሰፈነው ሥርዓት፤ « የእኔ የእኔ ነው፤ ያንተም የእኔ ነው » የሚለው የዘራፊነት፤ የሌብነትና የንቅዘት (የሙስና) ሥርዓት ነበር :: ህወሃት ጠፍጥፎ የፈጠራቸው አሽከሮቹ የ(ኦህዴድ/ኦነግ)ጥምር ብልጽግና ተብዬዎች፤ ከጌቶቻቸው ውድቀት፤ ምንም መማር የማይችሉ ደንቆሮዎች በመሆናቸው፤ ያንኑ የፈጣሪያቸው የህወሃትን የቀማኛ ሥርዓት በከፋ መልኩ « ሁንዱማ ኬኛ በማለት » መቀጠሉን መርጠዋል::

የዘረኝነትና የጎሠኝነት ሥርዓታቸውን ዕድሜ ለማራዘም፤ በገዛ ወገኖቻቸው ላይ፤ በድሮንና በጦር አውሮፕላኖች፤ ቦንብ የሚያዘንቡ ህሊና ቢሶች፤ የኢትዮጵያን ህዝብ፤ የኢትዮጵያዊነት ካባውን አውልቀው፤ የዘረኝነትና የጎሠኝነት ቡቱቱ ለማልበስ፤ የሚያደርጉትን ደባና ሸፍጥ፤ ሕዝብ በአንድነት በመነሳት አምቢ ሊላቸው ይገባል ::

ዘረኝነትና ጎሠኝነትን እያራገቡ፤ እኛን እርስ በርሳችን በማባላት፤ እነሱ በሌብነት፤ በንቅዘት (በሙስና) ተሰማርተው፤ የአገር ሃብት እየዘረፉ ያዘርፋሉ ::

አይምሯቸው በዘረኝነት በመበከሉ፤ አርቆ የማሰብ ችሎታቸው ተገድቦ፤ የገዛ ወገኖቻቸውን የሚያርዱ፤ የሚያፈናቅሉና እንዲሰደዱ የሚያደርጉ፤ በሌብነት የሰለጠኑ፤ የአገር ሃብት ዘራፊዎች፤ በንቅዘት ወይም በሙስና ማጥ ውስጥ ተዘፍቀው፤ አጉል አጉል የሚሸቱ ነቀዞች፤ ፍትህ ተረግጦ፤ ዜጎች ያለ ፍርድ ወህኒ ቤት እየታጎሩ፤ ዜጎችን በየቦታው በጠራራ ፀሓይ ፤ በጥይት የሚገሉ ወንጀለኞች ፤ የድሃ ወገኖቻችንን ቤት እያፈረሱ፤ ሜዳ ላይ የሚበትኑ፤ ዜጎችን እያፈኑ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ከድሃው ህዝብ የሚጠይቁ፤ የጠራራ ፀሐይ አጋሚዶዎችን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቃ ! ሊላቸው ይገባል ::

ጎበዝ ! ልብ ከሸፈተ ከተማም ጫካ ነው !! የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤ ፋኖ ይመጣል እያላችሁ ከመጠበቅ፤ እራሳችሁ ፋኖ ሁኑና፤ ትግሉን በመቀላቀል፤ የድሉን ቀን እናፋጥን !! የመከራውን ቀን እናሳጥር !!

አጠያፊዎችን መጠየፍ ወንጀል አይደለም !!

ፍርሃት፤ ዝምታና አድር ባይነት ወንጀል ነው!!

ሳይዘገይ በአንድነት በመነሳት ነፃ ህዝብ እንሁን !!

የፈራ ይመለስ !! ድል ለፋኖ !!

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

በሥር ነቀል ለውጥ፤ ወደ አዲስ ተስፋ !!

ነፃነት፤ እኩልነትና ወንድማማችነት ይለምልም !!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይባርክ !!

መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ( 06/04/2024 ) እኤአ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189681
የጎጃም ዕዝ ጥብቅ የተሰጠ መግለጫ
https://youtu.be/RZ5yjxRwLLE?si=GF-IfTw7cfWbRua-

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከአርበኛ ዘመነ ካሴ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ እና መልዕክት
https://amharic.zehabesha.com/archives/189704
ጎጃም የአብይ አህመድ ሰራዊት ተደመሰሰ ሻለቃ ዝናቡ ለአብይ መርዶ ላከ | "ደሴ እና ኮምቦልቻን እንቆጣጠራለን" ፋኖ ወልዲያ ቦንብ ፈነዳ ጀግናው ፋኖ ተሰዋ | ባህርዳር ተናወጠች
https://youtu.be/1VE7uLJ8b6U?si=92d3jdNt0jZa5qmd

"ደሴ እና ኮምቦልቻን እንቆጣጠራለን" ፋኖ ወልዲያ ቦንብ ፈነዳ ጀግናው ፋኖ ተሰዋ | ባህርዳር ተናወጠች

https://youtu.be/RZYORCSucVU?si=WY4IyJVfw-IaXcPz

 ጎጃም የአብይ አህመድ ሰራዊት ተደመሰሰ ሻለቃ ዝናቡ ለአብይ መርዶ ላከ | ህዝቡ ፋኖን ደግፎ አብይን ተቃውሞ አደባባይ ወጣ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189676
ጎጃም የአብይ አህመድ ሰራዊት ተደመሰሰ ሻለቃ ዝናቡ ለአብይ መርዶ ላከ | "ደሴ እና ኮምቦልቻን እንቆጣጠራለን" ፋኖ ወልዲያ ቦንብ ፈነዳ ጀግናው ፋኖ ተሰዋ | ባህርዳር ተናወጠች
https://youtu.be/1VE7uLJ8b6U?si=92d3jdNt0jZa5qmd

"ደሴ እና ኮምቦልቻን እንቆጣጠራለን" ፋኖ ወልዲያ ቦንብ ፈነዳ ጀግናው ፋኖ ተሰዋ | ባህርዳር ተናወጠች

https://youtu.be/RZYORCSucVU?si=WY4IyJVfw-IaXcPz

 ጎጃም የአብይ አህመድ ሰራዊት ተደመሰሰ ሻለቃ ዝናቡ ለአብይ መርዶ ላከ | ህዝቡ ፋኖን ደግፎ አብይን ተቃውሞ አደባባይ ወጣ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189676

Monday, April 8, 2024

https://youtu.be/OJgauKCzjkA?si=CFYM-Cfz68bxP5nX

ጄነራል አበባው ጦር ሜዳ ጉድ ሆነ | ኮረኔል ደመቀ ዘውዱ ኑና ግጠሙን አሉ | ጎንደር የአብይ ሰራዊት ጉድ ሆነ ተደመሰሰ ሸዋ ታላቅ ድል
https://amharic.zehabesha.com/archives/189671
https://youtu.be/OJgauKCzjkA?si=CFYM-Cfz68bxP5nX

ጄነራል አበባው ጦር ሜዳ ጉድ ሆነ | ኮረኔል ደመቀ ዘውዱ ኑና ግጠሙን አሉ | ጎንደር የአብይ ሰራዊት ጉድ ሆነ ተደመሰሰ ሸዋ ታላቅ ድል
https://amharic.zehabesha.com/archives/189671

Sunday, April 7, 2024

https://youtu.be/tUxw6R_eMJU?si=zYSGzFlSFQUZKUlJ

ፈጥነን እንተባበር የአብይ አገዛዝ ጸሐይ እየጠለቀች ነው | Hiber Radio with Dr Aklog
https://amharic.zehabesha.com/archives/189658
https://youtu.be/tUxw6R_eMJU?si=zYSGzFlSFQUZKUlJ

ፈጥነን እንተባበር የአብይ አገዛዝ ጸሐይ እየጠለቀች ነው | Hiber Radio with Dr Aklog
https://amharic.zehabesha.com/archives/189658

Saturday, April 6, 2024

አቶ ክርስቲያን ታደለ ለፍርድ ቤት ያቀረቡት አቤቱታ | ከአስክሬን ጋር እንድናድር ተደርገናል። በአማራ ማንነታችን በጸያፍ ስድብ ተሰድበናል። ታግተን ነው ያለነው'' አቶ ዮሐንስ ቧያለው | ከኮማንደር አሰግድ መኮንን የአማራ ፋኖ በሸዋ አዛዥ
https://youtu.be/sO3jcvOBoQY?si=4wLd1YfzpJZIswcA

የኢትዮታይምስ የዕለቱ ዜና |የነክርስቲያን የፍ/ቤት ዉሎ|ንግድ ባንክ በህግ ይጠየቃል?|የኦነግ መግለጫ|የኮማንድ ፖስቱ ምላሽ

 

https://youtu.be/eNtnLGoC-sU?si=0G6a4qKC-Ifkp0WS

https://youtu.be/8sUVYh-fVnc?si=Bl0y6xtX9Gh4_gwD

 

https://youtu.be/p_qOWzxH9tQ?si=wrwCiux-Sv77eLbL

 

 

 ከኮማንደር አሰግድ መኮንን የአማራ ፋኖ በሸዋ አዛዥ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189652
ከግሸን ገዳም የተላከልኝ ቪዲዮ | የአብይ ወታደር አሳፋር ተግባር | ቆይ ምን ይሻላል ??
https://youtu.be/Pff5z7IVZH8?si=NjxDqgAcWTdQJkd9

በግሸን ማርያም የሚሰማው እጅግ ይዘግንናል፡፡ የአብይ አህመድ ወታደሮች የቆረቡ መነኮሳት እንስቶችን በቡድን ሆነው መድፈራቸውን የአይን እማኞች ከስፍራው ዘግበዋል፡፡ ይሄ በታሪክ እንዴት እንደሚመዘገብ አላውቅም፡፡በአህመድ ግራኝ ሳይሆን በአብይ አህመድ የተደጸመ ነው፡፡ ደብረ ኤልያስ ገዳም ከ600 መቶ በላይ መነኮሳት ሲታረዱ ዝም አልን፡፡ የኦሮምያ ቤተ ክህነት በሚል አያሌ ምዕመናን ሲታረዱና ቤተ ክርስትያናት ሲቃጠሉ ዝም፤ ዝቋላ ገዳም አባቶችን ጨምሮ በብዙ ገዳማትና የአብነት ት/ቤቶች አማኞች ሲገደሉ ዝም፤ ዛሬ ተራው የግሸን ማርያም ሆኗል፡፡ እስከመቼ ዝም?  በእውነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አማኝ ህዝብ እውነት አማኝ ክርስትያን ቢሆን በአንድ ቀን አመጽ በደሉ ይቆም ነበር፡፡ ህዝበ ክርስትያኒ ቢነሳ አብይ አህመድ አንድ ቀን በአራት ኪሎ አይውልም ነበር፡፡ ቤተ ክርስትያኒቱ የደለበ አቅም አላት፤ተቋማትም አሏት፤ በእውነት ቢሰራ ማህበረ ቅዱሳን የሚባለው ተቋም ብቻ ይበቃ ነበር፡፡ ይሁን እንጅ አንድም የቤተ ክርስትያኒቱ ተቋማት ችግሩን በድፍረት ሲታገሉ አይታይም፡፡ ለምን?

ኦርቶዶክስ አማኝነት ነጣላ ለብሶ ቤተክርስትያን መሄድ ወይም ግዜው እንዳመጣው በተክሊል ሰርግ ማድረግ ወይም በበዓላት ቀን በሃበሻ ልብስ ደምቆ መታየት አይደለም፡፡ ኦርቶዶክስ እምነቷ ጸንቶ የኖረው በመራራ ትግል ነው፡፡ በስንፍና የሚገኝ ሃይማኖትም ይሁን እምነት አይኖርም፡፡ አባቶችም ጭምር ክርስትናው የገባቸው አይመስሉም፡፡

መፍትሄው ምን ይሁን? መንግስት መምራት ሲያቅተው የፋኖ ትግል እንደተጀመረ ሁሉ ሲኖዶስ ቤተክርትታኒቱን መምራት ስላልቻለ በካህናት የሚመራ የታችኛው መዋቅር መነሳት አለበት፡፡ ቤተ ክርትያኒቱን በትጋት የሚያገለግሉት ካህናትና ዲያቆናት አመራሩን ከጳጳሳት በመረከብ ለህዝቡ ቅርብ የሆኑት ካህናት፤ ዲያቆናትና የአብነት ተማሪዎች ህዝቡን ይዘው መታገለ አለባቸው፡፡ ጳጳሳቱ ከአዲስ አበባ ቁጭ ብለው ህዝቡን ሊታደጉት አልቻሉም፡፡ እንዴውም የችግሩ አካል ሆነዋል፡፡ታቦት ተወርውሮ ሲጣል ዝም የሚል ጳጳስ አባት አይደለም፡፡ አሁን የቀረው እንደተባለው ፓትርያርኩ መታረድ ብቻ ነው፡፡ አያድርገው እንጅ ፓትርያርኩን አንድ ቢያደርጓቸው የሚቆጣ የቤተክርስትያኒቱ ተቋም የለም፡፡ በቤተ ክርስትያኒቱና በአማኞች ላይ ያልተሰማ ግፍ የለም፡፡ አባቶች ለምን ዝም ይላሉ? የቤተ ክርስትያኒቱ ተቋማትስ የት አሉ? የቄርሎስና የዮሃንስ አፈወርቅ ልጆች የት አሉ? በበዓላት ላይ ደምቆ መታየት፤በጣዕመ ዜማ እየዘመሩ አምላክን ማመስገን የሚቻለው ቤተ ክርስትያኒቱ ስትኖር ብቻ ነው፡፡ ይሄ ትውልድ እመንቱን ከእጁ እየተነጠቀ መሆኑን ማወቅ፤ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡አማኝ የሆነ ሁሉ ሰይፉን ይዞ መታገል አለበት፡፡

--

Kaleb Menberu
https://amharic.zehabesha.com/archives/189645

Friday, April 5, 2024

አሸባሪው ጳጳሳት በለንደን ተዋረዱ | አርበኛ መሳፍንት ኮረኔሉን አደባዩት | አብይ 2 የአማራ ተወላጅ ግል ጠባቂዎችን አባረረ | የጀነራሉ ምስጢር ባለሥልጣኗ ውሽማው ታወቀች
https://youtu.be/QNu0Xk_M-EE?si=hD4VlkzbThaNitob

 

https://youtu.be/pXmbJr5RIFY?si=o0Z46_0tmymHtP9H

አርበኛ መሳፍንት ኮረኔሉን አደባዩት | አብይ 2 የአማራ ተወላጅ ግል ጠባቂዎችን አባረረ |

https://youtu.be/E_qLn3EiWW4?si=pKZ93NEpNTwh0KEe

 

https://youtu.be/lqb11gPzXr0?si=cjHn1RcLKtUnTJWx

የጀነራሉ ምስጢርባለሥልጣኗ ውሽማው ታወቀች
https://amharic.zehabesha.com/archives/189630
አሸባሪው ጳጳሳት በለንደን ተዋረዱ | አርበኛ መሳፍንት ኮረኔሉን አደባዩት | አብይ 2 የአማራ ተወላጅ ግል ጠባቂዎችን አባረረ | የጀነራሉ ምስጢር ባለሥልጣኗ ውሽማው ታወቀች
https://youtu.be/QNu0Xk_M-EE?si=hD4VlkzbThaNitob

 

https://youtu.be/pXmbJr5RIFY?si=o0Z46_0tmymHtP9H

አርበኛ መሳፍንት ኮረኔሉን አደባዩት | አብይ 2 የአማራ ተወላጅ ግል ጠባቂዎችን አባረረ |

https://youtu.be/E_qLn3EiWW4?si=pKZ93NEpNTwh0KEe

 

https://youtu.be/lqb11gPzXr0?si=cjHn1RcLKtUnTJWx

የጀነራሉ ምስጢርባለሥልጣኗ ውሽማው ታወቀች
https://amharic.zehabesha.com/archives/189630

Thursday, April 4, 2024

ጥቁር ቀን: የከሸፈው የበአለ ሲመት ዕቅድ...
1፦ ከመጋቢት 7 ጀምሮ በዐማራ ፋኖ ላይ ከፍተኛ ጦርነት በመክፈት በአለ ሲመቱን በድል አሸብርቆ ለማክበር አቅዶ ወደ ሥራ ለመግባት ሲሰናዳ አባደፋር ፋኖም ይቺን ተረድቶ ከመጋቢት 5 ጀምሮ የአራጁን ሠራዊት ኢሬቻውን አብልቶት አረፈው። በዚህ ላይ ሜጀር ጀነራል ውባንተ ተሰዋና የባሰ የዐማራ 4ቱም ክፍላተ ሀገራት ተጣምረው አንድ ሆነው አፈር ደቼ አስግጠው አዋረዱት። ዐማራን በድሮን ጨፍጭፎ በአለ ሲመቱን ኦሮሞን እያስጨፈረ ሊውል የነበረው ዕቅድ በዘመቻ ውብአንተ ውኃ በላበት

2፦ እንደ ኢትዮጵያ መሪ አክት በማድረግ ከቢሮው ወጥቶ በየክልሉ እየሄደ በሕዝባዊ ውይይት ስም ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ የጉም ተስፋ ለማስጨበጥም አሁን የሚመራው ክልል አዲስ አበባ ብቻ በመቅረቱ አልተመቸውም። እንዲያም ሆኖ በቤተ መንግሥቱ መሰብሰቡ አልቀረም። ጴንጤ፣ እስላሞች፣ ሴቶች፣ የክልል ተወካዮች፣ ባለሀብቶች ሁሉም ተመርጠው ሄደው እሱ እንደሚፈልገው ቢሆኑለትም በመሃል ኦርቶዶክስ ጣልቃ ገብታ እስኪሳደብ ድረስ  አስነቀለችው። ከሸፈበት።

3ኛ፦ መጋቢት 7 ዐማራን ዱቄት አድርጌ ትግሬና ኦሮሞን አስደስቼ ከጎኔ በማሰለፍ በአለ ሲመቴን በተለየ መልኩ አከብራለሁ ብሎ የነበረው እቅዱም መና ሲቀር በተለዋጭ ከ20/7/2016 ጀምሮ ቢልም ይኸው ወፍ የለም።

4፦ በአለ ሲመቱን ኦሮሞ ሁሉ ሆ ብሎ እንዲወጣለት በሽመልስ በኩል ብዙ ተስፋ አስነገረ። ጭራሽ ኦሮሞ እነ ሽመልስን ታዘበ፣ አገታቸውም ላይ ገመድ ከተተ እንጂ ጠብ የሚል ነገር ጠፋ።

5፦ አሁን ያለው አማራጭ አዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ሲቲ ያሉትን ኦሮሞዎችና በኦሮሚያ ክልል አናታችሁ ወይም ቤታችሁ ከሚፈርስ በማለት የተረሳውን የሕዳሴ ግድብ ሩጫ በማለት የአቢይን ፎቶ አስይዞ በመውጣት ኦሮሞ ከአቢይ ጎንን ነው ማለት ብቻ ነው።

ዘመዴ

"…ኢትዮጵያችን ድፍን ስድስት የእርድ፣ የጭፍጨፋ፣ የሌብነት፣ የዘረፋ፣ የዝሙት፣ የነውር ጌጥነት፣ የዋልጌነት፣ የዳተኝነት፣ የመርህ አልባነት፣ የዘማዊነት፣ የሆድ አደርነት፣ የአቃጣሪነት፣ የጭካኔ፣ የአረመኔነት፣ የከሃዲነት፣ የአስመሳይነት፣… pic.twitter.com/9zmtV7n9at— YehabeshaTube (@YehabeshaTube) April 3, 2024
https://amharic.zehabesha.com/archives/189599
፳ ፻ ፳ ዓ. ም. ሩቅ ነው - አንዱ ዓለም ተፈራ
ቀላሉ ነገር፤ እኔ የምፈልገውን ይሆናል ብሎ መተንበይ ነው።ሀቁ ግን በጣም የተወሳሰበና ጠለቅ ያለ ምልከታን የሚጠይቅ ነው።ከአራት ዓመታት በኋላ አገራችን ውስጥ ሊከተል የሚችለውን እውነታ ወዲህ ሆኖ ለመተንበይ፤ ብዙ በአገራችን የፖለቲካ ሂደት ውስጥ ያሉ ተለዋዋጭ ጉዳዮችን ማገናዘብ ግድ ይላል።ከሰማይ ዝቀው የሚያቀርቡት ተዓማራዊ እወነታ የለም። አሁን አገራችን ያለችበት የፖለቲካ እውነታ፤ ዛሬ በቦታው ላለነው እንኳ ለመረዳትና እንዲህ ነው! ብሎ ለመግለጥ በጣም አስቸጋሪ ነው።በኢትዮጵያ ተጨባጭ የፖለቲካ እውነታ ደግሞ፤ ፳፻፳ ዓ. ም. በጣም ሩቅ ነው።በዚህ ጽሑፍ ያ ወቅት ሲመጣ፤ በአገራችን ሊከሰት ይችላል የምለውን ለማሳየት እሞክራለሁ።

ከላይ ተንጠልጥሎ ሁሉን የሚገዛው ጉዳይ፤ በመንግሥት ሥልጣን የተቀመጠው አካል እምነትና አካሄድ ነው።ይህን ሥልጣን የሚቆጣጠረው፤ በአገራችን ሕዝብ የቀን ተቀን የኑሮ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ሚና አለው።ይህ እንግዲህ፤በርሻው፣ በንግዱ፣ በትምህርቱ፣ በሕክምናው፣ በሰዎች እንቅስቃሴ፣ በአገር ውስጥ ጉዳይና በውጪ አገራት ጉዳይ ሂደቱ፣ ወደ ሥልጣኔ በሚደረገው ግስጋሴ ወይንም የኋሊይሾ ጉዞ፣በአገራችን ስላምና ልማት፣ በጥቅሉ፤ በነገው እውነታ ላይ ማዕከላዊ የሆነ ሁለተናዊ ሚና አለው። ያ እንዳለ ሆኖ፤ ይሄ አካል ብቻ አይደለም ሜዳውን ተቆጣጥሮ ጨዋታውን የሚመራው። አሁን ያለውን መንግሥት ለመተካትና የተሻለ መንግሥት ለማቋቋም የተሰለፉት፤ ተቀራራቢ ሚና አላቸው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ይሄን አካል በመደገፍ ወይንም በመፎካከር የተሰለፉት የማይናቅ ሚና አላቸው።ሕዝቡ በተደራጀ መንገድም ሆነ ባልተደራጀ መንገድ፤ ለዚህ ሂደት አስተዋፅዖ አለው። እስኪ አሁን ያለውን ሀቅ እንመለከት።

በሥልጣን ላይ ያለው ገዢ ቡድን፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ነው መባሉ ቀርቶ፤ መንግሥት ለመባል በቂ አይደለም። ይሄን ያልኩበትን ምክንያት ላብራራ።የአንድ አገርን መንግሥት፤ መንግሥት የሚያስብለው፤ አገሪቱን ወክሎ ሲገኝ፣ ለአገሪቱ አጠቃላይ ሰላምና ልማት፣ ለመላ ሕዝቡ የኑሮ አመቻች ሆኖ ሲገኝ ነው። እኒህ ብቻ መመዘኛዎች አይደሉም፤ ነገር ግን መሠረታዊ መነሻ ናቸው። እኒህ ካልተሟሉ ሌላው ገብስ ነው።

በነኚህ መመዘኛዎች በአገራችን ያለውን ገዢ ቡድን ስናቆመው፤ ይሽመደመዳል። አንድን ወገን፤ ለዚያውም አክራሪውን ክፍል ወክሎ የቆመ አካል ነው። ያ ብቻ ሳይሆን፤ ዐማሮችን ለማጥፋት መንግሥታዊ ተልዕኮው ያደረገ ነው።እናም አገራችንን ለማስተዳደር ሳይሆን ለመቀየር የተነሳ ነው። በዚህ ሂሳብ ኢትዮጵያዊ ወይንም የኢትዮጵያ መንግሥት አይደለም። ይሄን ያልኩት፤ ገዢው ክፍል አገር አቀፍ የሆነ የተለየ ርዕዩተ ዓለም ስላራመደ ወይንም በተግባር ወደ ሥልጣኔ በፍጥነት ስለሄደ ወይንም ስላዘገመ አይደለም። በመሠረቱ አገር አቀፍ የሆነ ራዕይም ሆነ የፖለቲካ ፍልስፍናና የአስተዳደር መመሪያ ስለሌለው ነው።

ከዚህ ተነስተን፤ ስላምን ባገር ስለማስፈን፣ ስለትምህርት ወይንም ስለሌሎች መንግሥታዊ ተግባራት ማተቱ ከንቱ ነው። እናም ሰላም ሳይሆን ጦርነትን መዝራቱ ከዚህ ማንነቱ ጋር የተያያዘ ነው። ይሄን መንግሥት ወደ ሥልጣን ለማምጣት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ “አትከፋፍሉን!” “አንድ ነን!” ብሎ ነበር የትግሬዎችን ነፃ አውጪ ግንባር ከሥልጣን ያባረረው። ይሄ ገዢ ቡድን ተተክቶ ግን፤ በትግሮች ቦታ ኦሮሞዎችን ከመተካት ያለፈ የለወጠው ነገር የለም። ይልቁንም በበለጠ አረመኔነትና ልክ የሌሽነት፤ ያንኑ የትግሮች ነፃ አውጪ ግንባር የፖለቲካ ፍልስፍናና የአስተዳደር ዘይቤ አፋፋመው። ሕዝቡ ወዲህ፡ የተተካው መንግሥት ወዲያ! በረከትን እና ስብሃትን ፈቶ መስከረምን እና ታዲዮስ ታንቱን የሚያስር! ኦነግ ሸኔን በጉያው አስቀምጦ ዐማሮችን በድሮንና በታንክ የሚደበድብ! ይሄን ገዢ ቡድን፤ ኢትዮጵያዊም መንግሥትም ማለት አይቻልም።

ይሄን ጉዳይ ብቻ መነሻ አድርጎ፤ ፳፻፳ ዓ. ም.ን መተንበይ በጣም ቀላል ነው። የበለጠ ትርምስ፣ የበለጠ መተላለቅ፣ የከፋ ወደፊት ይሆናል። ጥሩነቱ ግን፤ ይሄ አካል ብቻ አይደለም በፖለቲካው ምህዳር ተጫዋች የሆነው። ሌሎች ተጫዋቾችም አሉ። ዐማራው ለህልውናው በሚያደርገው ትግል፤ የፋኖ ድርጅት ከፍተኛ ሚና አለው። ፋኖ፤ ለዐማራው ብቻ ሳይሆን፤ ለነገዋ የኢትዮጵያ መንግሥት እርሾ ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ፤ አሁን በዐማሮች ምድር ያለው፤ ገዢው ቡድን ወራሪ ሆኖ፤ ዐማሮች በፋኖ በኩል መከላከላቸውን ብቻ ሳይሆን፤ መንግሥታዊ ክንውናቸውን እያካሄዱ የለበት ሀቅ ነው። እናም በዐማራው ምድር፤ ፋኖ መንግሥት ነው። ታዲያ የፋኖ ዕድገትና ሂደት፣ የፋኖ ተግባርና እንቅስቃሴ፤ በአገራችን በ፳፻፳ ዓ. ም. ሊመጣ የሚችለውን ሀቅ ተናጋሪ ነው። ፋኖ አንድ ወጥ ሆኖ፤ ሌሎች ይሄንን አክራሪ ገዢ ቡድን “የኔ!” ያላሉ ኢትዮጵያዊያንን አስተባብሮ፤ ነገ የሽግግር መንግሥት ያቋቁማል።

በአንጻሩ ደግሞ፤ አሁን በመንግሥቱ ዙሪያ ያሉ ደጋፊም ሆነ ተፎካካሪ አካላት፤ የዚሁ ትንበያ ተጫዋቾች ናቸው። እነሱ የሚሠጡት የመንግሥት ድጋፍ ወይንም፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከገዢው ቡድን በላይ አድርገው በመመልከት የሚያከናውኑት ተግባር፤ የ፳፻፳ ዓ. ም.ን ሀቅ ሊነግረን ይችላል። ይህ ማለት፤ ገዢውን ቡድን ደግፈው ከቆሙ፤ ከስማጭ መርከብ ጋር ተቆራኝተው፤ ለጊዜው በጎውን መጪ ያዘገዩታል። የገዢውን ቡድን እውነተኛ ዓላማ ተረድተው፤ የራሳቸውን ቀዳዳ አበጅተው ከሕዝቡ ጋር ከቆሙ፤ ለውጡን በማገዝ አገራችን በትክክል ቀና መንገድ እንድትይዝ ይረዳሉ። እናም ፳፻፳ ዓ. ም.ን የተሻለ ቦታ ያስቀምጣሉ።

እንግዲህ ሶስቱን ክፍል ዳሰሰኩ። በዚህ ሂደት የሕዝቡ ተሳትፎ ምንድን ነው? ይሄን ለመመለስ ብዙ ጉዳዮችን ማገናዘብ ያስፈልጋል። በመሠረቱ ሕዝቡ በሰላም መኖር፣ ወጥቶ መግባት፣ ሠርቶ ማደር መሽከርከሪያ የኑሮ አምዱ ናቸው። ፳፻፳ ዓ. ም.ን በሚመለከት፤ በተናጠል ግለሰቦች ከሚያደርጉት አስተዋፅዖ ይልቅ፤ የተደራጁት ዋናውን ሚና ይወስዱታል። እናም የተደራጀው የኅብረተስ ክፍል ወሳኙን ሚና ይጫወታል። ሕዝቡ በግልጥም ይሁን በሕቡዕ የሚያደረው ተሳትፎ በተደራጀ መልክ እስካልሆነ ድረስ፤ አስተዋፅዖውን ግምት ውስጥ ማስገባት ያስቸግራል። ስለዚህ፤ ሕዝቡ ቢበደልም፣ ኑሮ ቢከፋም፣ መብራት ቢጠፋበትም፣ የበርበሬ ዋጋ ቢንርበትም፣ ዳቦ ከሱቅ ባይገኝም፣ የሚያደርገው ሚና አነስተኛ ነው። የ፳፻፳ ዓ. ም. ሁኔታ፤ አሁን ባለው ገዢ ቡድን፣ ይሄን ገዢ ቡድን ተቃውመው በተነሱ አካላትና ገዢውን ቡድን በመደገፍም ሆነ በመፎካከር ተደራጅተው በቆሙ አካላት ይወሰናል።

አሁን ባለንበት ተጨባጭ ሀቅ ደግሞ፤ ገዢው ቡድንና ፋኖ ናቸው የፖለቲካ መድረኩን ባብላጫው ይዘው የሚገኙት። በኔ ግንዛቤ፤ ገዢው ቡድን አጥፊ፣ ወደ ውድቀቱ እያሽቆለቆለ ያለ ኃይል፣ አገር አፍራሽና ኢትዮጵያዊያንን የሚጠላ አካል ነው። ፋኖ እያደገ ያለ፣ ወገኑን እና አገሩን ወዳድ፤ በስነ ስርዓት እየተመራ ያለና የወደፊቱ የበራ ኃይል ነው። በኔ እምነት በ፳፻፳ ዓ. ም.፤ ፋኖ አድጎ ከዚህ የፀረ ኢትዮጵያ ገዢ ቡድን የመንግሥቱን ሥልጣን በጉልበቱ ነጥቆ፤ ሰላምን በማስፈን፤ ዕድገትን አስገኝቶ፤ በውጪ አገራት የተበታተነው ወገኑን አፍቃሪው እና እምቅ ዕሴት ያዘለው ስደተኛ ወዳገሩ ተመልሶ፤ ባጭር ጊዜ ወስጥ አገራችን ታድጋለች። ለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ አስተዋፅዖውን አሁን ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ። መልካሙን እመኛለሁ!!!
https://amharic.zehabesha.com/archives/189615

Wednesday, April 3, 2024

https://youtu.be/WT-cBJ7QqZY?si=NaYZjfdzET6zc5kg

ሰበር : ወሎ ሁለት ጀነራሎች ተደመሰሱ | ፋኖ ደብረብርሃን ገባ ሸዋ የቀለ ጦርነት | ጎጄ ሳተናው ዛሬም እያጨደ ነው ባህርዳር አብይ ኦሮሞን አዋረደ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189611
ጥቁር ቀን: የከሸፈው የበአለ ሲመት ዕቅድ...
1፦ ከመጋቢት 7 ጀምሮ በዐማራ ፋኖ ላይ ከፍተኛ ጦርነት በመክፈት በአለ ሲመቱን በድል አሸብርቆ ለማክበር አቅዶ ወደ ሥራ ለመግባት ሲሰናዳ አባደፋር ፋኖም ይቺን ተረድቶ ከመጋቢት 5 ጀምሮ የአራጁን ሠራዊት ኢሬቻውን አብልቶት አረፈው። በዚህ ላይ ሜጀር ጀነራል ውባንተ ተሰዋና የባሰ የዐማራ 4ቱም ክፍላተ ሀገራት ተጣምረው አንድ ሆነው አፈር ደቼ አስግጠው አዋረዱት። ዐማራን በድሮን ጨፍጭፎ በአለ ሲመቱን ኦሮሞን እያስጨፈረ ሊውል የነበረው ዕቅድ በዘመቻ ውብአንተ ውኃ በላበት

2፦ እንደ ኢትዮጵያ መሪ አክት በማድረግ ከቢሮው ወጥቶ በየክልሉ እየሄደ በሕዝባዊ ውይይት ስም ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ የጉም ተስፋ ለማስጨበጥም አሁን የሚመራው ክልል አዲስ አበባ ብቻ በመቅረቱ አልተመቸውም። እንዲያም ሆኖ በቤተ መንግሥቱ መሰብሰቡ አልቀረም። ጴንጤ፣ እስላሞች፣ ሴቶች፣ የክልል ተወካዮች፣ ባለሀብቶች ሁሉም ተመርጠው ሄደው እሱ እንደሚፈልገው ቢሆኑለትም በመሃል ኦርቶዶክስ ጣልቃ ገብታ እስኪሳደብ ድረስ  አስነቀለችው። ከሸፈበት።

3ኛ፦ መጋቢት 7 ዐማራን ዱቄት አድርጌ ትግሬና ኦሮሞን አስደስቼ ከጎኔ በማሰለፍ በአለ ሲመቴን በተለየ መልኩ አከብራለሁ ብሎ የነበረው እቅዱም መና ሲቀር በተለዋጭ ከ20/7/2016 ጀምሮ ቢልም ይኸው ወፍ የለም።

4፦ በአለ ሲመቱን ኦሮሞ ሁሉ ሆ ብሎ እንዲወጣለት በሽመልስ በኩል ብዙ ተስፋ አስነገረ። ጭራሽ ኦሮሞ እነ ሽመልስን ታዘበ፣ አገታቸውም ላይ ገመድ ከተተ እንጂ ጠብ የሚል ነገር ጠፋ።

5፦ አሁን ያለው አማራጭ አዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ሲቲ ያሉትን ኦሮሞዎችና በኦሮሚያ ክልል አናታችሁ ወይም ቤታችሁ ከሚፈርስ በማለት የተረሳውን የሕዳሴ ግድብ ሩጫ በማለት የአቢይን ፎቶ አስይዞ በመውጣት ኦሮሞ ከአቢይ ጎንን ነው ማለት ብቻ ነው።

ዘመዴ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189599

Tuesday, April 2, 2024

https://youtu.be/QoK8peIeSSE?si=1Ct6TGcGx2nAd-j2

ፋኖ ዝናቡ የአብይን ኮረኔል ሳንባውን አስተፋው | የአብይ የቦንብ ሄሊኮፍተር ተከሰከሰች | ፋኖ ጎንደር ገባ ባለስልጣናት ተማረኩ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189596
https://youtu.be/QoK8peIeSSE?si=1Ct6TGcGx2nAd-j2

ፋኖ ዝናቡ የአብይን ኮረኔል ሳንባውን አስተፋው | የአብይ የቦንብ ሄሊኮፍተር ተከሰከሰች | ፋኖ ጎንደር ገባ ባለስልጣናት ተማረኩ
https://amharic.zehabesha.com/archives/189596

Monday, April 1, 2024

"የሰላም መንገድ አመቻቻለሁ"
March 31, 2024

ጠገናው ጎሹ

ይህንን እንደ ርዕሰ ጉዳይ የተጠቀምኩበትን አባባል የወሰድኩት ለእኩያን የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ቁማርተኞች በሽፋን ሰጭነት ያገለግል ዘንድ የተቋቋመውና ከተሰጠው የሥስት ዓመታት ተልእኮ አንድ ዓመት ብቻ የቀረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን (The Ethiopian National Dialogue Commission) ተብየው በዋና ኮሚሽነሩ (ሰብሳቢው) ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ በኩል ካስተላለፈውና በቢቢሲ የአማርኛው ክፍል ጠቅለል ተደርጎ በ03/28/24 በሪፖርት መልክ ከቀረበ ዜና ላይ ነው።

የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰብሳቢው ፕ/ር መስፍን አርአያ

ይህ አይነት ከዘመን ጠገቡና በእጅጉ አስከፊ እየሆነ በመሄድ ላይ ካለው ግዙፍና መሪር እውነታ ጋር በቀጥታና በግልፅ የሚላተም “እባካችሁ እኛንም ሆነ የሾመንን መንግሥት እመኑን እና ከህልውና አደጋ ለመዳንናም ሆነ ነፃነት፣ ፍትህና እኩልነት የሚረጋገጥባት የጋራ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የምትታገሉበትን መሣሪያ ሁሉ ቁጭ እያደረጋችሁ የምክክር በረከታችን ተሳታፊዎች ሁኑ” አይነት እጅግ ወራዳና ጨካኝ ዲስኩር አዲስና የሚያስገርም ባይሆንም በምሁርነትም ሆነ በእድሜና በሙያ ዓለም ተሞክሮ አንቱ እንባላለን ከሚሉ እንደ ፕሮፌሰሩ አይነት ወገኖች መምጣቱ ግን ቅንና ሚዛናዊ ህሊና ላለው የአገሬ ሰው የሚያሳድረውን የህሊና ቁስለት በቃላት ለመግለፅ የሚቻል አይመስለኝም።

ስለ እውነት በእውነት ከተነጋገርን አገርን አሁን ላለው ብቻ ሳይሆን ለነገው ትውልድም ምድረ ሲኦል ያደረገው፣ እያደረገ ያለው እና ከፀፀትና ከይቅርታ ጋር ፈፅሞ የማይተዋወቀው የጎሳ/የዘር አጥንት ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ተረኛ የበላይ ጠርናፊዎች በድንቁርና እና በመከራ ቀንበር ሥር ያለውን ህዝብ ስድስተኛ ዓመታዊ በዓላቸው (የወንጀል ተውኔታቸው) ተሳታፊ ይሆን ዘንድ በእጅጉ የበሰበሰና የከረፋ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ በሚያላዝኑበት በዚህ አስጨናቂ ወቅት በምሁርነትም ሆነ በተሞክሮ የአንቱታን ክብር  ልንቸራቸው ይገባቸው የነበሩ ወገኖች በምክክርና በሰላም ስም ራሳቸውን አዋርደው መከረኛው ህዝብ ከመከራና ከውርደት አዙሪት ሰብሮ እንዳይወጣ የሚያደርጉትን የህሊና ቢስነትና የምንደኝነት ባህሪና ተግባር አካፋን አካፋ በሚያሰኝ ደረጃ መንገርና መሞገት ቢያንስ የሞራል ግዴታ ሊሆንብን ይገባል።

አዎ! ሰብእናቸው በንፁሃን ደምና የቁም ሰቆቃ ፈፅሞ የበሰበሰውና የከረፋው ገዥ ቡድኖች ለሽፋን ሰጭ አሻንጉሊትነት ከፈጠሯቸውና ካሰማሯቸው አካላት መካከል አንዱ ይኸው የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተብየው መሆኑን ለማስረዳት በስድስት ዓመቱ የእነ አብይ አህመድ አገዛዝ በየትኛውም የረጅም ዘመን የአገርነት ፖለቲካ ታሪካችን ተሰምቶና ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ  በመሬት ላይ ከሆነውና እየሆነ ከቀጠለው  ግዙፍና መሪር እውነታ በላይ የተለየ አስረጅ መፈለግ የጤናማና የሚዛናዊ ህሊና ባለቤትነት አይመስለኝም።

የምክክር ኮሚሽን ተብየው (የእነ አብይ አህመድ የፖለቲካ ሴራና ሸፍጥ መጫወቻ ካርድ) ከተሳካለት በቀሪው አንድ ዓመት ካልሆነ ደግሞ በሚጨመርለት እድሜ ተጠቅሞ የእኩያን ገዥዎችን እድሜ የማራዘም (ከተሳካለት) እጅግ ትውልድ ገዳይና አስገዳይ ተልእኮውን ለመወጣት ጥረት  እንደሚያደርግ ዋናው ኮሚሽነር ነግረውናል።

ስድስት ዓመታት የሆነውንና አሁንም እጅግ አስከፊ በሆነ ደረጃ የቀጠለውን ፖለቲካ ወለድ የመከራና የውርደት ዶፍ ህግ የማስከበርና አገርን (ህዝብን) የመታደግ የተቀደሰ ዓላማና ተግባር እንደሆነ ሊያሳምኑን ሲሞክሩ ጨርሶ ሃፍረት በማይሰማቸው ገዥ ቡድኖች የተመለመሉ፣ የተሾሙና ምንዳዕ የሚሰፈርላቸው ኮሚሽነርሮች ተብየዎች በሚመሩት ኮሚሽን ተአማኒነት ያለውና ዘላቂ ሰላም የሚያረጋግጥ ምክክር መጠበቅ ወይ የለየለት ጨካኝ የብልፅግና ካድሬነት ወይም ድንቁርና ወይም ከመከራና ከውርደት ጋር የመለማመድ ክፉ ደዌ ወይም በእጅጉ ስር የሰደደውና አስከፊ የሆነው አድርባይነት ሰለባ የመሆን ወይም ከፈጣሪ እገዛ ጋር ለመብትና ለነፃነት ከመታገል ይልቅ እግዚኦ ማለትን እንደ የፅድቅ ዋስትና የመቁጠር ደካማነት ፣ወዘተ ካልሆነ በስተቀር ከቶ ሌላ ሊሆን አይችልም።

ዋና ኮሚሽነሩ (ፕሮፌሰሩ) ያነሷቸው ነጥቦች በርከት ያሉ ቢሆኑም ለዘማናት በመሬት ላይ ከሆነውና ከስድስት ዓመታት ወዲህ ደግሞ የበላይነት ጠርናፊነቱን የተቆጣጠሩት  የዚያው ሥርዓት ውላጆች (ኦህዴድ/ብልፅግናዎች) እንኳንስ ለማመን ለመስማትም በሚከብድ ሁኔታ እያስኬዱ ካሉት ፖለቲካ ወለድ መከራና ውርደት አንፃር ሲታዩ ተአማኔነት በእጅጉ የሚጎላቸውና አሳሳቾች ቢሆኑም ከምር ለመረዳት ለሚፈልግ ነፃነትና ፍትህ ፈላጊ ወገን  አስቸጋሪ ስለማይመስሉኝ ብዙ ለማለት የሚያስፈልገኝ ሆኖ አላገኘሁትም።

ፕሮፌሰሩ (ዋናው ኮሚሽነር) አገርን እጅግ ለመግለፅ በሚያስቸግር ሁኔታ ምድረ ሲኦል ያደረገውና እያደረገ ያለው የእነ አብይ አህመድ አገዛዝ ከተፈጥሮውና ከባህሪው ጋር ፈፅሞ ግንኙነት የሌላቸውን አካታችነት፣ ግልፅነት፣ ተአማኔነት፣ መቻቻል ፣መከባበር ፣ ምክንያታዊነት እና ገለልተኝነት የተሰኙ ወርቃማ ፅንሰ ሃሳቦች በኮሚሽን ተብየው ማቋቋሚያ አዋጅ እንዲካተቱ የማድረጉን የሸፍጥና የርካሽ ፖለቲካ ጨዋታ ከምር ወስደው ከእነዚህ መርሆዎች ንቅንቅ እንደማይሉ ለማሳመን ሲቸገሩ መታዘብ ባይገርምም በእጅጉ ያሳዝናል።

ቀደምት ወላጆቹ ደምና አጥንት ከፍለው ከውጭ ሃይል ባርነት ነፃ ሆኖ እንዴኖርባት አድርገው ያስረከቡትን አገር ለእርሱ ዘመን የምትበጅ ዴሞክራሲያዊት አገር በማድረግ የራሱን ታሪክ ከመሥራት ይልቅ ከየግሉ፣ ከየጎሳው፣ ከየመንደሩና ከየቡድኑ እጅግ ጠባብና አደገኛ ፍላጎት ሰለባነት ሰብሮ መውጣት አቅቶት ከፉኛ ለተቸገረ ትውልድ እንዲህ አይነት “መስሎና አስመስሎ መኖርም ወይም አድር ባይነትም የኑሮ ዘዴ ነው” የሚል አይነት  መልእክት ማስተላለፍ ምን የሚሉት የምክክርና የሰላም ተልእኮ ነው?

የኋላ ቀርነታችን ማለትም ከዘመን ጋር አብረን ያለመራመዳችን ምክንያቶች በርካታ ሊሆኑ ቢችሉም በዚህ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የገጠመንና እየገጠመን ያለው የምሁርነትና የመልካም ዜግነት ውድቀት ( crisis of intellectualism and good citizenship) ግን በእጅጉ አስከፊና አስፈሪ ነው።

ግዙፍና ጥልቅ የሆኑ እሴቶች መገለጫ የሆኑትን ፅንሰ ሃሳቦች በተለምዶ ከመጥቀስ ወይም ከማስተጋባት አልፈን ምንነታቸውንና ለምንነታቸውን ለመረዳት ካልሞከርን በስተቀር የእኩያን ገዥዎችን እና ለሽፋን ሰጭነት የፈጠሯቸውንና የፈቃዳቸው አስፈፃሚ ያደረጓቸውን እንደ የምክክር ኮሚሽን ተብየ አይነት  አካላትን ምንነትና ለምንነት የምንረዳበት አረዳድ ወይ በእጅጉ የተንሸዋረረ  ወይም ደግሞ ከግልብ ስሜት የማያልፍ ነው የሚሆነው።

ለነገሩ ሰላምን ሲያስፈልገው እያጋደመና ሲሻው ደግሞ ዘቅዝቆ የሚያርደው የሸፍጠኞችና የእኩያን አገዛዝ የሰላም ሚኒስቴር የሚል አካል አቋቁሞ እጅግ ውድ በሆነ የሰላም ምንነትና ለምንነት እና በመከረኛ ህዝብ ላይ የሚሳለቅ ገዥ ቡድን ከሚገዛት አገር ሌላ ምን ይጠበቃል?

በእነዚህ ገዥ ቡድኖች ከተመለመሉ፣ ከተሾሙና ምንዳዕ ከሚከፈላቸው ወገኖችስ (ኮሚሽነሮች ተብየዎችስ) እውነተኛ ምክክርና የምክክር ውጤት እንዴት መጠበቅ ይቻላል? በሌላ አገላለፅ በቆሻሻ ግባ እና ቆሻሻ ውጣ/ በጉልቻ መለዋወጥ ደዌ በበሰበሰና በከረፋ የጎሳ አጥንትና ደም ስሌት ፖለቲካ ሥርዓት ሥር የሚተነፍስና የሚንቀሳቀስ ኮሚሽን ተብየ እውነተኛ ሰላምን ማምጣት ከሚችል ምክክር ጋር ምን ዝምድና አለው?

ዘመን ጠገብ የሆነውንና ከስድስት ዓመታት ወዲህ ደግሞ እንኳንስ ለማመን ይሆናል (ይደረጋል) ብሎ ለማሰብም በሚከብድ ሁኔታ የሆነውንና እየሆነ ያለውን ፖለቲካ ወለድ ወንጀል ከምርና ከቁጭት ለሚያስተውል የአገሬ ሰው ምክክር፣ እርቅ ፣ መግባባት ፣ መስማማት ፣ ሰላም፣ መረጋጋት ፣ መተባበር፣ አንድነት፣ ሥልጣኔ፣ እድገት ፣ ወዘተ የተሰኙ እጅግ ግዙፍና ጥልቅ የእሴትነት ትርጉም ያላቸውን ፅንሰ ሃሳቦች ምን ያህል እንዳጎሳቆልናቸውና እያጎሳቆልናቸው እንደሆነ (how we terribly abused and abuse them) ለመረዳት የሚቸገር አይመስለኝም።

አዎ! በእውነት ስለ እውነት ከተነጋገርን ይህ የሆነውና እየሆነ ያለው ደግሞ በፊደል ቆጠራውም፣ በሙያና በሥራ ተሞክሮውም እና በእድሜ አንጋፋነቱም አንቱ መባል ሲገባቸው የትክክለኛ ሰብአዊነት መገለጫ የሆነውን የውስጠ ነፍሳቸውን (their inner soul) ምንነትና ለምንነት እጅግ ርካሽና ጊዜያዊ በሆነ ፍርፋሪ ለሚረካ ሥጋቸው አሳልፈው በሰጡና በሚሰጡ ወገኖች የመሆኑ ግዙፍና መሪር ሃቅ ባይገርምም በእጅጉ ያሳፍራል፤ ያስፈራልም ፤ ያሳዝናልም።

ፖለቲካ ወለድ የሆነው የህዝብ የመከራና የውርደት ሰንሰለት በማያዳግም ሁኔታ የሚሰበረው (የሚበጣጠሰው) እና እውነተኛ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን የሚሆነው የተጋድሎ ምክንያታዊነትን፣ አገራዊ ራዕይን፣ ዓላማን እና ግብን ፣ አርበኝነትን፣ ዲሲፕሊንን ፣እንደ ተጨባጭ ሁኔታው ሊተገበር የሚችል ስልትንና ሊጨበጥ የሚችል ውጤታማነትን፣ ሰብአዊነትን፣ ለንፁሃን (ለሲቪሊያን) ደህንነት ብቻ ሳይሆን ለአገርና ለህዝብ ንብረት የመጠንቀቅን እና ብሎም መልካም የሆነች የጋራ አገርን እውን የማድረግን  እጅግ  ወርቃማ አስተሳሰቦችንና አካሄዶችን በሃላፊነት (በመሪነት) በሚሸከምና ታግሎ በሚያታግል ኀይል ብቻ ነው።

ለዚህ ነው የአማራ ፈኖን እና የተጋድሎ መነሻውንና መዳረሻውን የሚጋሩ እና በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል የሚኖሩና የየትኛውም ብሔር/ብሔረሰብ/ነገድ አባል የሆኑ ኢትዮጵያውያን የሚያደርጉት የህልውና፣ የነፃነት፣ የፍትህና የእኩልነት ንቅናቄና ተጋድሎ ለስኬት ይበቃ ዘንድ ሂሳዊና ገንቢ የሆነ ሁለንተናዊ ድጋፍ በእጅጉ አስፈላጊ የሚሆነው።

ያኔም ነው ኮሚቴ፣ ኮሚሽን፣ ቦርድ፣ ወዘተ የሚሰኙትን አካላት ከእኩይ የፖለቲካ ዓላማ ማስፈፀሚያነት ነፃ በማውጣት ለትክክለኛው የህዝብ (የአገር) አገልግሎት ብቻ እንዲመሠረቱና ተልእኳቸውን እንዲወጡ ለማድረግ የምንችለው።
https://amharic.zehabesha.com/archives/189593
የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴና የ1966ቱ ሕዝባዊ አብዮት ዋዜማ - ፫ በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)
(ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደጻፈው)

- የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ እ.ኤ.አ. ከ 1950-1975

1967-74: Ethiopia's Student Movement

‹‹… ጭንቅ ብሎኛል ኢትዮጵያዊ ማን ነው?

ወጣት ሽማግሌው አገር ሲጠየቅ፤

አንዱ ጐጃም ነኝ ሲል ሌላው በጌምድር፤

አንዱ ኤርትራ ሲል ሌላው ተጉለት፤

አንዱ መንዝ ነኝ ሲል ሌላው ጋሙ ጐፋ፤

ኢትዮጵያዊ ነኝ ባይ ብፈልገው ጠፋ፤

እስቲ አዋቂዎች እናንተ ንገሩኝ፤

እኔን ያስጨነቀው ኢትዮጵያዊው ማን ነው…?!››

 

(በ1950ዎቹ በዛን ጊዜው ቀ.ኃ.ሥ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፤ የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረው ኢብሳ ጉተማ፤ ‹‹ኢትዮጵዊ ማነው?!›› ከሚለው ግጥሙ ተቀንጭቦ የተወሰደ)

በአፍሪካና በመላው ጥቁር ዓለም የናኘውና ከፍ ብሎ ከተሰማው የዐድዋው ድል ለሀገራችን ፖለቲካዊ እንጂ የሚጠበቀውን ያህል ኢኮኖሚያዊ ድል እንዳላጎናጸፈን ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ ጣሊያን ለዐርባ ዓመት ዝግጅት አድርጎ፣ አቅሙን አጠናክሮና በሰለጠነ የሚሊተሪ ኃይል፣ በተራቀቀ ወታደራዊ መሳሪያ፣ ዘመናዊ ተዋጊ ጀት ጭምር ታጥቆ ነበር ፋሽስት የሮማን የቀደመ ክብር አስመልሳለሁ በሚል ቁጭት ወደ ኢትዮጵያ የዘመተው፡፡

‹‹… የዛን ጊዜዋ ኢትዮጵያ ግን በወታደራዊ ኃይልም ሆነ በኢኮኖሚ አቅም ረገድ ከዐድዋው ጊዜ እምብዛም የተሻለ አቋም ላይ አልነበረችም፤›› ይላሉ የታሪክ ምሁሩ ባሕሩ ዘውዴ (ፕ/ር) ኢትዮጵያና ኢጣሊያ ከአርባ ዓመት በኋላ በሁሉም ረገድ የነበራቸውን ልዩነት ሲቃኝ፡፡

የፋሽስት ጦር የኢትዮጵያን ጦር በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳክሞ መዲናዋን አዲስ አበባን ሲቆጣጠር በእውነትም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የኃይል ሚዛን ጎልቶ ታየ፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ ራሳቸው ንጉሠ ነገሥቱ ኃይለ ሥላሴም እንዳመኑት ከዐድዋው ድል ዐርባ ዓመታት በኋላ በፋሽስቱ ኢጣሊያ ፊት የነበረችው ኢትዮጵያ ይህን ነው ሊባል በሚችል ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ወታደራዊና ማኅበራዊ ለውጥን አላሳየችም ነበር፡፡ ይህ ደግሞ በቀላሉና ለጊዜውም ቢሆን በአውሮፓውያን ቅኝ ገዢዎች እግር ስር እንድትወድቅ እንዳደረጋት የታመነ ጉዳይ ሆኖ ነበር፡፡ እናም ዐፄ ኃይለሥላሴና መንግሥታቸው አገሪቱ በለውጥና በዕድገት ጎዳና ላይ እንደትጓዝ ለማድረግ ፈጣንና በቀላሉ ሊገታ ማይችል ሁለተናዊ ዘመቻ ነበር የከፈቱት፡፡

የዚህ ዘመቻ ዋንኛው ቁልፍ ጉዳይ ትምህርት መሆኑ የገባቸው ዐፄ ኃይለሥላሴ ሳይውሉ ሳያድሩ ነበር በርካታ ትምህርት ቤቶችን የከፈቱት፡፡ ከዛም ባሻገር ከአገሪቱ የተለያዩ ጠቅላይ ግዛቶች ታዳጊ ልጆችን በራሳቸው ወጪ እያመጡ እንዲማሩ አድርገው ነበር፡፡ በተጨማሪም በርካታ ተማሪዎችን ወደ አሜሪካና አውሮፓ በመሔድ እንዲማሩ ሰፊ የሆነ ዕድልም ተመቻችቶላቸው ነበር፡፡ እነዚህ በውጭ አገር የተማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም ወደ አገራቸው በተመለሡበት ወቅትም፣ አገራቸው ያለችበት ድህነት፣ ኋላ ቀርነትና ጭቆና በእጅጉ ያንገበግባቸው ጀመር፡፡

ከዓመት ወደ ዓመት ከውጭው ዓለም ጋር ግንኙነት የነበራቸው ኢትዮጵያውያን ሌሎች ዜጎችን በተገናኙና ስለሌሎች አገሮች የዕድገት ደረጃ ባነበቡ ቁጥር፣ የሀገራቸው መሪነት ሣይሆን ጭራነቷ ወደ እውነታ የሚጠጋ ሐቅ እንደሆነ እየተገነዘቡ መጡ፡፡ በሚያስደንቅም ሁኔታ ነገሮች ለውጥ ማሳየት የጀመሩት ወጣቱ ትውልድ በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሪነት በመንግሥት ላይ የፖለቲካ ተበቃይ ኃይል ሆኖ ብቅ ባለባቸው በ1950ዎቹ መጨረሻ ዓመታት ውስጥ ነበር፡፡

ለተማሪዎቹ አየል ብሎ መውጣት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች መካከል የ1953ቱ የከሸፈው የመንግሥት ግልበጣ ሙከራ አንዱ መሆኑን የታሪክ ምሁራንና የፖለቲካ ተንታኖች በአንድ ድምፅ ይስማሙበታል፡፡

ቀደም ሲል በ1953 ዓ.ም. ትምህርቱን በአሜሪካ አገር በተከታተለው በግርማሜ ንዋይ በወንድማቸው በጄ/ል መንግሥቱ ንዋይ የተሞከረው የመፈንቅለ መንግሥት የንጉሡን የ‹‹ሥዩመ እግዚአብሔር›› ካባ በመግፈፉ፣ ሥልጣናቸው ተበጋሪ የሆነ ግለሰብ እንደሆኑ አሳየ፡፡ ከዚህ አልፎ ሙከራው በኅብረተሰቡ ውስጥ የነበሩትን ኢኮኖሚያዊና ማኅበረሰባዊ መበላለጦች ቁልጭ አድርጎ አሳየ፡፡ በከሸፈው በሁለቱ ወንድማማቾች የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራም የዛን ጊዜዎቹ የቀ.ኃ.ሥ ተማሪዎች ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተውት እንደነበር በጊዜው ወጥተው የነበሩት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

እንደውም ጄ/ል መንግሥቱ ንዋይ በመፈንቅለ መንግሥቱ ዋዜማ ለቀ.ኃ.ሥ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ባደረጉት ንግግራቸው እንዲህ ብለው መናገራቸው ይጠቅስላቸዋል፤

‹‹እናንተ የነገይቱ ኢትዮጵያ ተስፋዎች የኾናችሁ ተማሪዎች እኛ የለውጥ መስኮቱን ከፍተናል፣ ታላቁን የለውጥ በር የምትከፍቱት ግን እናንተ ናችሁ፤›› በእርግጥም ይሄ ትንቢታዊ ሊባል የሚችል የወቅቱ የጄ/ል መንግሥቱ ንዋይ ንግግር ከዐሥር ዓመት በኋላ አገሪቱን ከዳር እስከ ዳር ለለውጥ በእንዴት ያለ ኅብረትና አንድነት፣ በእንዴት ያለ ቁጣና እልክ ሁሉንም እንዳንቀሳቀሰው እውነታው በተግባር ታይቷል፡፡

የዚህ መፈንቅለ መንግሥት መንሥኤው አገሪቱ የነበረችበት ድህነትና የሕዝቡም መከራና ጉስቁልና ነበር፡፡ ምንም እንኳን በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ብርቱ ፍላጎትና ጥረት የተጀመረው የኢትዮጵያ ሥልጣኔና የዕድገት ሂደት ስር ነቀል ለውጥ ያመጣል ተብሎ ቢታሰብም የኋላ ኋላ በራስ ወዳድነትና ስግብግብነት ምክንያት የተጓጓለትንና ተጠበቀውን ያህል የረባ ዕድገትና ለውጥ ማሳየት ሲሳነው ማስተዋል ለሕሊና የሚቆጠቁጥ ሐቅ ሆነ፡፡ በመሆኑም በፊውዳሊዝም ቅሪቶች ላይ ለሚካሄደው ዘመቻ በንጉሡ ይተማመን የነበረው የብዙዎች ምኞት ቀስ በቀስ እንደ ጉም መተነን ጀመረ፡፡

እንደውም የገዥው መደብ አምርሮ በሚቃወማቸው የመሬት ስሪት ለውጥን በመሳሰሉ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ዐፄ ኃይለ ስላሴ ለውጥ ለማካሄድ ፍላጎት ወይም ችሎታው እንዳልነበራቸው ግልጽ እየሆነ መጣ፡፡ ቀስ በቀስም በንጉሠ ነገሥቱ የሚመራው መንግሥት ራሱ ለአገሪቱ ዕድገት ዋንኛው እንቅፋት ስለሆነ መነሳት አለበት የሚለው ግንዛቤ መልክ እየያዘና እየተጠናከረ መጣ፡፡ በቀ.ኃ.ሥ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ተማሪዎችና አንዳንድ ምሁራንም አገሪቱ ለውጥ እንደሚያስፈልጋት በማመን ሌሎችንም ለማሳመን ጥረት በማድረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ጀመሩ፡፡

ተማሪዎቹ በየዓመቱ በግቢያቸው በሚያቀርቡት የግጥም ውድድርም የዘውዱን ሥርዓት የሚሞግቱና አገሪቱ ያለችበትን አስከፊ የሆነ ኋላ ቀርነት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብም የሚገኝበትን አሰቃቂ ድህነትና ጭቆና የሚየጋልጡ ግጥሞችን ማቅረብ ጀመሩ፡፡ እነዚህ ንጉሠ ነገሥቱና ባለሟሎቻቸው ሳይቀር በሚገኙበት መድረክ የሚቀርቡ ግጥሞች ንጉሡንና ተከታዮቻቸውን ማስኮረፍ ብቻ ሳይሆን በሂደትም ግጭት ውስጥ አስገባቸው፡፡ በ1954 ዓ.ም. ለዩኒቨርሲቲው ቀን/በኮሌጆች ቀን የሚቀርቡት ግጥሞች በተቀዳሚ ለሳንሱር እንዲሰጡ ተጠየቀ፡፡ ተማሪዎቹም እምቢኝ ጽሑፎቻችንን አንሰጥም አሉ፡፡

ንጉሡም በዚሁ ተቀይመው በበዓሉ ላይ ሳይገኙ ቀሩ፡፡ በዓሉ ተከበረ፣ ግጥሞቹም ተነበቡ፡፡ አሸናፊ የሆኑት ግጥሞችም በፀረ-መንግሥትነት ተከሰሱ፡፡ ሦስት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር መሪዎችም ከትምህርት ገበታቸው ተባረሩ፡፡ በየጊዜው በሚከበረው የዩኒቨርሲቲ ቀን ከቀረቡት ዝነኛ ግጥሞች መካከልም፣ ‹‹ምላሴን ተውልኝ!›› በአበበ ወርቄ፣ ‹‹በረከተ መርገም!›› በኃይሉ ገ/ዮሐነስ/ገሞራው፣ ‹‹የገደል ስር አጥንት›› በዮሐንስ አድማሱ፣ ‹‹ኢትዮጵያዊ ማነው?!›› በኢብሳ ጉተማ፣ ‹‹ልረሳሽ እሻለሁ!›› በዋለልኝ መኮንን ይገኙበታል፡፡

በዚህ የተሟሟቀ የለውጥ ሂደትም የተማሪዎቹ እንቅስቃሴ ቀስ በቀስ እየተደራጀና ሌላ መልክ እያዘ በመምጣቱ በመንግሥት ዘንድ እምብዛም አልተወደደለትም ነበር፡፡ ከዚህም የተነሣ የተማሪውና የመንግሥት ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሻከረ በሚሄድበት ወቅት ቆራጥ የተማሪ መሪዎችን የሚያሰባስብ የድርጅት አስኳል በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ተጣለ፡፡

በ1956 ዓ.ም. ቀደም ሲል የተፈጠረው ስብስብ/ማኅበር ተጠናክሮ አዞዎቹ (Crocodiles) የተባለ ጠንካራ የሆነ ስብስብ ሊፈጥር ቻለ፡፡ በዚሁ ዓመትም ብሔራዊ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበርን የሚያቋቁመው ስብሰባ በይፋ ተደረገ፡፡

በዚህ ጉባኤም ማሳረጊያ አስራ ሁለት ገጾች የአቋም መግለጫዎችና ውሳኔዎች ተላለፉ፡፡ የመንግሥትን ቅጣትና ተፅዕኖ ሳይፈራ በኢትዮጵያ የተንሰራፋውን ችግርና አሰከፊ ድህነት ለመታገል ወደኋላ እንደማይል ማኅበሩ አስገነዘበ፡፡ የዐፄ ኃይለሥላሴ መንግሥት ማኅበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ ማሻሸያ እርምጃዎችን ይወስድ ዘንድም ጠየቀ፡፡

ተማሪዎቹ በዚህ ጥያቄቸውም በአርሶ አደሩ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል በጢሰኛውና በባለመሬቱ መሀል ያለው ግንኙነት ሕጋዊ እንዲሆን ጠይቀው ነበር፡፡ በዚህ ስብሳባ ላይ በተካሄደው ምርጫም ብርሃነ መስቀል ረዳ የብሔራዊው ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር የመጀመሪያው ዋና ጸሐፊ ሆኖ ሲመረጥ፣ ባሮ ቱምሳ ደግሞ የዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ማኅበር ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ፡፡

 

- የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴና የመሬት ላራሹ ጥያቄ፤

‹‹መሬት ላራሹን የምትሹ፤

ተዋጉለት አትሽሹ፡፡››

በ1957 ዓ.ም. ብሔራዊ ማኅበሩ ለኃይለ ሥላሴ ፓርላማ አንድ ወሳኝ የሆነ ጥያቄ ይዞ መጣ፡፡ ይኸውም፤ ‹‹የሰባ አምስት በመቶ የአርሶ አደሩን ምርት ባለ መሬቱ እንዲወስድ የሚደነግገው የፍትሐ ብሔር ሕግ ወደ ሰላሳ በመቶ እንዲወርድ፤›› የሚጠይቅ ነበር፡፡

‹‹መሬት ላራሹን›› በፊታውራሪነት ይዞ የተነሣው ተማሪዎቹ እንቅስቃሴ በተመሳሳይም አይነኬ የሚባሉ ሌሎች ጥያቄዎችን ይዞ ወደ አደባባይ ወጣ፡፡ የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ ታሪክ ከ1950ዎቹ አጋማሽ በኋላ ‹‹መሬት ላራሹ›› በሚለው መፍክር ስም የዘመኑ ተማሪዎች ያደርጉት ነበረውን ተከታታይ የተቃውሞ የአደባባይ ሰልፍና በተለይም ደግሞ በ1961 ኅዳር ወር መግቢያ ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልደት አዳራሽ የተካሔደው የተማሪዎቹ ስብሰባ የተማሪዎቹን እንቅስቃሴም ሆነ የአገሪቱን ፖለቲካ መሠረታዊ በሆነ መንገድ እንደቀየረው የታሪክ ምሁራን ያስረዳሉ፡፡

በተጠቀሱት ሁለት ዘመናት መኻል የተማሪውን እንቅስቃሴ ርዕዮተ ዓለምን የአሳብ መደላድል ለመስጠት በማሰብ ራሳቸውን ‹‹ኮሮኮዳይል›› በሚል ስም የጠሩ ጥቂት ተማሪዎች የግራ-ዘመም አሳቦችን የሚያብራሩ ሥራዎችን በማንበብና በአሳቡም ላይ መወያየት ጀመሩ፡፡

የኢትዮጵያን ተማሪዎች እንቅስቃሴ በማጥናት ቀዳሚ የሆኑት አውሮፓዊው ራንዲ ቫልሲቪክ፤ ‹‹Haile Selassie Students the Intellectual and Social Background to Revolution›› በሚለው ሥራቸው እንዳስነበቡት፣ ይሄ ኃይለኛ ምሥጢረኝነት፣ አይገመቴነትና በሌሎች ተማሪዎች ዘንድ አይነኬ የነበረው ከ10-15 ተማሪዎችን የሚይዘው የጥናት ቡድን አባል የነበረው የ27 ዓመቱ ወጣት የቀ.ኃ.ሥ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ ዋለልኝ መኮንን፤ ‹‹On the Question of Nationalities in Ethiopia›› በሚል ርእስ የጻፈውን ባለ አራት ገጽ ጽሑፍ በዩኒቨርሲቲው አዳራሽ በይፋ አቀረበ፡፡

- የብሔር ብሔረሰቦች መብት ጥያቄ በኢትዮጵያ

ይህ በዋለልኝ መኮንን የቀረበው ዝነኛ ጽሑፍ፤ ‹‹ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እስር ቤት/ማጎሪያ ናት፤ ኢትዮጵያዊነትም በአማራነት እንዲያም ሲል በትግሬነት ወይም ደግሞ በሰሜናዊ ኢትዮጵያ ባህልና ማንነት፣ በኦርቶዶክስ ሃይማኖት የተቀነበበ ማንነት ነው፤›› ሲል ወቀሰ፡፡ ይህ ባለ 5 ገጽ ጽሑፍም በተለይም ከኦሮሚያና ከደቡብ የአገራችን ክፍል ለመጡ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ትልቅ ደውልና ማንቂያ ሆኖ ነበር፡፡

‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከ መገንጠል›› የሚለው የእስታሊን መርህም ለመጀመሪያ ጊዜ ለብዙዎች ተማሪዎች ጆሮ ደረሰው የዛን ጊዜ ነበር፡፡ የለውጡ እንቅስቃሴ በጣሙን እየተጋጋለና እየደመቀ፣ ተማሪዎቹም እንደ ‹ታገል›፣ ‹ቻሌንጅ› ባሉ ጋዜጦቻቸው አሳባቸውን እያስፋፉ ትግሉን አፋፋሙት፡፡

ይህ የለውጥ እንቅስቃሴም አውሮፕላን እስከ መጥለፍና በሰሜናዊ አፍሪካና በመካለኛው እስያ ካሉ እንደ ፍልስጤም ነጻ አውጭ ድርጅት ጋር በጋራ ሥልጠና እስከመውሰድ የዘለቀ ግንኙነትን መፍጠር ችሎ ነበር፡፡ የኤርትራና የኦሮሞ ሕዝብ ነጻነት ጥያቄም ከዚሁ ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከ መገንጠል›› ጥያቄ ጋር ተሰናስሎ ነበር በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ ልደቱን አግኝቶ፣ ወደ በረሃ የተመመው፡፡

የሕወሓት ታጋዮችም፤ ‹‹ፍትሕን ተነፍገናል፣ የጭቁን ሕዝባችንም መብቱ ተረግጧል እናም ሁሉም በአገሪቱ ያሉ ብሔረ ብሔረሰቦችና ነጻ ሊወጡ ይገባቸዋል!›› የሚል መርሕን አንግበው ነበር የዩኒቨርስቲና የኮሌጅ ትምህርታቸውን አቋርጠው፣ ‹‹እምቢ ለሕዝባችን፤ እምቢ ለነጻነታችን!›› በማለት ወደ ደደቢት በረሃ ያቀኑት፡፡

እዚህ ጋር ‹‹ከብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ›› ጋር በተያያዘ አንድ ማጥራት ያለብን እውነታ ያለ ይመስለኛል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የብሔር ብሔረሰብ መብት ጥያቄ አሁንም ድረስ ተጋግሎ ያለ ጥያቄ ሲሆን፤ ‹‹ለኢትዮጵያ የመበታተን አደጋን የጋረጠ፤ የዛ ትውልድ ክፉ ዘር›› በሚል የዋለልኝን ጽሑፍ የሚረግሙና የሚተቹ በርካታዎች ናቸው፡፡ እውነታው ግን በሀገራችን የብሔር ብሔረሰቦች መብት ጉዳይ ሲነሳ እንኳን የተማሪ ጥያቄ ቀርቶ የዛን ጊዜው የቀኃሥ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም አልተመሠረተም ነበር፡፡

የታሪክ ድርሳናት እንደሚጠቁመትም፤ የብሔር ጥያቄ ቀድሞ የተጀመረ ትግል ነው፡፡ ኤርትራ ውስጥ የትጥቅ ትግል የተጀመረው ለምሳሌ ከአብዮቱ ብዙ ዓመታት በፊት ፌዴሬሽኑ እንደፈረሰ ነበር፡፡ ከትጥቅ ትግሉ በፊት ደግሞ የፖለቲካ ትግሉ እንግሊዞቹ ሳሉ ጀምሮ ለአሥር ዓመታት ተካሂዷል፡፡ ትግራይ የመጀመሪያው የወያኔ አመፅ የተነሳው ዩኒቨርሲቲው ከመመሥረቱ በፊት ነው፡፡ በኦጋዴን የነበረው ችግርም ቀድሞ ነው የተፈጠረው፡፡

ለአብነትም፤ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ብርሃኑ ድንቄ ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ በጻፉት ‹‹የለውጥ ያለህ›› ተማጽኖና የማስጠንቀቂያ ደብዳቤያቸው፤ ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት ጥያቄ›› በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው ውሎ አድሮ የአገሪቱ አደጋ፣ ቀውስ መሆኑ የማይቀር ሐቅ መሆኑን እንደሚከተለው ገልጸውላቸው ነበር፤

‹‹… ከሁሉ በላይ ግርማዊነትዎ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው እንቅስቃሴ በተለይ የብሔሮች ጥያቄ አንድ ወቅት ፈንድቶ አደጋ እንደሚያመጣ እንዲገነዘቡት እፈልጋለሁ፡፡ ግርማዊነትዎ አቤቱታዬ እንደ ፊተኞቹ ደብዳቤዎቼ ያነጣጠረው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለሥቃይና ለእንግልት የዳረጉትን ጭቆናዎችና ስሕተቶች እንዲያስተካክሉና አሁንም ቢሆን ጊዜው እንዳልመሸ ለማሳሰብ ጭምር ነው፤››

እንግዲህ ልብ ልንለው የሚገባው ጉዳይ ዩኒቨርሲቲ ሳይኖርና ተማሪው ትግል ሳይጀምር በፊት ነበር በሀገራችን ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት›› ጥያቄ ይነሳ የነበረው፡፡

- የዘውዱ መንግሥት የቁጣ በትር በተማሪዎች ላይ  

የዘውዱን ሥርዓት ዙፋን ያነቃነቁ ጥያቄዎችን ይዞ የተነሣው የተማሪዎች የለውጥ እንቅስቃሴ በሥርዓቱ ላይ በፈጠረው ጫና የተነሣ መንግሥት ቀስ እያለ በተማሪዎቹ መሪዎችና አመራሮች ላይ የአፈና፣ የግዞትና የግድያ ርምጃዎችን እንዲወስድ ገፋፋው፡፡ በዚህ ሁኔታም በ1964 የተማሪዎች እንቅስቃሴ ዋና መሪ የነበረው ጥላሁን ግዛው ተገደለ፡፡ ይህ የመንግሥት ዕርምጃ ክፉኛ ያስቆጣቸው ተማሪዎችም፤

ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ?

ዋለልኝ ለምን ለምን ሞተ?

ማርታ ለምን ለምን ሞተች?

በኃይል በትግል ነው፣

ነጻነት የሚገኘው፡፡

በሚል መፈክር የለውጥ እንቅስቃሴያቸውን ወደ ሌላ ወሳኝ ምዕራፍ እንዲሻገር አደረጉት፡፡ በነገራችን ላይ ጥላሁን ግዛው ከንጉሣውያኑ ቤተሰብ የተገኘ ቢሆንም ያን በተረት ተረትና በግብዝነት ላይ የተመሠረተ ማንነት አሽቀንጥሮ ጥሎ እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ራሱን የጭቁኑ ኢትዮጵያውያን ወገን አድርጎ ነበር ሲቆጥር የነበረው፡፡

በአውሮፕላን ጠለፋ ሙከራ ወቅት የተገደሉት ዝነኛው የተማሪዎቹ እንቅስቃሴ መሪና ፖለቲከኛ ዋለልኝ መኮንንም በተመሳሳይ ሁኔታ ራሱን ከጭቁኑ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የሚመድብ ነበር፡፡ የጥቁር አንበሳ የህክምና ዩኒቨርስቲ ተማሪ የነበረችውና በአይሮፕላን ጠለፋው ወቅት በጥይት ተደብድባ የሞተችው ማርታ መብራቱም፣ አባቷ ጄ/ል መብራህቱ ፍስሐ የጃንሆይ ከፍተኛ መኮንንና ባለ ሥልጣን ነበሩ፡፡

እንደ እነ ጥላሁን ግዛው፣ ዋለልኝ መኮንን፣ ማርታ መብራህቱ የመሳሰሉ ኮከብ የሆኑ የትግል አጋሮቻቸውን በእስራት፣ በግዞትና በሞት የተነጠቁ ተማሪዎቹ ትግላቸው መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን አስተማሩበት፣ ቀሰቀሱበት፡፡ ዐድዋና የአምስት ዓመቱ የፋሽስት የኢጣልያን ወረራ ድል የመቶ ሺህዎች ደምና አጥንት ውጤት መሆኑን ተገንዝቦ፤

ፋኖ ተሰማራ፣ ፋኖ ተሰማራ፣

እንደ ሆችሚኒ፣ እንደ ቼጉቬራ፣

በዱር በገደሉ፣ ትግሉን እንድትመራ፡፡

የሚሉት የቆዩ ወኔ ቀስቃሽ ዝማሬዎች የሰልፉና የተቃውሞው ማድመቂያና መቀስቀሻ ሆኑ፡፡ ማንነቱን ለሕዝብ መብትና ነጻነት አሳልፎ ሊሰጥ የተዘጋጀ በነፍሱ የቆረጠ ትውልድ በኢትዮጵያ ምድር ድምፁ እንደ ብዙ ውኆች ድምፅ ከፍ ብሎ ተሰማ፡፡ ቅድሚያ ጩኸቱ ለሀገርና ለሕዝብ ያደረገ ትውልድ፣ ያ ሩቅ አላሚ ቅርብ አዳሪ የሆነ ትውልድ!

ተው ስማኝ አገሬ፣ እረ ስማኝ አገሬ፣

ተው ስማኝ አገሬ፣ ሲከፋኝ ነው መኖሬ፡፡

ስማኝ ያገሬ ሰው፣ በአንድ ላይ ተነሳ፣

ድር ከተባበረ፣ ይጥላል አንበሳ፡፡ በማለት የዘመናት ብሶት እንጉርጉሮውን አሰማ፡፡

- ለውጥ ፈላጊ የዛን ጊዜው ተማሪዎች/ያ ትውልድ፤

‹‹ድሃ፣ ድሃ ምን ታየበት፤

እንዳይማር የሆነበት፤››

ብሎ ትምህርት ለሁሉም ብሎ የጮኸ ትውልድ ነው፡፡ ማንም የማንንም መብት ሰጪና ከልካይ አይደለም ብሎ፣ ‹‹የዲሞክራሲ መብት ያለገደብ ለሁሉም›› በሚል ደሙን አፍሶበታል፡፡ ከሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የተውጣጣ ‹‹ጊዜያዊ ሕዝባዊ መንግሥት አሁኑኑ›› መፈክሩ በሥልጣን ጥመኞች ጥይት ሕይወቱን ገብሮበታል፡፡ ‹‹የሴቶች መብት ይረጋገጥ›› መፈክሩ ጀግና ሴቶችን ወደ ትግሉ አደባባይ አሰልፏል፡፡ ሕይወታቸውን እስከ ጽንሳቸው የከፈሉ ታሪክ መዘገባቸው የትግል እመቤቶችን አፍርቶበታል፡፡

‹‹የሃይማኖት እኩልነት መረጋገጥ›› መፈክሩ እስላምና ክርስቲያኑ በአንድ ዓላማ አሰልፎ፣ አስተቃቅፎ አታግሏል፡፡ ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት ያለገደብ›› ጩኸቱ ኦሮሞው፣ አማራው፣ ትግሬው፣ ጉራጌው፣ ወላይታው፣ አደሬው ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በጋራ እንዲሰለፍ አድርጎታል፡፡ እንግዲህ ይህ ሁሉ የተጠራቀመ የዘመናት ብሶት ወለደው የተማሪዎቹ እንቅስቃሴ በጊዜ ሂደት የ1966ቱን የየካቲት ሕዝባዊ አብዮትን የወለደው፡፡

ይቀጥላል . . .

(ይህ ጽሑፍ ማስታወሻነቱ፤ በቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን መስሪያ ቤት የማይዳሰሱ ቅርሶች /Intangible Heritage/ ከፍተኛ ኤክስፐርት፤ የኢትዮጵያና አፍሪካ ታሪክ ተመራማሪ፣ ተቆርቋሪ ለነበረው ለወዳጄ፤ ለነፍሰ ኄር አቶ ኃ/መለኮት አግዘው እና በቅርቡ በሞት ለተለየን፤ ‹ለታሪክ አዋቂውና ለታሪክ ነጋሪው› ለነፍሰ ኄር፣ ገነነ መኩሪያ/ሊብሮ ይሁንልኝ)፡፡

 

 

 

 

 
https://amharic.zehabesha.com/archives/189590

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...