Thursday, April 4, 2024

ጥቁር ቀን: የከሸፈው የበአለ ሲመት ዕቅድ...
1፦ ከመጋቢት 7 ጀምሮ በዐማራ ፋኖ ላይ ከፍተኛ ጦርነት በመክፈት በአለ ሲመቱን በድል አሸብርቆ ለማክበር አቅዶ ወደ ሥራ ለመግባት ሲሰናዳ አባደፋር ፋኖም ይቺን ተረድቶ ከመጋቢት 5 ጀምሮ የአራጁን ሠራዊት ኢሬቻውን አብልቶት አረፈው። በዚህ ላይ ሜጀር ጀነራል ውባንተ ተሰዋና የባሰ የዐማራ 4ቱም ክፍላተ ሀገራት ተጣምረው አንድ ሆነው አፈር ደቼ አስግጠው አዋረዱት። ዐማራን በድሮን ጨፍጭፎ በአለ ሲመቱን ኦሮሞን እያስጨፈረ ሊውል የነበረው ዕቅድ በዘመቻ ውብአንተ ውኃ በላበት

2፦ እንደ ኢትዮጵያ መሪ አክት በማድረግ ከቢሮው ወጥቶ በየክልሉ እየሄደ በሕዝባዊ ውይይት ስም ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ የጉም ተስፋ ለማስጨበጥም አሁን የሚመራው ክልል አዲስ አበባ ብቻ በመቅረቱ አልተመቸውም። እንዲያም ሆኖ በቤተ መንግሥቱ መሰብሰቡ አልቀረም። ጴንጤ፣ እስላሞች፣ ሴቶች፣ የክልል ተወካዮች፣ ባለሀብቶች ሁሉም ተመርጠው ሄደው እሱ እንደሚፈልገው ቢሆኑለትም በመሃል ኦርቶዶክስ ጣልቃ ገብታ እስኪሳደብ ድረስ  አስነቀለችው። ከሸፈበት።

3ኛ፦ መጋቢት 7 ዐማራን ዱቄት አድርጌ ትግሬና ኦሮሞን አስደስቼ ከጎኔ በማሰለፍ በአለ ሲመቴን በተለየ መልኩ አከብራለሁ ብሎ የነበረው እቅዱም መና ሲቀር በተለዋጭ ከ20/7/2016 ጀምሮ ቢልም ይኸው ወፍ የለም።

4፦ በአለ ሲመቱን ኦሮሞ ሁሉ ሆ ብሎ እንዲወጣለት በሽመልስ በኩል ብዙ ተስፋ አስነገረ። ጭራሽ ኦሮሞ እነ ሽመልስን ታዘበ፣ አገታቸውም ላይ ገመድ ከተተ እንጂ ጠብ የሚል ነገር ጠፋ።

5፦ አሁን ያለው አማራጭ አዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ሲቲ ያሉትን ኦሮሞዎችና በኦሮሚያ ክልል አናታችሁ ወይም ቤታችሁ ከሚፈርስ በማለት የተረሳውን የሕዳሴ ግድብ ሩጫ በማለት የአቢይን ፎቶ አስይዞ በመውጣት ኦሮሞ ከአቢይ ጎንን ነው ማለት ብቻ ነው።

ዘመዴ

"…ኢትዮጵያችን ድፍን ስድስት የእርድ፣ የጭፍጨፋ፣ የሌብነት፣ የዘረፋ፣ የዝሙት፣ የነውር ጌጥነት፣ የዋልጌነት፣ የዳተኝነት፣ የመርህ አልባነት፣ የዘማዊነት፣ የሆድ አደርነት፣ የአቃጣሪነት፣ የጭካኔ፣ የአረመኔነት፣ የከሃዲነት፣ የአስመሳይነት፣… pic.twitter.com/9zmtV7n9at— YehabeshaTube (@YehabeshaTube) April 3, 2024
https://amharic.zehabesha.com/archives/189599

No comments:

Post a Comment

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...