Wednesday, August 10, 2022

የጠፋችን ‘ፅ’ናት
An Eritrean refugee woman seats with a child at the door of a house at Mai Aini Refugee camp, in Ethiopia, on January 30, 2021. - Eritrean refugees in Ethiopia fear their suffering may not be over, as Prime Minister Abiy Ahmed strains to end a brutal conflict in the northern region of Tigray that has rendered them uniquely vulnerable.Nearly 100,000 refugees from Eritrea, an oppressive, authoritarian nation bordering Ethiopia to the north, were registered in four camps in Tigray when fighting erupted in November between Abiy's government and the regional ruling party, the Tigray People's Liberation Front (TPLF). (Photo by EDUARDO SOTERAS / AFP) (Photo by EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images)

በኢትዮጵያ የሚደጋገሙ የዘመናት ጭቆና እና በደል እንደ አዙሪት ከቦ አንደ ዕንዝርት እየተሸከረከረ የሚፈራረቅባት  የመከራ ምድር ሆና ለዓመታት ዘልቃለች ፡፡

በየትኛዉም የአንድ አገር እና ህዝብ መገለጫዎች የሆኑት የባህል፣ ቆንቋ፣ ዕምነት ፣ ፖለቲካ ፣ ርዕዮተ ዓለም ፣ ኢኮኖሚ የመሳሰሉት በተለያየ መንገድ እንዲበረዝ እና እንዲከለስ ተደርጓል፡፡

እንዲያዉም ማንት ማሳያ የሆኑት የአንድ ህዝብ እና ማህበረሰብ ነፀብራቅ የሆኑት  የጥላቻ እና የበቀል ማራገቢያ ሆነዉ ቆይተዋል ፡፡

ለዓመታት አስቀድሞ ኢትዮጵያን የቆየ የአንድነት እና ታላቅነት ምሰሶ ለማናጋት በተለይም ኢትዮጵያዊነት እና ዓማራነት ጠላትነት ሆኖ በማንነት ላይ የተደረገ ብሄራዊ የማሳደድ ዘመቻ የተካሄደበት እንደነበር እና ይህም ቅርፅ እና መልክ ቀይሮ ካለበት ደርሷል፡፡

ለዚህ ሁሉ መጠነ ብዙ ማንት ተኮር የባህል ፣ የቋንቋ፣ የዕምነት እና የኢትዮጵያዊነት  የማጥላላት ፣ መግፋት ምክነያት የኢትዮጵያዉያን አንድነት እና ህብረት በቅርብ እና ሩቅ ዓላማ በፅናት አለመቆም እና አለመቀጠል ነዉ ፡፡

በነፃነት እና በህልዉና ጉዳይ በግል እና በተናጠል በችርቻሮ ማስተጋባት ለሆኑት እና ለሚሆኑት አገራዊ እና ህዝባዊ መከራዎች ዘመን መራዘም ምክነያት ሆኗል፡፡

አገር እና ህዝብ ሲሞት በዝምታ እና በምን ቸገረኝነት የሚያልፍ ነገር ግን የግል እና የቡድን ጥቅም ሲነካ ለምን እያሉ ብሄራዊ ችግርን እና መከራን መርሳት እና ማዘናጋት ከዓላማ አንድነት እና “ፅ”ናት አለመኖር ነዉ ፡፡

ለማናኛዉም አገራዊ እና ብሄራዊ ችግር  ምንጭ  ፅናት ብለን በጋራ መገንዘብ እና መናበብ ሲገባን እና ፅናት (Endurance and persistent  )እና ቁርጠኝነት ( courageous) ጠፍቶ የሰሞነኛ የግል ጫጫት ማስተጋባት ሰሚ ያጣ የቁራ ጩኸት  ከመሆን ሊያልፍ የሚችል ካለመሆኑ በላይ ጠብታ ዉጤት አያስገኘም ፡፡

የዘመናችን ችግር ሁላችንም ኢትዮጵያ እንደ አገር እንትቀጥል ለምንፈልግ  የጠፋችዉን ፅ ማግኘት እና  ‘ፅ’ ናት እንዲኖረን አሁንም አሁንም   “ፅ” ን እናፈላልግ ፡፡ ፅ በፊደል ገበታ ላይ እንጂ በቃላት እና በስነ ቃላት የሚነበብ እንጂ በዕዉን የሌለ በመሆኑ በተግባር እንዲተረጎም  መተውጋት ያስፈልጋል ፡፡  ዕድገት (ብልፅግና) ዕዉንነት  መሠረቱ እና ምክነያቱ ‘ፅ’ ናት  እና በፅናት  በሠለጠነ አስተሳሰብ( ብል’ፅ’ግና) እና ፅናት (አይበገሬነት) ላይ “ፅ”ን ደጋግሞ ማሰብ እና ማንበር ያስፈልጋል ተሰዉራለች እና ነዉ ፡፡

“ ያለ ዓላማ አንድነት እና ፅናት  ነፃነት እና ህልዉና ህልም ነዉ ፡፡”

“ኢትዮጵያን  ሲተባበር  ራሱን እና አገሩን ያስከብር  ፤ ኃይልም ከመተባበር  ነዉ ፡፡”

NEILLOSS –Amber
https://amharic-zehabesha.com/archives/176519

No comments:

Post a Comment

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...