Saturday, July 30, 2022

የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በየሰብአዊ እርዳታ በጫኑ ተሽከርካሪዎች ያልተፈቀደ ጥሬ ገንዘብ እና ቁሳቁሶችን የማስተላለፍ ተግባርን በጽኑ አወገዘ
በአፋር ክልል ሰርዶ ኬላ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ ወደ ትግራይ ክልል አስቸኳይ ድጋፍ እና የሕክምና ግብአቶችን በጫነ ተሽከርካሪ ውስጥ ገንዘብ እና ፈቃድ ያላገኙ እቃዎች ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ሊዘዋወር ሲል መያዙን ገልጿል።

ድርጊቱን የፈጸመው አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋሉንና ተሽከርካሪው ኮሚቴው ከአንድ የንግድ ኩባንያ ለአጭር ጊዜ በኪራይ የወሰደው መሆኑን አመልክቷል።

የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ “ከተገኘው ገንዘብ እና እቃዎች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለኝም ድርጊቱን አጥብቄ አወግዛለሁ” ብሏል በመግለጫው።

ኮሚቴው “በመላው ኢትዮጵያ በትጥቅ ግጭት እና ሌሎች ሁከቶች” የተጎዱ ሰዎችን ብቻ መርዳት የሚፈልግ የሰብአዊ ድርጅት እንደሆነና በኪራይ ያመጣው ከባድ የመኪና አሽከርካሪ ያጋጠመው ሁኔታ በስራው ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

በአፋር ክልል ጉምሩክ ኮሚሽን የሰመራ ቅርንጫፍ ዱብቲ ወረዳ ሰርዶ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ8 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ እና የተለያዩ ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶችን መያዙ ይታወቃል።

ኢዜአ)
https://amharic-zehabesha.com/archives/176382

No comments:

Post a Comment

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...