Monday, July 18, 2022

የግለሰቦች ውስጣዊ ፍላጎት ማርኪያ የሆነው የብሄረሰብ ጥያቄና መዘዙ! - ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)    
ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)          ሐምሌ 18፤ 2022

መግቢያ

የኢትዮጵያን ህብረተሰብ አመሰራረትና አወቃቀር በደንብ ግንዛቤ ውስጥ ሳያስገቡ በተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎች የተነሳው የብሄረሰብ ጥያቄ በተለይም ከትግሬና ከኦሮሞ ብሄረሰብ ለተውጣጡ ኤሊቶች ወደ ቂም-በቀል መሳሪያነት በመለወጥ ይኸው ዛሬ አገራችንን ወደማፈራረስና፣ በተለይም በአማራው ላይ ያነጣጠረ እልቂት እንዲደርስ ዋናው ምክንያት ለመሆን በቅቷል። የህብረተሰብን ዕድገት ውጣ ውረድነት በደንብ ሳያጠኑና ሳይንሳዊ ግንዛቤ ሳይኖር የሚደረግ ትግል የመጨረሻ መጨረሻ ዕውነተኛ ነፃነትን ሳይሆን የሚያስገኘው ህዝባዊ ዕልቂትንና የኋሊት ጉዞን ነው። ሳይንሳዊና ፍልስፍናዊ ግንዛቤ ሳይኖረው የሚደረግ የብሄረሰብ ትግል የሚሉት ፈሊጥና በሌላም መልክ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል በተለይም ለኢምፔሪያሊስት ኃይሎችና የተሟላና ዕውነተኛ ነፃነትን ለሚቀናቀኑ የውስጥና የውጭ ኃይሎች ቀዳዳ በመክፈት ወደ ውስጥ የንጹሃን ዜጎች ደም መፍሰሱ ብቻ ሳይሆን ለሁለ-ገብ ዕድገት የሚያገለግል የተፈጥሮ ሃብትና በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከአለአግባብ እንዲወድም ይደረጋል። በመሰረቱ ተጨቆን፣ ተበደልን ብለው የሚነሱ ከዚህም ሆነ ከዚያኛው ብሄረሰብ የተውጣጡ ኤሊቶች በምሁራዊ እንቅስቃሴ ሂደት ውስጥ ያላለፉና የተፈጥሮን ህግም ሆነ የህብረተሰብን ውስብስበነትና ውስጣዊ ኃይልና ዕድገት ያልተገነዘቡ በመሆናቸው የሰከነና ምሁራዊ የሆነ ውይይት እንዳይደረግ መንገዱን ሁሉ ለመዝጋት በቅተዋል። በተለይም አንገብጋቢ ወደሆኑ የህዝብን ፍላጎት ለማሟላት ብቻ ሳይሆን፣ በተሟላ መልክ አገርን ለመገንባት በሚያስችሉ  እንደ ፊዚክስ፣ አስትሮኖሚ፣ ማቲማቲክስ፣ ባይሎጂና ኬሚስትሪ፣ የህንፃ አሰራር ቴክኒኮች፣ የከተማ አገነባብ ዕውቀቶች፣ የማህበረሰብና የሶስዮሎጂ እንዲሁም የፍልስፍና ዕውቀቶችና፣ በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ ነክ ጉዳዮች ላይ ርብርቦሽ እንዳይደረግ በብሄረሰብ ዙሪያ ብቻ በመሽከርከርና ይህንንም ዋናው የትግል ዘዴ በማድረግ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ዕውነተኛ ነፃነትን እንዳይጎናጸፍና እፎይ ብሎ በሰላም እንዳይኖር ከፍተኛ እንቅፋት ለመፍጠር በቅተዋል። ከኋላ በመነሳት ዛሬ አነሰም በዛም የተሟላ ዕድገትን ከተጎናጸፉ እንደ ጃፓን፤ ደቡብ ኮሪያና ቻይና፣ እንዲሁም ሲንጋፖርና ራሺያ ትምህርት ከመቅሰምና ኃይልን ሰብሰብ አድርጎ በጋራ ከመነሳት ይልቅ የጦር ትግልን በማስቀደምና አስተሳሰብን በዚህ ብቻ በመወጠር አውሬ የሆኑና ምንም የማይገባቸው አስፈሪ ኃይሎች ብቅ እንዲሉና ህብረተሰባችንን እንዲያተረማምሱ ለማድረግ ችለዋል።

በአገራችን የፖለቲካ ትግል ታሪክ ውስጥ ያለው አስቸጋሪው ነገር የህብረተሰብን ዕድገትና የመንግስትን መኪና አገነባብና ሚና አስመልክቶ የተደረገ ጥናት ስለሌለና ለማድረግም ስለማይፈለግ የአስተሳስበ አድማሳችንን ለማጎለመስ በፍጹም አልተቻለም። ምሁራን ነን ብለው እዚህና እዚያ ንግግር የሚያደርጉትንና አንዳንድ ጽሁፎችን የሚያቀርቡትን ለሚያነብ ሰው የሚገነዘበው ጉዳይ አብዛኛዎቹ አቀራረቦች ሳይንሳዊና ፍልስፍናዊ ይዘት የጎደላቸው በመሆናቸው ተከታታይነት ላለው ክርክርና ጥናት የሚጋብዙ አይደሉም። ያለፈውን ወደ ስድሳ ዓመት ኃይል የሚያስቆጥር የምሁራኖችን አስተዋፅዖ ለተመለከተ ጽሁፎቹ ሳይንሳዊ ናቸው የሚያስብላቸው አንዳችም ነገር የለም። የአብዛኛዎቹም አጻጻፍና አስተሳሰብ ለሁለ-ገብ ዕድገትና ሰፋ ላለ የምሁራዊ እንቅስቃሴ፣ እንዲሁም ለሰላም መስፈን የሚያመች አይደለም። ስለሆነም እንደዚህ ዐይነት ምሁራዊ ክፍተት በመኖሩ በፖለቲካ ስም ለማወናበድ የሚፈልጉና የጨለማውን ዘመን የሚያራዝሙ ኃይሎችና፣ እንደዚሁም  ከዚህም ሆነ ሆነ ከዚያኛው ብሄረሰብ የተውጣጡ በጣም ጠባብ አስተሳሰብ ያላቸው ኤሊቶች፣ በመሰረቱ የኢምፔሪያሊስቶችና የአረብ አገር አሽከሮች የሆኑ የፖለቲካ ሜዳውን በመያዝ ህዝቡን ግራ ሲያጋቡ ይታያል።

ስለሆነም በአገራችን ያለው ትልቁ ውዝግብና ወደ ጦርነት ያዳረሰን ጉዳይ በሰፊው የአማራውና በሰፊው የትግሬ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን፣ በሰፊው የኦሮሞና በአማራው እህቶቻችንና ወንድሞቻችን፣ እንዲሁም በአማራውና  በተቀሩት ብሄረሰቦች እህቶቻችንና ወንድሞቻችን መሀከል በተፈጠረ ልዩነትና አለመግባባት ሳይሆን፣ ለእንደዚህ ዐይነቱ ውዝግብና  ጦርነት ዋናው ተጠያቂዎች ከዚህና ከዚያኛው ብሄረሰብ የተውጣጡ የራሳቸውን ጥቅም ከኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ጋር ያገናኙና የእነሱ አሽከር በሆኑ ጥቂት ኤሊቶች  ነው። ትግላችንም መሆን ያለበት ሰፋ ያለና የጠለቀ ዕውቀት ሳይኖራቸው የዶክትሬት ዲግሪን በጨበጡና በፖለቲካ ስም በመነገድ ወንድምን ከወንድምና፣ እህትን ከእህት ጋር በማጋጨት ሰፊው ህዝብ ዕውነተኛ ነፃነትን እንዳይጎናጸፍና የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት በመሆን የተከበረ አገር እንዳይገነባና ለተከታታዩ ትውልድ እንዳያስተላልፍ የሚያወናብዱትንና እንቅፋት የሚፈጥሩ ጥቂት ኃይሎች ላይ ያነፃፀረ መሆን አለበት። ከዚህ በመነሳት ለሁላችንም ግንዛቤን የሚሰጥ በብሄረሰብ ዙሪያ የሚደረግ አግባብነትና ሳይንሳዊ መጨበጫ የሌለው ጉዳይ እንዲቋጭ አጠር ባለ መልክ ለማቅረብ እወዳለሁ።

የህብረተሰብ አመሰራረት ጉዳይ!

የስልጣኔና የህብረተሰብን ዕድገት በቅጡ ላጠናና ለተከታተለ ከዝቅተኛ ሁኔታ በመነሳት ነው ውስጣዊ ኃይል እያገኛና እየተወሳሰበ በመምጣት ከአንድ አካባቢ በማለፍ ሌላ አካባቢዎችን በማዳረስ የበለጠ ውስጣዊ ኃይል ሊያገኝ የሚችለው። በህብረተሰብ ግንባታ ታሪክ ውስጥ ምናልባት በአንድ አካባቢ የሚኖር ጎሳ ወይም ብሄረሰብ የሚሉት ነገር “የተወሰነ የአገዛዝ መዋቅር ቢፈጥርም” የበለጠ ውስጣዊ ኃይል ሊያገኝና ሊዳብር የሚችለው ከሌላ አካባቢ የመጣ ስልጣኔን ውስጣዊ(Internalize) በማድረግና በመስፋፋት ብቻ ነው። በተፈጥሮ ውስጥም እንደዚህ ዐይነቱ ነገር ይታያል። ማንኛውም አትክልትና ዛፍ፣ በጠቅላላው ተፈጥሮ ብለን የምንጠራው ነገር ሁሉ የመዳበር ኃይል ሊያገኝ የሚችለው በፀሀይ፣ በውሃና በልዩ ልዩ ንጥረ-ነገረች አማካይነት ብቻ ነው። እነዚህን እንደምግብ በመጠቀም ነው ቀስ በቀስ ሊያድግና ፍሬ በመስጠት የኋላ ኋላ ለሰው ልጅ ጠቀሜታ ያለው ነገር ሊያበረክት የሚችለው። ይህ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ለምግብ የሚያገልግል ሰብልም ሆነ ፍራፍሬዎችን የሚለግስ አትክልት የግዴታ እንክብካቤ ያስፈልገዋል። በኢንሴክቶች እንዳይጠቃና ፍሬያማነቱ እንዳይቀንስ ከተፈለገም የግዴታ አጥቂ ኢንሴክቶችን የሚገድል ወይም ሊያባርር የሚችል የተባይ ማጥፊያ መርጨት ያስፈልጋል። ከዚህም ባሻገር የተፈጥሮን ህግና የልዩ ልዩ አትክልቶችንና ሰብሎችን ባህርዮች ለማወቅ ሲቻል ብቻ ነው ማባዛትና፣ አሳድጎ ለምግብ ማዋል የሚቻለው። የልዩ ልዩ አትክልቶችንና ዛፎችን ትርጉምና ጠቃሚነታቸውን ለመረዳት በየጊዜው ሳይንሳዊ ምርምር ማድረግ ያስፈልጋል። የተፈጥሮ ሚዛን እንዳይናጋና የአየርና የአካባቢ ቀውስ እንዳይከሰት ጥንቃቄ የትሞላበት እርምጃ መውስደ ያፈልጋል። ምክንያቱም የሰው ልጅ በተፈጥሮ ላይ ጥገኛ እንደመሆኑ መጠን የተፈጥሮን ምንነት ሳይረዳ የሚወስዳቸው እርምጃዎች በሙሉ የተፈጥሮን ሚዛን የሚያናጉና የመጨረሻ መጨረሻም የሰውን ልጅ ጤንነት የሚያቃውሱ ይሆናሉ።  በሌላ አነጋገር፣  የተፈጥሮን ህግ ሳይረዱ በጭፍኑ በተፈጥሮ ላይ የሚደረግ ዘመቻ ከፍተኛ ቀውስን በማስከተል የመጨረሻ መጨረሻ ለብዙ ሺህ ሰዎች ህይወት መቀጠፍ ምክንያት ሊሆን ይችላል። ይህ ብቻ ሳይሆን ተከታታዩ ትውልድ የሚመካበት የተፈጥሮ ሀብትም እንደልብ አይገኝም።

የህብረተስብን ዕድገት ጉዳይ ስንመለከትም ማንኛውም በዓለም ላይ የተመሰረተና ቀስ በቀስ እየዳበረ የመጣ ማህበረሰብ  በራሱ ኃይል ብቻ ያደገበት ጊዜ በፍጹም የለም። ሊዳብርና ከአንድ የዕድገት ደረጃ ወደ ተሻለ ለመሸጋገር የግዴታ በዕውቀትና በከፍተኛ ንቃተ-ህሊና መታገዝ አለበት። ለተሟላ ዕድገት፣ ለህብረተሰብ መተሳሰርና፣ በልዩ ልዩ መልኮች በሚገለጽ ባህላዊ ክንዋኔ ለመበልጸግ የግዴታ ከሌሎች ሻል ብለው ከሚገኙ ማህበረሰቦች ጋር በንግድና በሌሎችም እንቅስቃሴዎች አማካይነት ግኑኝነት መፍጠር አለበት። ይህ መሰረታዊ ጉዳይ ሲሆን፣ በአንድ አገር ውስጥ የሰፈነ መንግስታዊ ስርዓት ከውጭ የሚመጡ ስልጣኔዎችን ስርዓት ባለው መልክ ተግባራዊ ለማድረግና ሁለ-ገብ ዕድገትን ለመጎናጸፍ የግዴታ ከስልጣን ውጭ ባሉ ምሁራዊ ኃይሎች መታገዝና መገፋት አለበት። ምክንያቱም የንቃተ-ህሊና መዳበርና የዕውቀት መፈጠር  አብዛኛውን ጊዜ ከስልጣን ውጭ ባሉና ልዩ ዐይነት ስጦታ ባላቸውና፣ ተልዕኮም አለን ብለው በሚረዱ ጥቂት በሆኑና በተገለጸላቸው ሰዎች አማካይነት ስለሚፈጠር ብቻ ነው። በዓለም ታሪክ ውስጥ በየአገሮች ውስጥ በተፈጥሮ ጥበብን በተካኑና ልክ በአምላክ የተላኩ በሚመስሉ ኃይሎች አማካይነት ብቻ ነው በተፈጥሮና በኮስሞስ ላይ ምርምር በማድረግ ቀስ በቀስ ግን ደግሞ በእርግጠኝነት ለስልጣኔ የሚሆኑ ነገሮች የተፈጠሩትና የሚፈጠሩት። በሌላ ወገን ደግሞ ስልጣንን የተቆናጠጡ ኃይሎች ስልጣናቸው እንዳይነካባቸው ስለሚፈልጉና ይህንንም ዋናው የኑሮ ፍልስፍናቸው አድርገው ስለሚቆጥሩ አስተሳሰባቸው ስልጣንን በመያዝ ብቻ ስለሚጠመድ በዕውቀት ወይም ሳይንሳዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ርብርቦሽ የማድረግ ኃይል አይኖራቸውም። ስለሆነም አንድ ህብረተሰብ ከሞላ ጎደል በስምምነት እንዲኖር ከተፈለገ የተገለጸላቸው ምሁራን አስተዋፅዖ ከፍተኛና ወሳኝ ሚናን ይጫወታል። በዚህም ምክንያት ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የፖለቲካ ፍልስፍና በግሪክ ምድር ሲዳብር በፍትህ ላይ ርብሮቦሽ የተደረገውና፣ የፓለቲካ ፍትሃዊነት ጉዳይ ከሌሎች የማህበረሰብ ጥያቄዎች ጋር በመያያዝ ቀስ በቀስ በጊዜው የሰፈነውን በጨቋኝና በተጨቋኝ መሀከል የሚገለጸው ህብረተሰብአዊ ውዝግብ በምሁራዊ ኃይል ጣልቃ-ገብነት ሊፈታ የቻለው። ስለሆነም ነው እንደ ዲሞክራሲ የመሳሰሉት ጥያቄዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ህብረተሰቡን ሊየስተሳሰሩ የሚችሉ ልዩ ነገሮች፣ ማለትም እንደኪነትና ስፖርት፣ ከዚያም በላይ ኢኮኖሚያዊ የስራ-ክፍፍል የመሳሰሉ ጉዳዮች በመነሳትና መልስም በማግኘት ቀስ በቀስ መንፈሱ የተረበሸውና በጦርነት የተጠመደው ህዝብ መንፈሱን በመሰብሰብ ፈጣሪ ለመሆን የበቃው። በዚህም አማክይነት ብቻ ነው የኋላ ኋላ ሳይንስ፣ ኪነት፣ ስነ-ጽሁፍና ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎችና አስተሳሰቦች ሊዳብሩ የቻሉት።

በሌላ ወገን ደግሞ በአንድ ማህበረሰብ ወይም ህብረተሰብ ውስጥ ከውስጥ የተገለጸላቸው ኃይሎች ብቅ ማለት ካልቻሉና  በስልጣን ላይ ያለውን ኃይል መንፈሱን የሚያድሱ ዕውቀቶችን ማዳባር እስካልቻሉ ድረስ እንደዚህ ዐይነት አገዛዝ ግዛቱን የሚያስፋፋው በጉልበት ብቻ ይሆናል። ይሁንና ግን የተወሰነ ተቀባይነት ለማግኘት ሲል ሳያውቀው አንዳንድ ህዝቡን ሊያስተሳሰሩና ተቀባይነትን ሊያገኙ የሚችሉ በተለይም ባህል በመባል የሚገለጹ ነገሮች  ተግባራዊ እንዲሆኑ ያደርጋል። በአጭሩ በህብረተሰብና በህብረ-ብሄር ግንባታ ታሪክ ውስጥ ከውዝግብና ከጦርነት ነፃ በሆነ መልክ አንድ አገር እንደ ህብረተሰብና ማህበረሰብ የተገነባበት ታሪክ የለም። በተለይም በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገሮች ውስጥ አገርን እንደማህበረሰብ ወይም ህብረ-ብሄር ለመገንባት ኃይል ወይም ጦርነት ወሳኝ ሚናን ተጫውተዋል። በአንድ ግዛት ውስጥ አንጠቃለልም ያሉትንና ወደ ጦርነት ያመሩ መሳፍንታዊ ኃይሎችን በአንድ አገዛዝ ጥላ ስር ለማምጣት ሲባል የግዴታ ጦርነትን ማካሄድ አስፈላጊ ነበር። በተለይም በጀርመን የህብረ-ብሄር ምስረታ ውስጥ ጦርነት ከፍተኛ  ሚና እንደነበረው የሚታወቅ ጉዳይ ነው። ከዚህም በላይ የህብረ-ብሄርን ምስረታ መልክ ለማሲያዝና አገርን በጠንካራ መሰረት ላይ ለማቆም የግዴታ ጥገናዊ-ለውጦችን ተግባራዊ ማድረግና ሁለ-ገብ የሆነ የኢንዱስትሪ ፓለቲካ መከተል አስፈላጊ ነበር። በተጨማሪም በአንድ አካባቢ ብቻ ሳይሆን በአንድ ግዛት ውስጥ ከተማዎችንና መንደሮችን መገንባትና በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ማገናኘት አገርን የመገንባት መሰረታዊ የፖለቲካ ፍልስፍና ነበር። ምክንያቱም በአንድ አገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ አገሩን አገሬ ብሎ ሊጠራ የሚችለው የሚያስተሳስሩት ልዩ ልዩ ነገሮች ሲኖሩ ብቻ ነው። በዚህም አማካይነት ብቻ ነው ህብረተሰብአዊ ኃይል ሊፈጠር የሚቸለውና የኗሪውም የመፍጠር ኃይል ሊዳብር የሚችለው። ምክንያቱም የሰው ኃይል ተሰበጣጥሮ በሚገኝበትና የማያቋርጥ ሽኩቻ በሰፈነበት አገር ውስጥ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ማዳበር ስለማይቻል ነው።

ያም ሆን ይህ የአውሮፓን አገሮች  የህብረተሰብና የአገር ግንባታ ታሪክ ስንመለከት ትግል፣ መዋሃድና መዋዋጥ፣ እንዲሁም ጦርነት ወሳኝ ሚናን ለመጫወት ችለዋል። ስለሆነም ከሌላው የተሻልኩ ነኝ ብሎ የሚሰማው ኃይል፣ በመሰረቱ የብሄረሰብን ፍላጎት ሳይሆን የግዛት መስፋፋትን አስፈላጊነት የተገነዘበና፣ በዚህም የሚያምን በመነሳት ነው አብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገሮች እንደ አገር ሊገነቡ የቻለው። በሌላ አነጋገር፣ በአንዳች ምክንያት ካልሆነ በስተቀር ማንኛውም ተፈጥሮአዊ ነገር ከትንሽ ነገር ተነስቶ የማደግና የመስፋፋት ውስጣዊ-ኃይል ያለውን ያህል ከሞላ ጎደል የህብረተሰብም አመሰራረት ይህንን ዐይነት ሂደት ይዞ በመጓዝ ነው ትልቅ ሊሆንና ሊስፋፋ የሚችለው። ተፈጥሮ ኃይለኛ ሙቀትን፣ ኃይለኛ ዝናብንና ጎርፍን፣ እንዲሁም የመሬት መንቀጥቀጥን እየተቋቋመችና አንዳንዴ ደግሞ አንዳንድ ነገሮች እየወደሙ የምታድገውንና የምትስፋፋውን ያህል ህብረተሰብም ብዙ ውጣ ውረዶችንና ህብርተሰብአዊ ውዝግቦችን በመቋቋም ነው ቀሰ በቀሰ እያለ እየዳበረና እየተሻሻለ የሚሄደው። ይሁንና የሰው ልጅ የማሰብ ኃይል ስላለውና ትክክለኛውን ዕውቀት እስካገኘ ድረሰና በየጊዜውም ራሱን የሚጠይቅና መንፈሱን የሚያድስ እስከሆነ ድረስ በህብረተሰብ ውስጥ ሊደርሱ የሚችሉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መዛባቶችን በማረም ህብረተሰቡ ፈሩን ለቆ እንዳይሄድ የማድረግ ችሎታ አለው።

ስለሆነም በአገራችንም ይህ ዐይነቱ ሂደት ከአክሱም አገዛዝ ጀምሮ እስከፊዪዳሊቱ ኢትዮጵያ ድረስ በመዝለቅና እስከተወሰነ ደረጃም ድረስ በመሻሻል ሁላችንንንም፣ ከዚኸኛው ወይም ከዚያኛው ብሄረሰብ የተውጣጣን በማዋሃድና በማስተሳሰር የኋላ ኋላ ኢትዮጵያ የሚባል አገር ሊፈጠርና የዛሬውን ቅርጽ ለመውሰድ ችሏል። ከአክሱማዊት አገዛዝ ጀምሮ እስከ ፊዩዳሊቱ ኢትዮጵያ ድረስና፣ የኋላ ኋላ ደግሞ ካፒታሊዝም በተቆነጸለ መልክ ሲገባ የተፈጠረውን የህብረተሰብ ዕድገት ሁኔታ ስንመለከት ስልጣንን የተቆናጠጡ ነገስታት በሙሉ አንድም ቦታ ላይ እኔ የዚህ ብሄረሰብ አባል ነኝ፣ ስለሆነም ብሄረሰቤን በመወከልና ጥቅሙን በማስጠበቅና በሌሎች ብሄረሰቦች ላይ የበላይነትን ማስፈን አለብን ብለው የተነሱበትና ትግል ያደረጉበት ጊዜ በፍጹም አልነበረም።  በጊዜውም እንደዚህ ዐይነት ነገር በፍጹም አይታወቅም ነበር። በኢትዮጵያ የአገዛዝና የህብረተሰብ ዕድገት ታሪክ ውስጥ እስከ ደርግ አገዛዝ መውደቅ ድረስ አንዳችም ኃይል በመነሳት የአማራውን ብሄረሰብ ጥቅምና ባህል አስጠብቃለሁ በማለት በሌሎች ላይ የበላይነቴን ማስፈን አለብኝ ብሎ የተነሳበት ጊዜ በፍጹም አልነበረም። የሚፈጠሩና የሚያድጒ ነገሮች፣ በተለይም በባህል የሚገለጹና እንደቋንቋ የመሳሰሉ ነገሮች በአንዳንድ አገሮች ካልሆነ በስተቀር አንድ ሻል ያለ ቋንቋ በራሱ ውስጣዊ ኃልይ በመዳበርና በሌሎች ዘንድ ተቀባይነትን በማግኘት የአብዛኛው ህዝብ አፍ መፍቻና፣ የኋላ ኋላ ደግሞ በሰዋስው መልክ በሚገባ በመቀረጽና በመሻሻል የመጻፊያና የስነ-ጽሁፍ መገለጫ ቋንቋ ሊሆን የሚችለው። በመሆኑም በአገራችንም የአማርኛ ቁንቋ ሻል ብሎ በመገኙትና ውስጣዊ ኃይል ስላለው ብቻ ነው ብሄራዊ ቋንቋ ለመሆን የቻለው።

እንደ ሌሎች አገሮችም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በተለይም ከአራተኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ ከነገስታቱ ባሻገር የክርስትና ሃይማኖት ዛሬ ኢትዮጵያ ለምትባለው አገር የራሱን አስተዋፅዖ ለማበርክት ችሏል። እንደ ግዕዝ ፊደልና ቋንቋ፣ የኋላ ኋላ ደግሞ የግዕዝን ፊደል በመውሰድ የአማርኛ ቋንቋ መጻፊያና መናገሪያ ለመሆን የተቻለው የሃይማኖት ሰዎች ባደረጉት ከፍተኛ የጭንቅላት አስተዋፅዖ አማካይነት ብቻ  ነው። በጠቅላላው ሰዋሰውም ሆነ ሰነ-ጽህፍ፣ ዜማና ቅኝት፣ እንዲሁም የሙዚቃ መሳሪያዎች የተፈጠሩትና የዳበሩት በቤተክርስቲያን አካባቢ በቀሳውስቱ አማካይነት ነው። ቀሳዋስቱም ቋንቋንና ዜማን ሲፈጥሩና ሲደርሱ ሌሎችን ለመጨቆንና የእነሱን ቋንቋ ለመቅበር ሳይሆን በውስጣዊ ፍላጎትና ኃይል በመነሳሳት ብቻ ነው። ስለሆነም እነሱ የፈጠሩልንን የምናከብርና የምናወድስ መሆን አለብን እንጂ እንደመጨቆኛ መሳሪያ አድርጎ በመቁጠር አንዱን ኬላው ጋር ለማጣላትና ለማባላት መታገል ያላዋቂነት ነው፤ አሊያም በሰይጣናዊ ኃይል በመገፋፋት አገርን ለማውደም የሚደረግ ተንኮል ነው።

ከዚህ ስንነሳ በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ከአስራአራተኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ በተለይም በሰሜኑ ክፍል ብቻ ተወስኖ የቀረው ፊዩዳላዊ ስርዓት ሊሰፍንና በውስጡም ደግሞ፣ እህል በመዝራትና ልዩ ልዩ ሰብሎችን በማዳበር፣ እንጀራን በመጋገር፣ ጠላንና ጠጅን እንዲሁም ካቲካላን በመጥመቅ የሚገለጽ ማሀብረሰብ ለመመስረት ተችሏል። ከአስራአራተኛው ክፈለ-ዘመን ጀምሮ የክርስትናን ሃይማኖት ለማስፋፋት በሚል ደብተራዎችንና ቄሶችን ወደ ተቀረው፣ እንደ ከፋ ወደ መሳሰሉት አካባቢዎች ከመላክ በስተቀር የፊዩዳሉ ስርዓት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ግዛት ብቻ ተወስኖ የቀረ ነበር። የፊዩዳሉ ስርዓት ተመሰረተ ከተባለበት ከአስራአራተኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ እስከ አስራዘጠነኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ ከአምስት መቶ ዓመታት በላይ በሰሜኑ የፊዩዳል አገዛዝ ይበዘበዝ የነበረው የአማራው ገበሬ ብቻ ነበር። በሌላ አነጋገር፣ ከአስራአራተኛው ክፍለ-ዘመን እስከ አስራዘጠነኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የሰሜኑ ነገስታትና የአሪስቶክራሲው መደብ በዛሬው መልክ የሚታየውን የደቡቡን ክፍል የበዘበዙብትና ባህሉም ቀጭጮ እንዲቀር ያደረጉበት ጊዜ በፍጹም አልነበረም። በሌላ ወገን ግን አንዳንድ በደቡቡ ክፍል ያሉ አገዛዞች የክርስቲያኑን አገዛዝ ዕውቅና በመስጠት በመሀከላቸው ትስስርና፣ የደቡቡ ክፍል ነገስታትም ግብር(Tribute) ይከፍሉ እንደነበር ይታወቃል። ከዚህ አጠር መጠን ያለ ገለጻ ስንነሳ የአማራው ፊዪዳላዊ ስርዓት በመስፋፋቱ የተነሳ ነው የተቀሩት በዛሬው መልክ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የተጠቃለሉት ግዛቶች ወይም ብሄረሰቦች ባህላቸው ሊቀጭጭ የቻለው፤ ወይም በያዙት የስልጣኔ ሂደት ሊገፉበት ያልቻለው የሚለው አባባል በኢትዮጵያ የህብረተሰብ የግንባታ ታሪክ ውስጥና በሳይንስ የሚረጋገጥ ጉዳይ አይደለም። የደቡቡ ክፍል ከሰሜን በመጡ መጤዎች ሊጨቆን ችሏል ብለው የሚያወሩ የትግሬና የኦሮሞ ኤሊቶች በተለይም ከአውሮፓው የህብረተሰብና የህብረ-ብሄር አገነባብ ታሪክ ጋር ያልተዋወቁ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮ ራሷ እንዴት እያደገችና እየተስፋፋች እዚህ ዐይነቱ ደረጃ ላይ ለመድረስ እንደቻለች ለመረዳት የማይችሉ ናቸው።

ይህን ትተን ወደ ዘመናዊት ኢትዮጵያ አመሰራረት ታሪክ ስንመጣ የዘመናዊ ኢትዮጵያ አስተሳሰብ በአፄ ቴዎድሮ ቢጸነስም፣ ተግባራዊ ለመሆን የቻለው ግን በአፄ ምኒልክ አማካይነት ነው። አፄ ምኒልክም ሲነሱና የኋላ ኋላ ጣሊያንን ድል አድርገው ለዘመናዊ አገዛዝና ማህበረሰብ የሚሆኑ አንዳንድ ነገሮችን ተግባራዊ ሲያደርጉ ጭቆናንና ብዝበዛን፣ ወይም የአንድ ብሄረሰብን የበላይነት ለማስፈን በሚል አስተሳሰብ በመነሳት ሳይሆን፣ አዲስና የተሻለ፣ እንዲሁም ዘመናዊ ህብረተሰብ ለመፍጠር ብቻ ነው። አፄ ምኒልክ ግዛታቸውን አስፋፉ እስከተባለበት ጊዜ ድረስ በተቀረው የኢትዮጵያ ግዛት እንደ ህብረተሰብ የሚገለጽ ስርዓት በፍጹም አልነበረም። በደቡቡ ክፍል የነበሩ አምስት ነገስታት  ከ16ኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ እንዳሉ በኦሮሞዎች መስፋፋት የተነሳ ሊዋጡና ሊወድሙ ችለዋል። ኦሮሞዎች ሲነሱና ሲስፋፉ ደግሞ በከብት እርባታ የሚተዳደሩና በጎሳ መልክ የተደራጁ ስለነበር ያገኙትን በሙሉ አይ በመደምጠጥ፣ አሊያም ደግሞ በመዋጥ ነው ለመስፋፋትና በቁጥር በልጠው ለመገኘት የቻለት። በተስፋፉባቸው ቦታዎች በሙሉ ቋንቋቸውን በኗሪዎቹ ላይ በመጫን መግባቢያ ቋንቋ እንዲሆን ለማድረግ ችለዋል። ከሌሎችም ጋር በመጋባትና ተቀማጭ በመሆን ቀደም ብሎ ከነበራቸው ባህርይና ባህል ቀስ በቀስ እየተላቀቁ ለመምጣት ችለዋል። ይህም ማለት ዛሬ ኦሮሞዎች ነን ብለው የሚጠሩ ሰዎች ከሌሎች ብሄረሰቦች ጋር ሳይጋቡና ሳይዋለዱ እዚህ ደረጃ ላይ የደረሱበት ጊዜ የለም። በህብረተሰብ ዕድገት ሂደት ውስጥም በመጋባት ብቻ ነው እርስ በርስ መተሳሰርና  በስራ-ክፍፍልና በንግድ ወደ ሚገለጽ  ወደ ተሻለ ማህበረሰብ ለመሸጋገር የሚቻለው። በሌላው ወገን ደግሞ እንደ ቋንቋ የመሳሰሉት በአንድ አካባቢ የሚፈጠሩና የሚዳብሩ ነገሮች በመሆናችው ራስን የመግለጫ መሳሪያዎች እንጂ በመሰረቱ ከባዮሎጂ አንፃር አንደኛው ሰው ከሌላኛው ጋር ሲነፃፀር ልዩ መሆኑን የሚያረጋግጡ አይደለም። አሁንም በሌላ አንጋገር፣ ማንኛው ሰው  በእግዚአብሄር አምላክ የሚፈጠር ሲሆን ብሄረሰብ በራሱ ተፈጥሮአዊ ሳይሆን የተወሰኑ ሰዎች በአንድ አካባቢ ሲኖሩና የተወሰነ የሚያስተሳስራቸው ባህል ነክ ነገሮች ሲፈጥሩ  ከሌሎች የሚለዩ መሆናቸውን የሚገልጽ አንዳች የብሄረሰብ ስም ይሰጡታል። ይሁንና በጎሳ መልክ የሚገለጽ የሰው ቁጥር በዚያው ተወስኖ የሚቀር አይደለም። ተወስኖ የሚቀር ከሆነ የማሰብ ኃይሉን ለማንቀሳቀስ የማይችልና ራሱን ከሌላው ሻል ብሎ ከሚገኘው ማህበረሰብ ጋር በንግድም ሆነ በስራ-ክፍፍል ለመገናኘት ያልፈለገ እንደሆን ብቻ ነው። ይህ ከሆነ ደግሞ እንደዚህ ዐይነቱ ሰው ውስጣዊ ፍላጎት የሌለውና፤ የተወሰኑ ነገሮችንም እየተመገበ የሚኖር ብቻ ነው። በአሁኑ በዘመነ-ግሎባላይዜሽን ዘመን ራሳቸውን ከሌላው የማህበረሰብ ክፍል አግልለው የሚኖሩ ጎሳዎች በተወሰኑ አገሮች የሚኖሩ ብቻ ናቸው። እነዚህ ዐይነት ጎሳዎችቭ ደግሞ መንፈሳቸው የረጋና ሌላውን እንግዳ ነው ብለው የሚገምቱትን የማይገድሉ ወይም የሚያባርሩ አይደሉም። እንደዚህ ዐይነቱ ሌሎች ጎሳዎችን መጤ እያሉ ማፈናቀል፣ ማሳደድና አሰቃቂ በሆነ መንገድ መግደል በእኛ አገር ብቻ በአሁን በ21ኛው ክፍለ-ዘመን ጎልቶ የሚታይ አጸያፊ ተግባር ነው። ይህንን ደግሞ የሚያደርጉት አብዛኛዎቹ ብሄረሰቦች ሳይሆኑ፣ ከአሮሞና ከትግሬ የተውጣጡና ወደ አውሬነት የተለወጡ ኤሊቶች ናቸው። የያዙትን መሬትና ተፈጥሮን በጠቅላላው የፈጠሯቸው ይመስል በእህቶቻቸውና በወንድሞቻቸው፣ እንዲሁም በህጻናትና በልጆች ላይ ግድያ በመፈጸም መቆሚያና መቀመጫ ለማሳጣት በቅተዋል። ይህ ዐይነቱ አረመኒያዊ ተግባር እስከ ህንድ ድረስ በመሰማቱ አገራችንን በጣም ኋላ-ቀርና ሰው በላ ሰዎች የሚኖሩባት አገር ናት በማለት ሲጠሩ ይሰማል።

ለማንኛውም እስላም በኢትዮጵያ በመባል የሚታወቀውና በትርሚንግሃም የተጻፈው መጽሀፍ(J.Spencer Trimingham; Islam in Ethiopia) በመሰረቱ የሚያትተው ስለ እስላም ሃይማኖት መስፋፋት ሳይሆን፣ አብዛኛው አትኩሮው ስለኦሮምዎች መስፋፋትና ሌሎች ሻል ብለው ይገኙ የነበሩ አገዛዞችንና የአኗኗር ስልቶችን በመዋጥ የራሳቸውን ቋንቋ በመጫን እንዴት እንደጨፈለቋቸው ነው። በዚህ መጽሀፍ አገላለጽም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ውድመትን ያስከተሉት አማራዎች ሳይሆኑ የኦሮሞ የጎሳ መሪዎች ናቸው። ኦሮሞ የሚባለው ጽንሰ-ሃሳብ ከየት እንደመጣና ትርጉሙም ምን እንደሆነ በፍጹም አይታወቅም። ለምሳሌ አማራ ማለት የተራራ ላይ ኗሪ ሰዎች በመባል የሚታወቅ ሲሆን፣ ኦሮሞ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ግልጽ አይደለም። እንደሚባለው ከሆነ ኦሮሞ የሚባለው መጠሪያ በአንድ የጀርመን የቅኝ-ግዛት አቀንቃኝ እንደተሰጠ ነው የሚታወቀው። ምክንያቱም ኦሮሞዎች በመጀመሪያ መጠሪያ ስማቸው ጋላ በመባል በሚታወቀው ለመጠራት ባለመፈለጋቸው የተነሳ ነው። ይሁንና ግን ጋላ የሚባለው አጠራር በሶማሌዎች ለኦሮሞዎች የተሰጠ ሲሆን፣ ትርጉሙም እንግዳ ወይም ከሌላ ቦታ የመጣ ማለት ነው። ምክንያቱም ኦሮምዎች ከሌላ ቦታ በመምጣት ከሶማሌዎች ጋር ግኑኝነት በመፍጠራቸው ነው። የቦረናው ኦሮሞ የሆነው ፕሮፈሰር ጉፉ ኦባ(Prof. Gufu Oba) „Nomads in the Shadows of Empires“ በሚለው በጣም ግሩም መጽሀፉ የሚያረጋግጠው ጋላ የሚለው ስም የማንቋሸሺያ መጠሪያ ሳይሆን በሶማሌዎች የተሰጠ መሆኑን ነው። ያም ሆነ ይህ እስከ 19ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ ኦሮምዎች በተሻለ የአኗኗር ስልትና የስራ-ክፍፍል የሚገለጽ ማህበረሰብ እንዳልነበራቸው የሚታወቅ ጉዳይ ነው። አብዛኛው የኦሮሞ ማህበረሰብም በከብት እርባታ የሚተዳደር ስለነበር ከዚህ በመላቀቅ ሻል ያለ የስራ-ክፍፍል በማዳበር ወደ ንግድ ልውውጥና የገበያ ኢኮኖሚ በመሸጋገር የተሻለ ማህበረሰብ ለመመስረት የቻለ አልነበረም። ይህ ዐይነቱ ኋላ-ቀርነት በሌሎች የአገሪቱ ግዛቶችና በአማራውም ክፍል የነበረና የሚታይ  ጉዳይ ነው። ይሁንና ሌሎችን ከኦሮሞዎች ለየት የሚያደርጓቸው ተቀማጭ በመሆን ዋናው የኑሮአቸው መሰረት እርሻ እንደነበር ይታወቃል።

ለማንኛውም በኦሮሞ ኤሊቶች ከሳይንስና ከህብረተሰብ ዕድገት ወጭ የሚተረከው የተሳሳተ አባባል አፄ ምኒልክ በመስፋፋተቸው ነው ስልጣኔያችን ሊፈራርስ የቻለው የሚለው አነጋገርና አፃፃፍ ሳይንሳዊ መሰረት የሌለውና በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ግንባታ ታሪክ ውስጥም በፍጹም ሊረጋገጥ የሚችል አይደለም። አፄ ምኒልክ እስከተስፋፉበት ጊዜ ድረስም ቢሆን ከሌላው ጋር በመጋባት የተቀላቀለው ኦሮሞ እስካልሆነ ደረስ አብዛኛው የኦሮሞ ጎሳ በእርሻ የሚተዳደርና፣ ተቀማጭ በመሆን የስራ-ክፍፍልን በማዳበር በንግድ ግኑኝነትና በገንዘብ አማካይነት የሚገለጽ ማህበረሰብ ለመመስረት የቻለ አይደለም። እንደሚታወቀውና ፈላስፋዎችና የአንትሮፖሎጂ ምሁራን እንደሚያስተምሩን ከሆነ አንድ ማህበረሰብ በዕድገት(Progressive) የሚገለጽ ነው:: ይሁንና ማንኛውም ማህበረሰብ ወይም ህዝብ ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ ሊሸጋገር የሚችለው ከሌሎች ጋር ሲዋሃድ፣ ሲጋባ፣ ከሌሎች ሲማርና የተማረውን ወይም የኮረጀውን ሲያሻሽል ብቻ ነው። ይህ ዐይነቱ ሂደት የአብዛኛው የሰው ልጅ ዕድገት ታሪክ ነው።

 

አፄ ምኒልክ ወደ ደቡቡ ክፍል ሲስፋፉ በጊዜው በነበረው ውስን ሁኔታ ወይም ዕድገት ያለመኖር ሁኔታ፣ የተማረ የሰው ኃይል አለመኖር፣ ፈላስፋዎችና ሳይንቲስቶች አለመኖር፣ በአጭሩ የነበራቸው የማህበረሰብ መሰረት ያልተማረና ያልተገለጸለት ስለነበር የህብረ-ብሄር አመሰራረቱና ኢትዮጵያን ዘመናዊ የማድረጉ ጉዳይ እሳቸው በፈለጉትና በተመኙት መንገድ ሊሄድ አልቻለም። የግዴታ ሆኖ በነበረው የስልጣን አደላደል የተነሳ ከሰሜኑ የኢትዮጵያ ለየት ባለ መልክ ፊዩዳላዊ ስርዓት ሊፈጠር ችሏል። በሌላ አነጋገር፣ በደቡቡ ክፍል ርስትና ጉልት የሚባሉ የመሬት አደላደሎች በፍጹም አይታወቁም። ስለሆነም በሰሜኑ የፊዩዳል ስርዓትና በደቡቡ መሀከል ከፍተኛ ልዩነት አለ። አፄ ምኒልክ ግዛታቸውን ወደ ደቡቡ ክፍል ሲያስፋፉ አብዛኛው መሬት ጠፍ ወይም ያልለማ ስለነበር፣ ወይም የእርሻ ተግባር የሚከናወንበት ስላልነበር ነፍጠኛ የሚባሉት መሬት ሲሰጣቸው ከይዞታው የተፈናቀለ የየአካባቢው ኗሪ ህዝብ በፍጽም አልነበረም። በመሰረቱ ነፍጠኛ በመባል የሚወነጀሉት ሰዎች ወደ ደቡቡ ክፍል ሲላኩ አካባቢውን እንዲያስተዳድሩና እንዲያለሙ ብቻ እንጂ ከመጀመሪያውኑ በኗሪዎች ላይ የራሳቸውን ቋንቋና ባህል ለመጫን አልነበረም።  በሌሎችም አገሮችም እንደታየው በዚህ ዐይነቱ አዲስ የአገዛዝ መዋቅር መስፋፋትና የአመራረት ስልት መዳበር የተነሳ የአማርኛ ቋንቋና ልዩ ልዩ ባህሎች በኗሪው ህዝብ ዘንድ ሊወሰዱ ችለዋል። ይህ ጉዳይ ታዲያ እንደ መጥፎ ነገር ወይም የሌሎችን ቋንቋና ባህል እንደመጨፍለቅ መታየት ያለበት ሳይሆን በራሱ ውስጣዊ ኃይል ለመዳበር በመቻሉና ሻል ብሎም በመገኘቱ ብቻ ነው። በሌላ ወገን ግን  አፄ ምኒልክ በጊዜው የነበረውን በእነ አባጅፋር የሚካሄደውን የባሪያ ንግድና ጭቆና ለማስቀረት ችለዋል። ከዚህም በላይ ጨቋኝና በመደብ የተደራጀው የገዳ ስርዓት ሳይወድ በግድ እንዲፈርስ ለመደረግ በቅቷል። እነ አቢይ አህመድና ሌሎች የኦሮሞ ኤሊቶች  እንደሚነግሩን የገዳን ስርዓት ዲሞክራሲያዊና እኩልነት የሰፈነበት ስርዓት ሳይሆን ጭቆና የተስፋፋበትና የበለጠ በጦርነት የሚገለጽ “ስርዓት” እንደነበር የሚታወቅ ጉዳይ ነው። አንደኛ፣ በገዳ ስርዓት ውስጥ ማንኛውም ግለሰብ የመሳተፍ መብት የለውም። የተወሰኑ ስዎችን የሚያሳትፍና  በመደብ ላይ የተመሰረተ አገዛዝ ነው። በሁለተኛ ደረጃ፣ ሴቶች የመሬት ባለቤት የመሆን መብት የላቸውም። በሶስተኛ ደረጃ፣ ዘመናዊ በሚባሉ ዲሞክራሲያዊ አሰራሮች የሚገለጽ ስላልነበር ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ ዕድገት፣ እንዲሁም ለሌሎች የፈጠራ ስራዎችም የሚያመች አልነበረም። ፍልስፍናዊና ሳይንሳዊ መሰረቱም ምን እንደሆነ በፍጹም አይታወቅም። በእነ ፍሪድሪሽ ኤንግልስ አተናተን መሰረት እንደዚህ ዐይነቱ ስርዓት ኋላ-ቀር ናቸው በሚባሉ ማህበረሰቦች ውስጥ የነበረ የአኗኗር ዘዴ ነው። ዋናው ተግባሩም ጦርነትን ማካሄድና ሌሎችን በማሸነፍ የሚገለጽ እንጂ ስልጣኔን አፍላቂና ስልጣኔን አስፋፊ አይደለም። ከዚህ ሀቅ ስንነሳ ዛሬ ኦሮሚያ ክልል ተብሎ የሚጠራው ሌሎችን በማፈናቀል ወይም ከራስ ጋር በማዋሃድ በኃይል የተወሰደ ቦታ ከመጀመሪያውኑ ኦሮሞ በመባል የሚጠራው ጎሳ መኖሪያ አልነበረም። የገዳ ስርዓትም ኋላ-ቀር ስለነበር የአገዛዝ መዋቅር አልነበረውም። ስለሆነም ስርዓቱ በዘመናዊ ኢንስቲቱሽንና በቢሮክራሲያዊ አሰራር ዘዴ የሚተዳደር እንዳልነበር ነው ታሪኩ የሚያረጋግጠው። ዛሬ የኦሮሚያ ክልል ተብሎ የሚጠራው ክፍል የሀዲያዎች፣ የከንባታዎች፣ የጃንጀሮዎችና የየም ኗሪዎች ቦታ የነበረና በኦሮሞ ወራሪዎች የተነጠቀ ነው። ስለዚህም ኦሮሞዎች መልሰው ሌላውን መጤ እያሉ የሚያሳድዱበት ምክንያት በፍጹም ሊኖር አይችልም፤ መብትም የላቸውም። ኦሮሚያ በመባል አርቲፊሻል ስም የተሰጠው ቦታ ብቻ ሳይሆን ጠቅላላው ኢትዮጵያ የጠቅላላው ኢትዮጵያ ህዝብ ሀብት ነው።፡ቀደም ብዬ ለማሳየት እንደሞከርኩት ኦርሞዎች ከመስፋፋታቸው በፊት ከአስራአራተኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ አንዳንድ አማራዎች በደቡቡ ክፍል እየተላኩ ሃይማኖትን ያስተምሩና፣ እዚያውም በመቅረትና በመጋባት እንደተዋሃዱ የሚታወቅ ጉዳይ ነው። ዛሬ ኦሮሚያ ተብሎ የሚጠራው ክፍል ቀደም ብሎም ሆነ ኋላ ላይ በአማራዎችና በሌሎች የብሄረሰብ ኗሪዎች ይለማ እንደነበር፣ በተለይም አፄ ምኒልክ ግዛታቸውን ሲያስፋፉ በዚያው መጠንም የእርሻ ስራና ልዩ ልዩ የሰብል ዐይነቶች ሊስፋፉና አነሰም በዛም የስልጣኔ መሰረት ሊሆን እንደቻለ የሚታወቅ ጉዳይ ነው።

 

ስለሆነም የኦሮሞ ኤሊቶች ትረካ ሳይንሳዊ መሰረት የሌለውና በታሪክም የሚረጋገጥ አይደለም። በሌላ ወገን ደግሞ የግዴታ የገዳን ስርዓት መመለስ አለብን ብለው የሚታገሉት እነ አቢይ አህመድና ሺመልስ አብዲሳ፣ እንዲሁም ሌሎች የኦሮሞ ኤሊቶች በመኪና ከመሄድ ይልቅ በፈረስ መጋለብ አለባቸው። በቪላ ቤትና በቤተ መንግስት ውስጥ ከመኖር ይልቅ በጎጆ ቤቶች ውስጥ መኖር አለባቸው። በተጨማሪም ሌሎች ብሄረሰቦች የፈጠሯቸውን እንደ እንጀራና ወጥ፣ እንዲሁም ጠጅና ጠላ መብላትና መጠጣት የለባቸውም። ስለሆነም ባህላችን ነው፣ ይህንን ነበር ስንመገብና ስንጠጣ የነበርነው የሚሏቸውን ነገሮች መመገብ አለባቸው። በአጭሩ ዘመናዊ ከሚባሉ የአኗኗር፣ የአመራረትና የፍጆታ አጠቃቀም ዘዴዎች በሙሉ በመላቀቅ ወደ ኋላ ተጉዘው የገዳን ስርዓት መመስረት ይችላሉ። ይህንን ለማድረግ ከፈለጉ ደግሞ በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ሳይሆን ሌላ ቦታ መፈለግ አለባቸው። ምክንያቱም ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚገለጽ የአመራረትና የአኗኗር ዘዴን ስለሚመኝና፣ በአርትስ፣ በቆንጆ ቆንጆ ከተማዎች የሚገለጽ ማህበረሰብ በመመስረት ሰው መሆኑን ለማረጋገጥ ስለሚፈልግ ነው። ስለሆነም የዚህ ዐይነቱ የስልጣኔ መሰረት ገዳ ሳይሆን. ፍልስፍናና ሳይንስ፣ ኢኮኖሚክስና ሶስዮሎጂ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የህብረተሰብን ችግር መፍቻ ዕውቀቶች ናቸው።       

 

የካፒታሊዝም መግባትና የብሄረሰብ ጥያቄ መነሳት!

የተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎች በአገራችን ውስጥ ነበር ስለሚባለው የብሄረሰብ ጭቆና ሲያወሩ የካፒታሊዝም ወደ አገራችን መግባት የፈጠረውን አዲሱን የህብረተሰብ አወቃቀርና፣ ህዝባችን በብሄረሰብ ሳይሆን በመደብ የተከፋፈለ ህብረተሰብ(Social Differentiation) መሆኑን በደንብ ለመመርመር የቻሉ አልነበሩም። ሰለመደብ መኖር ቢያወሩም፣ በጊዜው የነበረው ጭቆና አጠቃላይና፣ አንደኛውን ብሄረሰብ ከሌላው ብሄረሰብ ሳይነጠል በሁሉም ላይ የሰፈነ መሆኑን በፍጹም የተገነዘቡ አልነበሩም። በሌላ አነጋገር፣ የተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎችና የብሄረሰብ አቀንቃኞች ስለማህበረሰብ ሳይንስ(Sociology) የነበራቸው ግንዛቤ ወይም ዕውቀት ይህ ነው የሚባል አልነበረም። ከዚህም ባሻገር ካፒታሊዝም በምን መልክ እንደገባና የራሱ የሆነ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደነበረው የጻፉትና የሚያውቁት ነገር የለም ብል የምሳሳት አይመስለኝም። እንደምገምተው ከሆነ ከ1960ዎች ዓመታት ጀምሮ በተለይም በምዕራብ አውሮፓ የካፒታሊስት አገሮች ይካሄድ በነበረው ስለህብረተሰብ ለውጥና(Transformation Debate)፣ በአንትሮፖሎጂና በፍልስፍና ዙሪያ በሚደረገው ክርክርና ጥናት ውስጥ የተሳተፉ አልነበሩም። በአብዛኛዎች የሶስተኛው ዓለም አገሮች ስለሚታየው ያልተስተካከለ ዕድገት(Unequal Development) ዋናው ምክንያት ምን እንደሆነ የሚያውቁት ነገር ያለ አይመስለኝም። ስለሆነም ካፒታሊዝም ወደ አገራችን ምድር ሲገባ በደንብ ተጠንቶ ተግባራዊ ባለመሆኑና ውስጣዊ ኃይሉም ደካማ ስለነበር  ያልተሰተካከለ ዕድገት(Uneven
https://amharic-zehabesha.com/archives/175240

No comments:

Post a Comment

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...