Thursday, June 30, 2022

የአስራ አምስት ቀን ህፃን! - በላይነህ አባተ
ንፁህ የአማራ ደም ወለጋ ተንጣሎ፣

ጠራርጎ ሊወስደው ዓባይ መጣ ደሞ፣

የተከሉት ችግኝ ስላልዋጠው መጦ፡፡

የደም ጅረት ሲፈስ ፀጥና እረጭ ያሉ፣

የዓባይ ጎርፍ ሲባል መብረቅ ይሆናሉ፡፡

የአስከሬን ተራራን ተመጤፍ ያልጣፉ፣

ምሁር ተብዮዎች ግድብ ይዘክራሉ፡፡

የአስራ አምስት ቀን ህፃን ተደፍታ ስታለቅስ፣

ተናቶች ታያቶች የሬሳ ክምር ውስጥ፣

ምኑን ሰው ሆንና ቆመን የምንሄድ፡፡

ኧረ ተው የሰው ልጅ በሰውነት ቀጥል፣

ተበግ መንጋ አትውረድ በአባይ በመደለል፡፡

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ሰኔ ሁለት ሺ አስራ አራት ዓ.ም.
https://amharic-zehabesha.com/archives/173759

No comments:

Post a Comment

https://youtu.be/VUfa5eupQTc?si=Zm73w18dFB27xlqD       https://youtu.be/LcFmz2Xq5MY?si=7uP6VZsd2ksEulUf   https://youtu.be/7dUVmj8go7s?si=Px...